ch
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

前往频道在 Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

显示更多
2 274
订阅者
+524 小时
+117
+3430
帖子存档
ሰይጣን በጭራሽ እንድታውቁት የማይፈልገው ነገር!! ጠላታችን ሰይጣን እንዳትደርሱባቸው የሚፈራቸው ምሥጢራት!! ጸሎት በአጋንንት ውጊያ ወቅት #ጸሎት #መዝሙር https://youtu.be/1EsqB30YQJ0?si=UZMMoC0d62GCutOx

🙏 ካናዳ ያላችሁ ተዘጋጅታችኋል! ላልሰሙት አሰሙ በካናዳና በአቅራቢያው ለሚገኑ በሰሜን አሜሪካን በካናዳ ካል ጋር የተዘጋጀ መንፈሳዊ አገልግሎት! የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ አገልግሎት በምዕራ
🙏 ካናዳ ያላችሁ ተዘጋጅታችኋል! ላልሰሙት አሰሙ በካናዳና በአቅራቢያው ለሚገኑ በሰሜን አሜሪካን በካናዳ ካል ጋር የተዘጋጀ መንፈሳዊ አገልግሎት! የመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ አገልግሎት በምዕራብ በካናዳ ሃገረ ስብከት በካልጋሪ መካነ ሰላም መድኃኒአለም ቤተ ክርስቲያን ከ (July ,18 19 20, 2025 ወይም ሐምሌ 2017.ዓ.ም መርሐ ግብሩ ይጀመራል ወንጌል ሁል ጊዜ አዲስ ነውና ላልሰሙት አሰሙ ትውልድ ይዳን ለበለጠ መረጃ ይደውሉ +4033544410, +15872279769, +14036040477 ሸር ያድርጉ ለሁሉም እንዲደርስ!

እግዚአብሔር ታላቅ ነገር ሊሰጠን ሲል እነዚህን ምልክቶች ታያላችሁ! ልታውቁትና ልትጠነቀቁት የሚገቡ ነገሮች! https://youtu.be/tXTs8Nl5YD0?si=8FBJKi6xFQ4h5A4j

በስህተት የተወረወረ መተት በገዛ ልጆቿ ላይ ያስከተለውን ጣጣ ተመልከቱ!! ሳይገባን ጸበል ለጸበል የምንዞር ሰዎች ይኼንን አዳምጡ!! #ethiopia #ጸሎት https://youtu.be/AWluwcHUS1Q

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 21 +++ ኢየሱስም ወደ ፊልጶስ ቂሣርያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን። ሰዎች የሰውን ልጅ ማን እንደ ሆነ ይሉታል? ብሎ ጠየቀ። እነርሱም። አንዳንዱ መጥምቁ ዮሐንስ፥ ሌሎችም ኤልያስ፥ ሌሎችም ኤርምያስ ወይም ከነቢያት አንዱ ነው ይላሉ አሉት። እርሱም። እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ስምዖን ጴጥሮስም መልሶ። አንተ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ነህ አለ። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ። እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም። የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል። ያን ጊዜም እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ ለማንም እንዳይነግሩ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው። (የማቴዎስ ወንጌል 16፡13-20)

«ምእመናን በቤታቸው የተባረከ ዘይት ይኑራቸው። ይህንንም ሲጠቀሙ እንደ አስማት ወይም ድግምት ሳይሆን፣ በእምነትና በጸሎት ይሁን። ጸጋው በራሱ በዘይቱ ውስጥ ሳይሆን፣ የምእመናንን ጸሎት በሚሰማው በእግዚአብሔር ኃይል ውስጥ ነውና። ይኼም ማለት ማንኛውም ምእመን በሕመም ወይም በመንፈሳዊ ተጋድሎ ጊዜ የእግዚአብሔርን ምሕረት እየጠራ ራሱን ወይም የሚወዷቸውን ሰዎች መቀባት ይችላል።» «Let the faithful keep blessed oil at home. Use it with faith, and not as a magic charm, but with prayer. For the grace is not in the oil itself, but in the power of God who hears the faithful. This means Any believer can anoint themselves or loved ones in times of sickness or spiritual struggle, invoking God's mercy.» (አባታችን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

=> ቅዱስ ፓይስዮስ እንዲህ ብሏል፡- “ትንሽ ያልተፈታ ግጭት እንኳን አጋንንት ትዳርን እንዲያፈርሱ ቦታ ሊሰጣቸው ይችላል። ሁልጊዜ ከመተኛታችሁ በፊት ታረቁ።” => እርስ በርሳችሁ እንዲህ ተባባሉ፡- “በቃል፣ በሐሳብ፣ ወይም በድርጊት ዛሬ አንተን/አንቺን አስከፍቼህ/ሽ እንደሆነ ይቅር በለኝ/በይኝ።”

ሰኔ ፳፩ /21/ በዚች ቀን ከምስር አገር ቅዱስ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ከእንዴናው ገዥ ከአርያኖስ ጭፍራዎች ውስጥ ነበር ሰው ሁሉ ጣዖታትን እንዲያመልክ የሚያዝ የዲዮቅልጥ
ሰኔ ፳፩ /21/
በዚች ቀን ከምስር አገር ቅዱስ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ከእንዴናው ገዥ ከአርያኖስ ጭፍራዎች ውስጥ ነበር ሰው ሁሉ ጣዖታትን እንዲያመልክ የሚያዝ የዲዮቅልጥያኖስ የመልእክት ደብዳቤ በተነበበ ጊዜ ይህ ቅዱስ ከሕዝቡ መካከል ተነሥቶ የንጉሡን ደብዳቤ ወስዶ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለም ብሎ የከሀዲውን ንጉሥ የመልእክት ደብዳቤ ቀደደ። መኰንኑም ድፍረቱን አይቶ ጽኑ ስቃይን አሰቃየው እርሱም የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ርዳኝ እያለ ይጮኽ ነበር። ጌታችንም ትዕግሥቱን አይቶ መልአኩን ልኮ ከሥቃዩ አድኖ ጤነኛ አደረገው ወደ መኰንኑም ቀርቦ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከአንዱ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ የለምና አንተ ከሀዲ እፈር አለው። ያን ጊዜም ይዞ ጽኑ ሥቃይን አሠቃየው በመጋዝም መግዞ ሰቀለው ከዚያም በኋላ ሥጋው እንደ ሰም ቀልጦ እንደ ውኃ እስቲፈስ በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰለው ከከተማ ውጪም ጣሉት። ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ያለምንም ጉዳት አንሥቶ ጤነኛ አደረገው። ወደ መኰንኑም ተመልሶ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀርሌላ አምላክ የለምና አንተ ከሀዲ እፈር ብሎ ጮኸ። ይህንንም ድንቅ ተአምር አይተው ቁጥር የሌላቸው ብዙ አሕዛብ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ሞቱ። መኰንኑም ማሠቃየቱ በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። የድል አድራጊነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ዛሬው ዕለት የሰኔ ጎሎጎታን ጸሎት ሳትጸልዩ በጭራሽ እንዳትውሉ! የሰኔ ጎሎጎታ ጸሎት በረከቶች! ሰኔ 21 ለምን ይከበራል? #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/2a2Q8N6FkxY

በዛሬው ዕለት የሰኔ ጎሎጎታን ጸሎት ሳትጸልዩ በጭራሽ እንዳትውሉ! የሰኔ ጎሎጎታ ጸሎት በረከቶች! ሰኔ 21 ለምን ይከበራል? #hailegebrielreacts19 https://youtu.be/2a2Q8N6FkxY

ይኼንን ጉድ ስሙ! ሀብታሞችና ዘፋኞች የግል ልብስ ሰፊ የሚቀጥሩት ለዚህ መሆኑን ያውቃሉ! የእግር ኳሱ አለም የመናፍስት ሴራ ሲገለጥ! https://youtu.be/kP0bEud7yB8?si=cL_ZKUuApenNRUmI

እንኳን አደረሳችሁ! ++ ሕንጸተ ቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም።  የቤተ ክርስቲያን መታነጽ በእመቤታችን ስም #ሰኔ_21 => ጌታችን በዐረገ በስምንተኛው ዓመት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ወደ ፊልጵስዩስ ገብተው በክርስቶስ ስም አሳምነው ብዙ አሕዛብን ካጠመቁ በኋላ ቤተ ክርስቲያን ሊሠሩላቸው ወደዱ፡፡ በዚህ ጊዜ ርእሰ ሐዋርያት እያለ እኛ መሥራት አይገባንም ብለው በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ላኩበት፡፡ እርሱም ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር መጥቶ ከቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ በርናባስ ጋር በኢየሩሳሌም ተገናኙ፡፡ በዚያም በአንድነት ሱባዔ ይዘው ከቆዩ በኋላ ጌታችን የሞቱትን አስነሥቶ፣ ያሉትንም ጠርቶ ቅዱሳን ሐዋርያትን #በፊልጵስዩስ አገር ሰብስቦ ‹‹በእናቴ በድንግል ማርያም ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚሠራዉን የአብያተ ክርስቲያናት ሥራ ላሳያችሁ፤ ሥርዓቱንም ላስተምራችሁ ሰብስቤአችኋለሁ›› ብሎ ወደ ምሥራቅ ይዟቸው ወጣ፡፡ ++ በዚያም ሥፍራ የነበሩትን ሦስት ድንጋዮችንም የተራራቁትን አቀራርቦ፣ ጥቃቅኑን ታላላቅ አድርጎ ቁመቱን በ፳፬፤ ወርዱን በ፲፪ ክንድ ለክቶ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰጣቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ሰም እሳት ሲያገኘው እንዲለመልም፣ ድንጋዩ በእጃቸው ላይ እየተሳበላቸው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ሠርተው ፈጽመዉታል፡፡ ++ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ የተሠራዉም ጌታችን በዐረገ በ፲፱ኛው፤ እመቤታችን በዐረገች በ፬ኛው ዓመት ሰኔ ፳ ቀን ሲኾን፣ በ፳፩ኛው ቀን (በማግሥቱ) ኅብስት ሰማያዊ፣ ጽዋዕ ሰማያዊ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ወረደ፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችን ጋር ከሰማየ ሰማያት መጥቶ እመቤታችንን ታቦት፤ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ “ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ“ ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ ++ ንጽሕት በድንግልና፣ ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ወላዲተ አምላክ ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ትሰውረን።

«አምላካችን ክርስቶስ ሆይ፣ በሕማምህ የዓለምን ሥቃይ ለውጠሃል። መስቀላችንን እንድንሸከም ኃይልን ስጠን፤ በትንሣኤህም ተስፋን አኑርልን።»

የትኛውም ዓይነት መንፈስና አጋንንት የሚያጠቁን ለዚህ ነው!! ሃይማኖትን ለማጥፋት የመጡ የሴት ተቆርቋሪዎች!! ፓስተር ቸሬ ለፈሚኒስቶች የሰጠው መልስ! #ጸሎት https://youtu.be/yy3ZOTR4D4A

«ዓለም ከአንተ ጋር እንዳወራ ብትተወኝ ብዬ እመኛለሁ እኔም ላንተ ብዬ ብተዋት! ሰው ያንተን ድምጽ ብቻ እንድሰማ ዝም ቢለኝ እኔም አንተን ለማውራት ለሰው ዲዳ ብሆን እሻለሁ! ....ትሰጠኝ ይሆን?
«ዓለም ከአንተ ጋር እንዳወራ ብትተወኝ ብዬ እመኛለሁ እኔም ላንተ ብዬ ብተዋት! ሰው ያንተን ድምጽ ብቻ እንድሰማ ዝም ቢለኝ እኔም አንተን ለማውራት ለሰው ዲዳ ብሆን እሻለሁ! ....ትሰጠኝ ይሆን? ታሰማኝ ይሆን ድምጽህን? ና ብለህ ከዚህች አድካሚ ዓለም ትገላግለኝ ይሆን? አንተ  የሁል ጊዜ ጥያቄዬ ነህ! ለሁሉም ጥያቄዎቼ  መልሴ ነህ !....ምኔ አልሆንክ የኔ ብቸኛ ታማኝ ወዳጄ ክርስቶስ ሆይ ምን አልሆንክልኝ? አቁመኝ አንተ ጋር ስደርስ ልቁም ! ሳልፍህ አትለፈኝ  እጄን ይዘህ እዚህ ጋር ነኝ ቁም በለኝ ....!»

» “God gave you eyes, but you reshape them; He gave you skin, but you stain it; He gave you form, but you alter it. Are you not ungrateful to the Creator?” => "እግዚአብሔር ዓይንን ሰጠህ፣ አንተ ግን ቅርጹን ትለውጣለህ፤ ቆዳ ሰጠህ፣ አንተ ግን ትቀባዋለህ፤ መልክ ሰጠህ፣ አንተ ግን ታዛባዋለህ። ፈጣሪህን የማታመሰግን አይደለህምን?" » “Women who are so concerned with cosmetics and perfume become ministers of Satan's deceit. They lead others to destruction—and will share in their punishment.” => “በመኳኳያና በሽቶ ይህን ያህል የሚጨነቁ ሴቶች የሰይጣን የማታለል አገልጋዮች ይሆናሉ። ሌሎችን ወደ ጥፋት ይመራሉ—በቅጣታቸውም ይካፈላሉ።” ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው!

» St. Cyprian of Carthage: “Those who dye their hair, paint their faces, or enhance their looks deny the handiwork of God.” "ጸጉራቸውን የሚቀቡ፣ ፊታቸውን የሚቀባቡ ወይም መልካቸውን የሚያሳምሩ የእግዚአብሔርን የእጅ ሥራ ይክዳሉ።" » St. Clement of Alexandria: “The use of rouge and eyeshadow is evidence of a soul sick with vanity.” "የቀለምና የኩል አጠቃቀም በከንቱ ውዳሴ የታመመችን ነፍስ ያመለክታል።"

የዕለቱን ወንጌል እናንብብ! ሰኔ 20 +++ እንዲህም አለ። እውነት እላችኋለሁ፥ ነቢይ በገዛ አገሩ ከቶ አይወደድም። ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፥ በኤልያስ ዘመን ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ሰማይ ተዘግቶ ሳለ በምድር ሁሉ ብርቱ ራብ በነበረ ጊዜ፥ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ፤ ኤልያስም በሲዶና አገር ወዳለች ወደ ሰራፕታ ወደ አንዲት መበለት እንጂ ከእነርሱ ወደ አንዲቱ አልተላከም። በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፥ ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልነጻም። በምኵራብም የነበሩ ሁሉ ይህን ሰምተው ቍጣ ሞላባቸው፥ ተነሥተውም ከከተማ ወደ ውጭ አወጡት፥ ይጥሉትም ዘንድ ከተማቸው ተሠርታባት ወደ ነበረች ወደ ተራራው አፋፍ ወሰዱት፤ እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ። ወደ ገሊላ ከተማም ወደ ቅፍርናሆም ወረደ። በሰንበትም ያስተምራቸው ነበር፤ ቃሉ በሥልጣን ነበርና በትምህርቱ ተገረሙ። በምኵራብም የርኵስ ጋኔን መንፈስ ያደረበት ሰው ነበረ፥ በታላቅ ድምፅም ጮኾ። ተው፥ የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደ ሆንህ አውቄሃለሁ፥ አንተ የእግዚአብሔር ቅዱሱ አለ። ኢየሱስም። ዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው። ጋኔኑም በመካከላቸው ጥሎት ሳይጐዳው ከእርሱ ወጣ። ሁሉንም መደነቅ ያዛቸው፥ እርስ በርሳቸውም። ይህ ቃል ምንድር ነው? በሥልጣንና በኃይል ርኵሳን መናፍስትን ያዝዛልና፥ ይወጡማል ብለው ተነጋገሩ። ዝናም በዙሪያው ባለች አገር ወደ ስፍራው ሁሉ ስለ እርሱ ወጣ። በምኵራብም ተነሥቶ ወደ ስምዖን ቤት ገባ። የስምዖንም አማት በብርቱ ንዳድ ታማ ነበር ስለ እርስዋም ለመኑት። (የሉቃስ ወንጌል 4፡24-38)

ዶክተሯ ያጋለጠችው ከባድ ምስጥር!! በማሕጸን ካንሰርና ልጅ በማጣት የምትቸገሩ አዳምጡ!! የመናፍስት ውጊያ የገባት ዶክተር!! መምህር ተስፋዬ አበራ #ጸሎት https://youtu.be/pYAh-yWOacY?si=K8M38pv7U4dJdILt