uz
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Kanalga Telegram’da o‘tish

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Ko'proq ko'rsatish
2 277
Obunachilar
-124 soatlar
+107 kunlar
+3530 kunlar
Postlar arxiv
በሰሞነ ሕማማት የሚጸለይ እና የማይጸለይ ጸሎት የቱ ነው? የአመጋገብ ሥርዓታችንስ እንዴት ይሁን? ሩካቤ ሥጋ ለምን ተከለከለ? #በማለዳ_ንቁ_2024 🚩💥🔥 https://youtu.be/eOze0jUPg-4

ወሰን አጋጅ ቆማጣው የዛር መንፈስ ጣጣ || ከንቱ ጸሎት፣ ስግደትና ምጽዋት || አርትስት ለመሆን መንጨባረር ግድ ነው! ዘመናዊ ስንሆን እምነታችንን ረሳን 🚩🔥 https://youtu.be/NAjW_Gjg638

🚩የፍጹማን ብርሃን የሕያው አምላክ ልጅ ✨ ከማይለይ ጸጋህ አብራልን መተከልን፤ መጽናትንም፤ መታመንንና ጥበብን፤ የማያዘነብል የሐይማኖትን ኃይል የማይለወጥ ተስፋንም የነፍስ ዕውቀትን ለትህትናችን ስ
🚩የፍጹማን ብርሃን የሕያው አምላክ ልጅ ✨ ከማይለይ ጸጋህ አብራልን መተከልን፤ መጽናትንም፤ መታመንንና ጥበብን፤ የማያዘነብል የሐይማኖትን ኃይል የማይለወጥ ተስፋንም የነፍስ ዕውቀትን ለትህትናችን ስጥ፤ አቤቱ እኛ ባሮችህ በሚገባ ዘወትር ንጹሐን እንሆን ዘንድ።    (ቅዳሴ እግዚእ ቍ. 20 , 21) #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ጸራሞና ደራሞ የዱካክና የእንቅልፍ መናፍስቶች የጸሎት ሰዓታት ውጊያዎች የአፍዝና አደንግዝ መንፈሶች || ለምን በጠዋት መጸለይ አስፈለገ? #ንቁ 🚩💥🔥 https://youtu.be/m_4HNLIHNm4

ሩሐንያ የአህዛብ የሰሴኝነትና የአመፃ መንፈስ || የተሐድሶዎች ቅጥፈትና ኑፋቄ || የዮሐንስ ወንጌልና ቅዱስ ታቦት || ሰውና ኃጢአት በማለዳ ንቁ 2024 🚩💥 https://youtu.be/OyRVunTENh4

🚩እንኳን ለፃድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊና ለመናኙ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ የመታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ። 🚩🔥💥 #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@ha
+1
🚩እንኳን ለፃድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊና ለመናኙ ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ የመታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ። 🚩🔥💥 #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«በተስፋ የተመላ ሕይወት ለመኖር» ◈ በእግዚአብሔር ላይ ያለህን እምነት አጠንክር። ተስፋ መቍረጥ ብዙ ቅዱሳን ሊቃውንት እንዳስረዱት በእግዚአብሔር ያለማመን ሕይወት ውጤት ነው። ስለዚህ ተስፋ ወዳለውና እጅግ ደስ ወደሚያሰኝ ሕይወት ለመግባት በእግዚአብሔር ያለህን እምነት አጠንክር። ቅዱስ ጳውሎስ "ያን ጊዜ ክርስቶስን አታውቁትም ነበር፤ ከእስራኤል ሕግ የተለያችሁ ነበራችሁ፤ ከተስፋው ሥርዓትም እንግዶች ነበራችሁ፤ ተስፋም አልነበራችሁም፤ በዚህም ዓለም እግዚአብሔርን አታውቁትም ነበር። አኹን ግን ቀድሞ ርቃችሁ የነበራችሁ እናንተ በኢየሱስ ክርስቶስ ኾናችሁ በክርስቶስ ደም ቀረባችሁ።" ይላል። (ኤፌ 2፥12 ◈ እግዚአብሔርን አለማወቅ ወይም በእርሱ አለማመን ከተስፋ ውጭ ያደርገናል። በእርሱ ስናምን ግን ተስፋችን ይለመልማል። ተስፋና እምነት አብረው ተያይዘው የሚሄዱ ነገሮች ናቸው። ተስፋችን ከፍ እያለ እንዲሄድ እምነታችንን ማጠንከር አለብን። ቅዱስ ጳውሎስ፦ "እምነትስ ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የምታረጋግጥ፥ የማናየውንም ነገር የምታስረዳ ናት"ይላል። (ዕብ 11፥1) ተስፋችን የሚረዳን በእምነት ውስጥ ስንኾን ነው። በእግዚአብሔር ያለን እምነት እየጠፋ ከሄደ ተስፋ ወደ መቍረጥ ክፉ ጒድጓድ ውስጥ ገብተን እንሰጥማለን። ◈ አባ መቃሪዮስ በእግዚአብሔር ስለ ማመን ሲናገር፦ "አንድ ቀን አንድ እኁ አባ መቃርዮስን እንዲህ ሲል ጠየቀው፦ "ራስን በእግዚአብሔር ፊት መጣል ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ ንገረኝ" አለው። አባ መቃርዮስም እንዲህ አለው፦ "ጌታችን ለሕዝቡ ያለ ምሳሌ እንዳልተናገራቸው ተጽፏል። በእርሱ ጥበቃና ባለቤትነት ሥር ያለው እንስሳ በድካም ኾኖ በፊቱ የጭንቀት ትንፋሽ እስኪተነፍስ ድረስ ክፉ የኾነ አውሬ በኃይል እላዩ ላይ ዘልሎ ቢያርፍበትና በላዩ ላይ ቢቆምበት በዚህ ጊዜ የእንስሳው የመዳን ተስፋ በባለቤቱ ላይ የተመሠረተ ነው። ስለዚህም እንስሳው ለጌታው ለማሰማት በኃይል ይጮሃል። ባለቤቱ ከሰማ ያስጥለውና ያድነው ዘንድ ፈጥኖ ወደ እርሱ ይሄዳል፣ በአውሬው ከመበላትም ያድነዋል። የዚህ እንስሳ ጌታው እንዲህ የሚያዝንለትና ከአውሬው እስኪያድነው ድረስ የሚፋጠን ከኾነ በአርአያውና በአምሳሉ ለፈጠረን ለክርስቶስ መንጋዎች ለእኛማ ጥበቃው ምን ያህል ይኾን? ◈ እምነታችንን በእርሱ ላይ ካደረግን ለጠላታችን በእኛ ላይ ክፉ እንዲያደርግ አይፈቅድለትም ከዲያብሎስ እጅ ያድነን ዘንድ መልአኩን ወደ እኛ ይልካል እንጂ። ስለዚህ ልጆቼ ሆይ ራስን በእግዚአብሔር ፊት መጣል ማለት ሰው በራሱ ኃይልና ጥንካሬ ላይ ብቻ መተማመኑን ትቶ ኦምነቱን በእግዚአብሔር ዕርዳታ ላይ ሲያደርግ ነው፤ የሚያድነን እርሱ ነውና" ይላል። (ዘውዴ ገ/እግዚአብሔር (B.Th, PGD፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምርቅት)፣ ታላቁ ቅዱስ መቃርዮስ፣ 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 143-144)። ስለዚህ በእግዚአብሔር ላይ ያለን ፍጹም እምነት ተስፋችንን እንዲያብብ ያደርግልና፥ ጭንቀታችንንም ከሕይወታችን ያስወግድልናል። ◈ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ፦ "ተስፈኛ አመለካከት ከአንተ አይራቅ! ጠንካራ እምነት ያዝ! እግዚአብሔር ባሕሩን እንደሚከፍለው በዚያም ውስጥ መንገድ እንደሚያዘጋጅልህ ተማመን! "ጻድቅ በእምነት ይኖራል" እንደ ተባለ በድኅነትም ትወጣለህ (ዕብ 10፥38)። የፍርሓትና የጥርጣሬ አመለካከት ግን ቀቢጸ ተስፋን ጨለምተኛነትን ያመጣል። ተስፈኛ አመለካከትና እምነት ግን በሃያ አራተኛውም ሰዓት ቢኾን እግዚአብሔር አንዳች ነገር እንደሚያደርግ ያስተማምናል። በክስተቶች ውስጥ ኹሉ በእግዚአብሔር የረድኤት እጅ ካላመንን በእርግጠኛነት ደስተኞች ልንኾን አንችልም። የእግዚአብሔርን ቃል አስታውስ "በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አልፈራም፤ አንተ ከእኔ ጋር ነህና" (መዝ 23)። ... የተስፈኛነት አመለካከት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዙ ኃጥአን የንስሓ ሕይወት ውስጥ ታይቷል። በቅዱስ አግናጥዮስ፣ በቅዱስ ሙሴ ጸሊም፣ በቅድስት ማርያም ግብጻዊት፣ በቅድስት ፔላጊያ፣ በቅድስት ሣራ ... ወዘተ ሕይወት ውስጥ ታይቷል። ሕይወታቸው ተስፋ የሚያስቈርጥ ነበር፤ በእግዚአብሔር ሥራ ውስጥ ግን ተስፋ ቢስነት የለም። እርሱ ከድንጋዮች ልጆችን ሊያስነሣ ይችላል (ማቴ 3፥9)።" ይላሉ። (ማለደ ዋስይኹን (ተርጓሚ)፣ የኤልኬሬዛ በረከቶች ቍ 2፣ 2008 ዓ.ም፣ ገጽ 129-132)። ◈ ሕይወታችን በእምነት ሲመላ ተስፋችን ከፍ ስለሚል እጅግ አስጨናቂ በሚባል ኹኔታ ውስጥ እንኳን ብንኾን ተስፋ አንቈርጥም። እግዚአብሔርን ማመን ያለብን እኛ በምንፈልገው መንገድ ይሠራል ብለን ብቻ ሊኾን አይገባውም። እኛ ተስፋ የለንም ብለን በምናስበው ኹኔታ ውስጥ ብንኾን እንኳን፥ እግዚአብሔር እንደሚረዳንና ከዚያ ውስብስብ ገጠመኝ ሊያድነን እንደሚችል በእምነት እርሱን ተስፋ ልናደርግ ይገባል። ◈ የኦቲናው ባርሳቡፊየስ "ተስፋ ልትቈርጥ አይገባም። ተስፋ የሚቈርጡ በእግዚአብሔር የማያምኑ ናቸው። በእርግጥ ለእነዚህ ኀዘን ሸክም ነው። ምክንያቱም ከምድራዊ ደስታ በቀር ምንም ሌላ ነገር የላቸውምና። ነገር ግን አማኞች ፈጽሞ ተስፋ አይቈርጡም፤ በኀዘን የልጅነትን መብት ያገኛሉ፥ ያለ ኀዘንም ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አይቻልም።" ይላል። (St. Barsanuphius of Optina, quoted from Living Without Hypocrisy: Spiritual Counsels of the Holy Elders of Optina)። ስለዚህ እምነታችን እየጠነከረ ሲሄድ ተስፋችን እያደገ የሚሄድ ስለ ኾነ፥ በተስፋ የተመላ ሕይወት ለመኖር እንችላለን። ተስፋ የሕይወት ማጣፈጫ መኾኑን ልብ ልንል ይገባናል። በመኾኑም በተስፋ ላይ የተመሠረተን የክርስትናን ሕይወት በአግባቡ ለመኖር በእግዚአብሔር ማመንና እርሱን ተስፋ ማድረግ ይገባናል። ተስፋ እንድንናጣ የሚያደርጉንን መንገዶች በሙሉ ልባችን ኹሌም እናውግዛቸው፥ እነዚያ መንገዶች በሙሉ ከሰይጣን ናቸውና። የክርስትና አንዱ መልክ በማንኛውም ኹኔታ ውስጥ ኾኖ ተስፋ ሳይቈርጡ መጽናት ነውና። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ስትቀራረቡ የሚያጨቃጭቅ፣ ስትራራቁ የሚያስናፍቅ ዓይነጥላና መተት || የፍቅር መቀስ የሆነ ክፉ መንፈስ || የባለትዳሮችና የእጮኛሞች ዓይነጥላዊ ፈተና 🚩💥🔥 https://youtu.be/MK7q0_Ma_2A

ትዳራችንን፣ ሰላማችንን እንዴት እንጠብቅ? || መቁጠሪያና ርኩሳን መናፍስቶች || ጸሎትን ለምን እናቋርጣለን? ጸሎት ምንድነው? || የክርስቶስ መዘግየት 🚩💥🔥 https://youtu.be/bdWEE1jS0Iw

🚩የተደረገልንን እናስብ! ◈ በጥንተ ፍጥረት እግዚአብሔር በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረን፤ ኋላም በሐዲስ ተፈጥሮ በእግዚአብሔር አብ የባሕርይ ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ የተፈጠርን፤ በተቀደሰች ጥምቀት አማካኝነት ክርስቶስን የለበስን፤ በቅብዓ ሜሮን አማካኝነት በመንፈስ ቅዱስ ማኅተም የታተምን፤ በቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ የክርስቶስ አካል የኾንን ታላቅ ጸጋና ክብር የተሰጠን ሰዎች መኾናችንን እናስተውል። አምላክ ሰው ኾኖ ያን ኹሉ መከራና ሕማም የተቀበለው በኃጢአታችን ምክንያት ጠፍተን የነበርነውን እኛን ወደ ቀደመ ቦታችን ሊመልሰን ነው። እንግዲህ ይህን ያህል ክብር የሰጠንን አምላክ ተስፋ ቈርጠንበት ራሳችንን ስናጠፋ ምን ይሰማው ይኾን ብለን ለአንድ አፍታ ቆም ብለን እናስብ። ◈ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ክርስቶስ ለኛ ያደረገልንን እንድናስብ በአጽንዖት ይመክረናል። እንዲህ ይላል፦ "... ክብራችንን እንገንዘብ፣ እንመስለው ዘንድ ያለንን የፍጻሜያችንን አርአያ እናክብር፣ የምሥጢሩን ኃይል እንወቅ፣ ክርስቶስ ስለ ምን እንደ ሞተ እናስተውል። ክርስቶስን እንምሰል፣ ክርስቶስ እኛን መስሏልና። ስለ እርሱ ስንል አማልክት ዘበጸጋ እንኹን፤ እርሱ ስለ እኛ ሰው ኾኗልና። ለኛ ከኹሉ በላይ ታላቅና የተሻለ የኾነውን ይሰጠን ዘንድ እርሱ ለአምላክነቱ የባሕርይ ክብር ተገቢ ያልኾነውን ዝቅተኛ ነገር ገንዘቡ አደረገ። በእርሱ ድህነት እኛ ባለጠጎች እንኾን ዘንድ ድሀ ኾነ፤ እኛ ነጻነታችንን መልሰን እናገኝ ዘንድ እርሱ የባሪያን መልክ ያዘ፤ እኛ ከፍ ከፍ እንል ዘንድ እርሱ ወደ ታች ወርዶ መጣ፤ እኛ ድል እናደርግ ዘንድ እርሱ ተፈተነ፤ እኛን ያከብረን ዘንድ እርሱ ተዋረደ፤ እኛን ያድን ዘንድ እርሱ ሞተ፤ በኃጢአት ምክንያት የመጨረሻ ውርደት ተዋርደን፣ ኃጢአት በሚያመጣው ተዋርዶ ዘቅጠን የነበርነውን እኛን ወደ እርሱ ይወስደንና ያነሣን ዘንድ እርሱ ወደ ላይ ወጣ (ዐረገ)" (በእንተ ትንሣኤ ወምክንያተ ጎንድዮቱ። ትምህርት 1፣ቍ 4፤ ያረጋል አበጋዝ (ዲ/ን)፣ መድሎተ ጽድቅ ቅጽ አንድ፣ 2007 ዓ.ም፣ ገጽ 115-116)። ◈ እንግዲህ በዚህ ኹሉ መንገድ በከበረ ደሙ ፈሳሽነት ላዳነን፥ እንዲሁ ለወደደን ለእርሱ መልሳችን ራስን በማጥፋት እርሱን መቃረን ሊኾን ይገባዋልን? አፍቃሪያችን ክርስቶስን ይህን ክፉ ግብር በመፈጸም ልናሳዝነውስ ማሰባችን ተገቢ ነውን? ወዳጄ ሆይ! ክርስቶስ በሕማሙ የከፈለልህን ዋጋ አስበህ ራስን የማጥፋት ክፉ ሐሳብን ከራስህ አስወግድ። ንጹሕ የኾነ እርሱ ያን ያህል ክብርን ሰጥቶን አክብሮን ሳለ እንዴት ያን የእርሱን መሥዋዕትነት ትተን ወደ ሌላ ሐሳብ ልናዘነብል እንችላለን! ◈ እስከሞት ድረስ መከራን ተቀብሎ ሞታችንን ለማስወገድ ስለ እኛ ብሎ የመስቀል ሞትን የተቀበለልንን አምላክ የፍቅሩን ነገር ቆም ብለን እናስበው። እርሱ ያን ያህል ያፈቀረን በፍቅር እንድንኖር ነው። ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊው "የክርስቶስ ፍቅር የሌለው ማንም ቢኾን የክርስቶስ ጠላት ነው። በጨለማ ይሄዳል፤ ወደማንኛውም ኃጢአት በቀላሉ ይጓዛል።" ይላል። (St. Ephraim the Syrian, Homily on Virtues and Vices)። ራስን የማጥፋት ሐሳብ የመጣብን ፍቅረ ክርስቶስን ከሕይወታችን በማስወጣታችን ምክንያት መኾኑን እናስተውል። ◈ እርሱ አምላካችን እየጠላነው እንኳን ይወደናል። ለዚህም ነው በጥላቻቸው ተቃጥለው የሚሰቅሉትን እንኳን "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" የሚለውን የፍቅር ጸሎት ያቀረበልን። ይህ እርሱን አርአያ እናደርግ ዘንድ ሊያስተምረን የተናገረው ንግግር ነው። ስለዚህ ይህን ያህል ለወደደን ለእርሱ ፍቅር ሊኖረን አይገባምን? እርሱ አምላክ ሲኾን ከእኛ የሚያገኘው ምንም ነገር ሳይኖር እስከ ሞት ድረስ ከወደደን ለእርሱን ስንል እኛ መልካም መኾን እንዳለብን አይሰማንምን? በእውነት ለሚያፈቅረን ለእርሱ ጠላትቹ ልንኾን ይገባልን? ራስን ማጥፋት ከክርስቶስን መጥላትና በእርሱ ላይ ጠላት መኾን ከኾነ፤ ይህ እንደ ምን ያለ ጉዳት ነው። በመኾኑም አፍቃሪያችንን እንውደደው! ለእርሱ ካለንም ፍቅር የተነሣ ክፉ ነገር በራሳችን ላይ አናድርግ። #ከፈውሰ_ሕይወት_መጽሐፌ_የተወሰደ! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🚩የእግዚአብሔር ቸርነት ◈ (ንስሐ እስከ ገቡ ድረስ) የእግዚአብሔር ቸርነት የማይፍቀው ምንም ዓይነት ኃጢአት የለም፡፡ አንድ ሰው የፈለገ ያኽል ዝሙት ወይም ሴሰኝነት ወይም ሌላ ኃጢአትን ቢሠራ፥ ይ
🚩የእግዚአብሔር ቸርነት ◈ (ንስሐ እስከ ገቡ ድረስ) የእግዚአብሔር ቸርነት የማይፍቀው ምንም ዓይነት ኃጢአት የለም፡፡ አንድ ሰው የፈለገ ያኽል ዝሙት ወይም ሴሰኝነት ወይም ሌላ ኃጢአትን ቢሠራ፥ ይህ ከአእምሮ ፍጹም የሚያልፍና ሊናገሩት የማይቻለው የእግዚአብሔር ጸጋውና ፍቅሩ ኃጢአተኛውን ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ እጅግ ብሩህ ያደርጓል … በልብ መታሰቡ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት መዘገቡ፣ በቃልም መነገሩ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የሰው ዘርን በሙሉ ወደ እርሱ ሲጠራ እንዲህ ብሏል። “እናንተ ሸክም የከበደባችሁ ኹሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ”…የሚጠራው ወደርየለሽ ከኾነ ቸርነቱ የተነሣ ነው! ይህ ቸርነቱም ማንም ሊደርስበት የማይችልና ከሕሊናት ኹሉ እጅግ የራቀ ነው። ◈ የሚጠራው ማንን እንደ ኾነ ደግሞ ተመልከቱ ትእዛዙን በማፍረስ ዕድሜያቸውን የጨረሱ ኹሉ፣ ኃጢአት ሸክም የኾነባቸው ኹሉ፣ በቀቢጸ ተስፋ ተይዘው ራሳቸውን ቀና ማድረግ ያቃታቸው ኹሉ፣ በሐፍረት ካባ የተከናነቡ ኹሉና ኃጢአታቸው በዝቶ እግዚአብሔርን ለማናገር እንኳን ዓቅምን ያጡ ኹሉ የሚጠራቸውስ ለምንድን ነው? “እስከ አሁን ድረስ ምን ስትሠሩ ነበር” ለማለት ነውን? ወይስ ሊፈርድባቸው ነውን? በጭራሽ! ታዲያ ለምንድን ነው? ከስቃያቸው ይገላግላቸው ዘንድ ከባድ የኾነ ሸክማቸውን ያስወግድላቸው ዘንድ! ከኃጢአት በላይ የኾነ ከባድ ሸክምስ ምን ሸክም ሊኖር ይችላል? … በመኾኑም ጌታችን ኹላችንንም እንዲህ ሲል ይጠራናል። “እናንተ ኃጢአት ሸክም የኾነባችሁ እናንተ ኃጢአት ቀንበር ኾኖባችሁ ያቀረቀራችሁ ሆይ! ወደ እኔ ኑ፤ ኑና ሥርየተ ኃጢአትን እሰጣችኋለሁ፡፡” አባ ገብረ ኪዳን #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239

ዓይነጥላና ዛር በህክምና ላይ የሚያሠሩት ከባዱ ስህተት || የላብራቶሪ ውጤት መዛባት || የሌለብንን በሽታ መናገር እና ክፉኛ ማስደንገጥ #ethiopia 🙏😭🚩 https://youtu.be/XY3-rNsQ7eg

🚩የዝሙት አጋንንትና የዝሙት ፈተና በአረጋዊ መንፈሳዊ ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ! ◈ ተወዳጆች ሆይ በመጻሕፍተ መነኰሳት በአረጋዊ መንፈሳዊ ላይ ስለ ዝሙት አጋንንት ክፉኛ ፈተና ተጽፏል። ለአንባቢ እንዲመች ይዘቱን ሳይለቅ አቀራረቡን ብቻ ጥቂት በመቀየር፣ ትንሽ በመጨመር አቅርቤዋለሁ። ከአጋንንት ሁሉ ይልቅ የዚህ የሰይጣን ዝሙት ፈተናው ቡዙ ነው። የዝሙት አጋንንት ሕዋሳታችንን የሚያዝልበት ጊዜ አለ። ልቦናችንን የሚለውጥበት ጊዜ አለ። ሕሊናችንን የሚሰውርበት ጊዜ አለ። ሰውነታችንን ማዘዝ የማንችልበት ጊዜ አለ። ከጸጋ ስጦታ ለይቶ ኅሊናችንን ይለውጣል። ተኝተን ሳለን በዝሙት የሚዋጋን ጊዜ አለ። ◈ የዝሙት አጋንንትን አመጣጡን እንወቅበት። በምን እናውቃለን? ካልን የዝሙት እሳቱ በፊታችን ላይ እንደ እሳት ብልጭ ይልብናል። የዝሙት አጋንንት ሲመጣ ድንግጥ ድንግጥ እንላለን። የዝሙት አጋንንት ሲፈትነን ጸሎታችን፣ ስግደታችን ይከብደናል። እንዳንጸልይ እንዳንሰግድ ከባድ አድርጎ ያሳየናል። የዝሙት አጋንንት ሲፈትነን ጸሎታችንን የአምልኮት ስግደታችንን ትተን ወይም አቋርጠን እንተኛለን። ቆመን ተኝተን ሕዋሳታችንን እንዳብሳለን። እግራችንን እናፋትላለን። ነገር ግን ታግሰን ብንጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ ይረዳናል። ብንጸልይ ብንሰግድ ብንተጋ ፈተናው ይቀልልናል ይርቅልናል። ◈ እነዚህ የዝሙት አጋንንት የፈተና ምልክቶች እያሉብን ያለ ጸሎትና ያለ ስግደት መተኛት የለብንም። ያለ ጸሎት ያለ ስግደት ብንተኛ ጠባቂ መልአክ ይርቀናል የዝሙት አጋንንት ቀርቦ ይፈትነናል። የዝሙት አጋንንት በዓይን ይገባል። በዓይን ሲገባ ወደ ሰውነታችን ገብቶ በመቆጣጠር ሕዋሳችንን በእጅ እንድናሽ ያደርገናል። /ይህ አባባል ግለ ወሲብ እንድንፈጽም ያደርገናል ለማለት ነው/ የዝሙት አጋንንት እንዲህ ሲፈትነን በክርስቶስ ኃይል እናማትብበት። ◈ ወደ ተግባረ ዝሙት እንዳይከተን በርትተን መጸለይ መስገድ አለብን። ይህን ካለደረግን የዝሙት አጋንንት ወደ አባለ ዘር ገብቶ ያለ ርህራሄ በዝሙት ፈተና ያስጨንቀናል በዝሙት ይጥለናል። የዝሙት አጋንንት ሰዎችን እንደ ጊንጥ ይነድፋሉ። ቆመንም ቢሆን፣ ተቀምጠንም ቢሆን፣ ሥራም በያዝንበት ጊዜም ቢሆን የዝሙት ስሜት ቢያነሳሳብን በሕሊናችን እንጸልይ እንገስጸው። ◈ ከወትሮ ይልቅ አብዝተን ስንበላ ስንጠጣ የዝሙት ፆር ይጸናብናል። አብዝቶ መብላት መጠጣት እና እላፊ መተኛት የዝሙት አጋንንትን ያቀርበዋል። አብዝተን ስንበላ ስንጠጣ ያኔ የዝሙት አጋንንት ሊዋጋን እንደቀረበ እንወቅ። ሰውነታችንን ለዝሙት ካነሳሳ ያኔ የዝሙት አጋንንት እንደሰለጠነብን እንወቅ። ◈ ወዳጆቼ ብዙዎቻችንን ከንስሐ መንገድ ያራቀን፣ ክብራችንን ቅድስናችንን ያስጣለን፣ ከዓለማዊ እስከ መንፈሳዊ፣ ከምዕመን እስከ አባቶች እናቶች፣ በአምልኮት ሕይወት ከጸኑት፣ በቅዱስ ቁርባን እስከ ተወሰኑት ወዘተ የዝሙት አጋንንት እየፈተነን በቀላሉ እየጣለን ነው። በዚህም ቅድስና ከሕይወታችን ርቋል። ◈ ከዝሙት አጋንንት የሸሸ እግዚአብሔርን ይከተላል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ጸጋና በረከቱን ይዞ ይኖራል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በማዕረግ ያገባል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ንጽሕናውን ቅድስናውን ይጠብቃል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ከርኩሰት ይሸሻል። ከዝሙት አጋንንት ሸሽቶ፣ ወደ እግዚአብሔር ተጠግቶ የሚኖር ሰማያዊ ሽልማት ያገኛል። ከዝሙት አጋንንት እና ከዝሙት እንሽሽ። ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ "ከዝሙት ሽሹ" ያለን። /1ኛ ቆሮ 6፥ 18/ ◈ እጅግ በጣም የገረመኝ አረጋዊ መንፈሳዊ "የሰይጣናት ተንኮላቸውን እናገር ዘንድ ከምን ተችሎኝ ላልፈጽመው" በማለት ገና ያላወቅናቸው ነገር ግን በወጥመዱ የተያዝንባቸው፣ በሴራው የወደቅንባቸው ተንኮሎቹ እንዳሉ ይነግረናል። እኛ ግን ስለ ጥንተ ጠላታችን ከገነት ስላስወጣን፣ ከእግዚአብሔር ስለለየን፣ ከዘላለማዊ መንግሥቱ እንድንባረር ስላደረገን ሰይጣን ተንኮሉ ሴራው ውጊያው ሲነገረን ስለ ሰይጣን የተሰበክን መስሎን እንጃጃላለን። ስለ ጠላታችሁ ንቁ እወቁ ሲባሉ ሰይጣን ለምን ተነካ የሚሉ አሉ። ◈ ቅዱስ ጴጥሮስ ግን "ባላጋራችሁ ዲያቢሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራልና" በማለት ውጊያው ቀላል እንዳልሆነና የማንጸልይ፣ የማንሰግድ፣ ቅዱስ ቁርባን የማንቀበል ከሆነ እንደ አንበሳ፣ በሕይወታችን እያገሳ ስንት ነገራችንን እየነሳ ይኖራል። /1ኛ ጴጥ 5፥8/ ወዳጆቼ ዲያቢሎስ "ፈልጎ እንደሚያገሳ" መባሉን ልብ በሉ። እኛ ባንፈልገውም እሱ ፈልጎ ይዋጋናል። የመንፈሳዊ የጦር ዕቃዎችን ማለትም ጸሎት፣ ስግደት ወዘተ የማያነሳ ሰው ላይ እንደ አንበሳ መሆኑን አንርሳ። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

#እንዲህ_እያላችሁ_አብዝታችሁ_ስገዱ! እግዚአብሔር አብ ምስጉን ነው እግዚአብሔር ወልድ ምስጉን ነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ምስጉን ነው መንፈስ ቅዱስ ሆይ ወደኔ ና 3X ጵራቅሊጦስ ሆይ ወደኔ ና
#እንዲህ_እያላችሁ_አብዝታችሁ_ስገዱ! እግዚአብሔር አብ ምስጉን ነው እግዚአብሔር ወልድ ምስጉን ነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ምስጉን ነው መንፈስ ቅዱስ ሆይ ወደኔ ና 3X ጵራቅሊጦስ ሆይ ወደኔ ና 3X መለኮተ እሳት ሆይ ወደኔ ና 3X ለንጽሕና መንፈስ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለቅድስና መንፈስ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለእውነት መንፈስ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለስጦታ ምንጭ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለእውቀት ፋና ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለቸርነት ብርሃን ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለእሳት ጎርፍ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለመለኮታዊ እርግብ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለወርቅ ልብስ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለንስረ ትንቢት ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለሃይማኖት መሪ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለእምነት መምህር ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለቅዱሳን ጌጥ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለጻድቃን አክሊል ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለሰማዕታት መመኪያ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ለሕይወት መብረቅ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ነብያትን ላናገረ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ ሐዋሪያትን ለመራ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለው ድንግል ማርያምን ለከለለ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ መልአክትን ላሰለጠነ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ መናፍስትን ለሚያሳድድ ጵራቅሊጦስ እሰግዳለሁ መንፈስ ቅዱስ ኃይልን አብዛልኝ መንፈስ ቅዱስ ጉልበትን ስጠኝ መንፈስ ቅዱስ ጽናትን አካፍለኝ መንፈስ ቅዱስ ብርታትን ላክልኝ መንፈስ ቅዱስ ጸጋን ስደድልኝ መንፈስ ቅዱስ በረከትን አካፍለኝ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🚩ቻይ እና ትዕግስተኛ የሆነ ሰው ይጸልያል ስለሚሰጠውም የእግዚአብሔር መልስ አይጨነቅም፤ እግዚአብሔር ጸሎቱን እንደሚሰማው እርግጠኛ ነው፤ ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ጥበብና ፈቃድ እንደሚሆን በተገቢው ጊዜና መንገድ መልስ እንደሚሰጠው በማመን ለእግዚአብሔር ፍቅር ይተዋል፤ አንዳንድ ሰዎች ይህ መሰል ትዕግሥት የላቸውም፤ እግዚአብሔርን መውቀስ እና ከእርሱ ስሕተት መፈለግ እንጂ መጠባበቅ አይችሉም፤ እርሱን ይወነጅሉታል እርሱ ግን እጅግ ይታገሳቸዋል ወቀሳቸውንም ይሸከማል፤ እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔር ለእነርሱ እንደሚሰራ ማመን አለባቸው። አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

🚩ከጭንቀት ለመውጣት ምን ላድርግ? ◈ ኹል ጊዜም ቢኾን አእምሮን በመልካም ሐሳቦች መሙላት ከጭንቀት ያላቅቀናል። አረጋዊው ታዴዎስ ሐሳባችን ሕይወታችንን ይወስናል በሚለው ታዋቂ ሥራው “ሕይወታችን በምናስበው የሐሳብ ዓይነት ላይ የተመሠረተ ነው። ሐሳባችን ሰላማዊ፣ የተረጋጋ፣ ቅንና መልካም ከኾነ፥ ሕይወታችንም ይህንኑ ይመስላል።" ይላል። (Elder Thaddeus’s famous work, “Our Thoughts Determine our Lives,)። ሐሳባችን ከኑሯችን ጋር ግንኙነት የሚኖረው ከኾነ፥ ሐሳባችንን ማጥራትና መልካም እንዲኾን ማድረግ ይጠበቅብናል። ሐሳባችን መልካም የሚኾነው ደግሞ መልካም በኾነው በእግዚአብሔር ቃል ላይ ሲደገፍ ነው። ◈ የእግዚአብሔርን ሕግ ማሰብ የሕይወታቸው መርሕ የኾነላቸው ሰዎች ልበ አምላክ ዳዊት "ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋንም በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይኾናል፤ የሚሠራውም ኹሉ ይከናወንለታል።" ያለውን ይመስላል። መዝ 1፥1-3። እንዲህ ዓይነት ሰው ኹል ጊዜም በመልካም ሐሳቦች አብቦ፥ በሕገ እግዚአብሔር አጽር ቅጽር ውስጥ ኾኖ ነው የሚገኘው። ሕሊናውን የእግዚአብሔርን ቃል በማሳሰብ ያኖረዋል። ወደ ጭንቀት ሊወስዱን የሚፈልጉ ሐሳቦች እየመጡ ሲረብሹን እየደጋገምን የእግዚአብሔርን ቃል እናስታውስ፤ በእግዚአብሔር ቃል ኃይልም የጭንቀትን ነገር ከእኛ እናርቀው። ቅዱስ ጳውሎስ ለዚህም ነው "አኹንም ወንድሞቻችን ሆይ፥ እውነትን ኹሉ፥ ቅንነትንም ኹሉ፥ ጽድቅንም ኹሉ፥ ንጽሕናንም ኹሉ፥ ፍቅርንና ስምምነትንም ኹሉ፥ በጎነትም ቢኾን፥ ምስጋናም ቢኾን፥ እነዚህን ኹሉ አስቡ።" በማለት ሕሊናችን በምን መመላት እንዳለበት የሚያሳስበን። ፊል 4፥8። በመኾኑም አእምሯችን በመልካም ሐሳብ እንዲሞላ ማድረግ ይገባናል። አእምሯችን በመልካም ሐሳብ ሲሞላ ጭንቀት በእኛ ዘንድ መቆየት አይችልም። ◈ በጸሎት ጭንቀታችንን ለእግዚአብሔር ማቅረብ። በቅብጣውያን ስብከት ውስጥ "... ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "በነገር ኹሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋናም ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ" አለን። እንግዲህ የቅዱስ ጳውሎስ የጭንቀት መፈወሻ ይህ ነው። መፈወሻውን በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ውሰዱት። አንድ መንፈሳዊ ጸሐፊ ስለዚህ ጥቅስ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፦ "የፍላጎቶቻችሁን ሙሉ ዝርዝር በእውነትና በምስጋና ጸሎት ለእግዚአብሔር ንገሩት" ... "በነገር ኹሉ ... በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ" ይሄ ምን ማለት ነው? "በነገር ኹሉ" ይህ ቃል የሚገልጠው እግዚአብሔር ሊያደርግ የማይችለው ምንም ዓይነት እጅግ ትንሽ ነገር እንኳ የለም ማለት ነው። ለእርሱ ውድ እና አንዳችም እጅግ የማይጠቅም የሚባል ነገር የለም። ◈ ስለዚህ እኛ ለእርሱ እንዲታወቁ አድርገን የምናቀርባቸውን አነስተኛ ጥያቄዎች በማስታወቃችን ፈጽሞ እርሱን እንዳስቀየምነው አድርገን ማሰብ የለብንም። ... ስለዚህ የእኛን ጭንቀቶች የሚያስወጣው ማስወጫ ልመናችንን በየዕለቱ ለእግዚአብሔር ማስታወቃችን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ አለ፦ "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበዳችሁ ኹሉ ወደ እኔ ኑ፤ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ማቴ 11፥28። እንግዲህ ዛሬ ምንም ዕረፍት የሌለን ከኾን ጭንቀቶቻችንን ለእግዚአብሔር አላሳወቅንም ማለት ነው። አሊያም ብቻችንን ልንሸከማቸው እየሞከርን ነው ወይም ወደ ሌላ ቦታ ወስደናቸዋል ወይም ደግሞ አንቀውናል ማለት ነው።" ተብሎ ተብራርቷል። (አያሌው ዘኢየሱስ (ተርጓሚ)፣ ምርጥ የቅብጣውያን መንፈሳዊ ስብከቶች፣ 2007 ዓ.ም፣ ገጽ 38-39)። እንግዲህ ይህ የሚያስረዳን ከጭንቀት ለመላቀቅ በጸሎት በኩል ወደ ጭንቀት የመሩንን ሐሳቦች ለእግዚአብሔር ማሳወቅ እንዳለብን ነው። ◈ ጭንቀቶቻችንን ለእግዚአብሔር ገልጠን በጸሎት በኩል ማቅረብ የሚገባን፥ እግዚአብሔር ስለማያውቃቸው እርሱን ለማሳወቅ ብለን አይደለም። ይልቅስ በእርሱ አምነን እንድንጠይቀው፥ እርሱ የሚያስፈልገንን የሚሰጠን መኾኑን ልብ እንድንል ነው። በሌላ በኩል በፈቃዳችን የሚረዳንና የሚጠብቀን መኾኑንም እንድናስተውል ነው። እርሱን አልፈልግም ማለት ሕይወትን መራራ ያደርጋል። በሕይወታችን በራሳችን ልንወጣቸው የማንችላቸው ብዙ ነገሮች ስላሉ፥ እርሱ ደግሞ ኹሉን ማድረግ የሚችል ስለ ኾነ፥ በልጅነት መንፈስ ኾነን እንዲሰጠን ስንጠይቀው ደስ ይለዋል። ስለዚህ ሳንታክት በተደጋጋሚ እግዚአብሔርን እርዳን እያልን ከልቅሶ ጋር በጸሎት መጠየቅ አለብን። ◈ ቅዱስ ኤፍሬም "ጌታ ሆይ ወዳንተ እማፀናለሁ፤ መልካም እረኛ የኾንክ አቤቱ በርህን አንኳኳለሁ። ጌታ ሆይ ቃል ኪዳንህ አትተው። ስለ ቃል ኪዳንህ ስል ወዳንተ እጮኻለሁ። አንተ "አንኳኩ ይከፈትላችኋል፤ ለምኑ ይሰጣችሁማል" ማቴ 7፥7 ብለሃልና። ጌታ ሆይ በርህ ፍጹም የተዘጋ፣ የተቆለፈውም አይደለም። ኃጢአተኞች መጥተው ቢያንኳኩ ትከፍትላቸዋለህና። አቤቱ በርህ ለቅዱሳንም ለሰነፎችም ኹል ጊዜ የተከፈተ ነው። ... አቤቱ በቶሎ ወደ እኔ ተመልከት። በቃል ኪዳንህም መሠረት ጌታ ሆይ መልካሙን ኹሉ ስጠኝ። እነሆ ወዳንተ እጮኻለሁና ወደ መልካም መንገድ ምራኝ። ◈ ጌታ ሆይ እንደ ቃልህም በርህን ክፈትልኝ። ... አቤቱ በኹሉም አቅጣጫ ችግር፣ መተላለፍ እና ኃጢአት ከበውኛል። አንተን የመሰለ ባለ መድኃኒት የለምና ካንተ በቀር በሽታዬን ለማን እናገራለሁ? ጌታ ሆይ ወደዚህ ዓለም መምጣትህ ለቅዱሳን ሳይኾን ለኃጢአተኞች ነው። ኃጢአተኛው በንስሓ ወዳንተ ይመለስ ዘንድ ነው።" ይላል። (መዝገቡ ከፍያለው (ትርጒም)፣ በእንተ ንስሓ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ወአፍርሐት፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 16-22)። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube