HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
Kanalga Telegram’da o‘tish
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
Ko'proq ko'rsatish2 277
Obunachilar
-124 soatlar
+107 kunlar
+3530 kunlar
Postlar arxiv
🙏 የጻድቁ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ረድኤት በረከቱ በሁላችን ላይ ይደር። እንኳን አደረሳችሁ ውድ ቤተሰቦቼ 💥❤🔥
አጋንንት በጣም ረቂቅና ብልጥ ነው መክልታችን ምንድነው? የብዙ ወጣቶች ችግር ራስን ማጥፋት መልካምነት የጠፋበት ዘመን || የልጆች አስተዳደግ 💥🚩
https://youtu.be/q-Y3uwxLL3U
🚩 መርሳት
◈ በአንድ ወቅት የግብጹ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ (በጣም ነው የምወዳቸው) እያስተማሩ ባሉበት ወቅት ብዙ ጥያቄዎች በጹሑፍ ይደርሳቸው ነበር፤ ታዲያ ከነዛ ጹሑፎች መካከል አንዱ እንዲህ ይላል "... አባቴ እኔ ታላቅ የመርሳት ችግር አለብኝ ያደረኩትን የሰማሁትን ነገሮች በሙሉ እረሳቸዋለው እና አባቴ ምን እንደማደርግ ይምከሩኝ" ነበር የሚለው። ብጹእነታቸውም "ልጄ መምከሩንስ እመክርሃለሁ ምን ማድርግ እንዳለብህ እነግርሃለሁ ግን እንዳትረሳው እፈራለሁ" አሉት ይባላል።
◈ አሁን አሁን በቤተክርስቲያን ጉዳይ የብዙዎቻችን ችግር ይኼ ይመስለኛል፤ አንድ ችግር ሲፈጠር ለአንድ ሰሞን ሁላችንም ሆ ብለን እንነሳለን እንረግማለን፤ እንተቻለን ተቃውሟችንን እናሰማለን መልሰን ግን ወዲያው እንረሳዋለን፤ በዚህም ምክንያት ለጥያቄዎቻችን መልስ ለችግሮቻችንም መፍትሔ የማናገኘው፤ ይህም ብቻ አይደለም መሠረታዊ ሀሳብን አሻጋሪ መፍትሔንም የሚያፈልቁ ሰዎች ዝምታን የሚመርጡት፤ ነገር ግን ሁለቱም ጠቃሚ አይደለም እኛም ዋና አጀንዳችንን አንርሳ ለችግራችን መፍትሔ አመንጪዎችም መርሳታችን ቢያሳስባቸውም መፍትሔውን ይንገሩን፤ እንድማመጥ እንመካከር እንከባበር! የተፈጠረውን ረስተን በአዲስ አጀንዳ አንነዳ፤ በነገሮችም ሁሉ አስተዋዮች ልንሆን ይገባል። እግዚአብሔር ሁላችንንም ይርዳን!
(ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"ሥላሴ ክቡር ምስጉን ነው፤ በአካላት ሦስት ናቸው፤ መለኮት አንድ ነው፤ ሥልጣን አንድ ነው፤ ሥራ አንድ ነው፤ ፈቃድ አንድ ነው፤ የመለኮት ገንዘብ የሚሆን ባሕርይ አንድ ነው።" /አባ ገብርኤል ሃይማኖተ አበው94፥2/
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🚩 እምቢ ማለት!
◈ የሰውን ልጅ ከብዙ መከራ ሊያወጣ የሚችል መፍትሔ ነው፤ ከጋብቻ በፊት የሚደረግ ያልተገባ ሩካቤን እና በዚያ ምክንያት የሚፈጠር ጽንስን ቀድሞ ለመከላከል የሚረዳ በቤተ ክርስቲያን የተፈቀደ ፍቱን መድኃኒት ነው፤ ይህን መድኃኒት ከፋርማሲ አንገዛውም ከቅጠልም አንሸመጥጠውም፤ እኛው ውስጥ ያለ እና ወደ አፍ የሚዋጥ ሳይሆን ከአፍ የሚወጣ መድኃኒት ነው፤ በእርግጥ ከአፍ የሚወጣ ቢሆንም አወጣጡ ላይ ግን ትንሽ ሊያስቸግር እና አንደበት ላይ መረር ሊል ይችላሉ፤ ያው መጎምዘዝ የብርቱ መድኃኒቶች ጠባይ ስለሆነ ይህ ብዙ አያስገርመንም፤ ኸረ መድኃኒቱ ይነገረን አላላችሁም? ይኸው ያዙ መድኃኒቱ "እምቢ" የሚለው አጭር ቃል ነው።
◈ ይህ ቃል ለብዙዎች መነሣትና መውደቅ ምክንያት የሚሆን ወሳኝ ቃል ነው፤ ሔዋን በእባብ ያደረ የዲያብሎስን ምክር ባትሰማ እና እምቢ ብትለው የሰው ልጅ ወደ ምድረ ፋይድ ባልወረደ ነበር "እምቢታ" ሰይጣን እኛን ለመጥለፍ የሚያዘጋጀውን አሽክላ ቆርጠን የምንጥልበት የተሳለ ሰይፍ ነው።
◈ ጌታ በገዳመ ቆሮንቶስ ሊፈትነው የመጣን ጠላት ድል የነሣው የጠየቀውን ሁሉ ሳይቀበል ድንጋዩን ዳቦ አላደርግም፣ ወድቄ አልሰግድልህም፣ ከመቅደስም ጫፍ አልዘልም ሲል "እምቢ" በማለት ነው፤ ቅዱስ ያዕቆብስ "ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል" አይደል የሚለው። (ያዕቆብ 4፥7)
◈ ለልጆቻቸው የሚሳሱና የሚጨነቁ ወላጆች ለወለዷቸው ከሚሰጧቸው ውድ ስጦታዎች አንዱ "እምቢ" ማለትን ነው፤ የሚሰጡበትም መንገድ ልጆቻቸው አድርጉልኝ ሲሉ የሚጠይቋቸውን አላስፈላጊ ነገሮች "እምቢ" ሲሉ በመከልከል ነው፤ የዛሬ ወላጆች አስፈላጊ እምቢታ የነገ የልጆች የፈተና ጊዜ መልስ ይሆናል፤ ዛሬ ወላጅ ሁሉን እሺ እያለ ካሳደገ፣ ነገ ልጁ ሲያድግ ክፋትና ወንጀልን "እምቢ" የሚልበት አቅም ያጣል። ለምን? ከልጅነቱ አልተማረማ።
◈ ጲላጦስ "እምቢ" ቢል ኖሮ የአይሁድን እብደት ባገደ የንጹሑ የኢየሱስ ክርስቶስም ደም ባልፈሰሰ ነበር፤ እምቢ አለማለት ለክፋት እምቢታን የማያውቁ ወንበዴዎችን ያበረታታል፤ ንጹሐንን ያስፈጃል፤ እስኪ ኃጢአትን፣ ክፋትን፣ ዘረኝነትን በአጠቃላይ ሰይጣንን እምቢ እንበል? እምቢ!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🚩 እግዚአብሔርን መፍራት
ወደ ፍቅር መንገድ ለመድረስ የመጀመርያው ፍርሃት ነው።
◈ በመጽሓፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኘው በመጽሓፈ ምሳሌ ላይ "የጥበብ መጀመርያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው" የሚል ቃል አለ፡፡ (ምሳ 9፥10) በዳዊት የመዝሙር መጽሓፍ ውስጥም ከዚህ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ቃል አለ። (መዝ 110፥10)
◈ ይህ እንዴት ነው የሚሆነው? በፍርሃትና በፍቅር መካከል ያለው ግንኝነት ምንድር ነው? ፍቁረ እግዚእ ቅዱስ ዩሐንስ ግን እንዲህ ይለናል "በፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም . . ." (1ኛ የሐ 4፥18)
መፍራት ስትጀምሩ ለእግዚአብሔር ትታዘዛላችሁ ትእዛዛቱንም ትፈጽማላችሁ።
◈ ቢያንስ ቢያንስ የእርሱን ቅጣት ትፈራላችሁ፥ አስፈሪው የፍርድ ቀን ትፈራላችሁ፥ ዘላለማዊ ስቃይ ትፈራላችሁ፤ የእርሱን ትእዛዛት የምትቀበሉ ከሆናችሁ ግን ለሕይወታችሁ ደስታንና ታላቅ ጥቅምን ታገኛላችሁ። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙራቱ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር ትእዛዛት ስለ ሥርዓቶቹና ስለ ሕግጋቱ እንዲህ እያለ ዘምሯል "የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፥ ዓይንንም ያበራል" "የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው ልብን ደስ ያሰኛል . . ." ፥ "ሕፃናት ጠቢባን ያደርጋል" "ከወርቅ እና ከክቡር እንቁ ይልቅ ይወደዳል ከማር ወለላም ይጣፍጣል" (መዝ 18፥7-10)
◈ ከዚህ በተጨማሪ ዳዊት በረዥሙ መዝሙሩ ውስጥ እንዲህ ብሏል "ለባርያህ ተስፋ ያደረግኸውን ቃልህን አስብ፤ ቃልህ ሕያው አድርጎኛልና ይህቺ በመከራዬ ደስ አሰኘችኝ" "እኔ ግን በፍጹም ልቤ ትእዛዛትህን እፈልጋለሁ" "እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል" "የሥራህን ሁሉ ፍጻሜ አየሁ ትእዛዛህ ግን እጅግ ሰፊ ነው" "አቤቱ ሕግህ እንደ ምን እጅግ ወደድሁ! ቀኑን ሁሉ እርሱ ትዝታዬ ነው" (መዝ 118፥...)
◈ የእግዚአብሔር ትእዛዛት በመውደድ መልካም የሆነውን እንወዳለን፤ መልካም የሆነውን በመውደድ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር እንደርሳለን።
(ብጽዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🚩 ወዳጄ ሆይ እስኪ ንገረኝ ለምንድነው የምታዝነው?
◈ ድሃ ስለሆንክ ነውን? ይልቁንስ በዚህ ምክንያት በማዘንህ ልታዝን ይገባሃል፤ ማዘን የሚገባኽ ድሃ ስለሆንክ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ሐሳብ ምን ያህል እንደራቅክ በማሰብ ልታዝን ይገባሃል፡፡
◈ ሐሳብህን ከጊዜአዊው ገንዘብ አንሥተህ ሰማያዊውን አክሊል ሽልማትህን ባለማሰብህ ልታዝን ልትተክዝ ይገባሃል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ በየቀኑ ይገደል ነበር፤ ነገር ግን አላዘነም፤ አላለቀሰም፤ ደስ ይለው ነበር እንጂ፤ ብዙ ጊዜ በረሃብ አለንጋ ይጠበስ ነበር፤ ነገር ግን አላዘነም፤ አላጉረመረመም፤ ይከብርበት ነበር እንጂ፤ ታድያ አንተ የዓመት ቀለብ የለኝም ብለህ ታዝናለህን “እኔ እኮ የቤተሰብ አባወራ ነኝ፤ ልጆችን አሳድጋለሁ፤ ሠራተኛ አለኝ፤ ሚስት አለችኝ፡፡
◈ ቅዱስ ጳውሎስ ግን ቢያስብ ለራሱ ብቻ ነው” ልትለኝ ትችላለህ፤ እኔም እንዲህ ብዬ እመልስሃለሁ ቅዱስ ጳውሎስ ያስብ የነበረው ለራሱ ብቻ አይደለም፤ ለዓለም ኹሉ እንጂ፤ አንተ አንድን ቤተሰብ ለማስተዳደር ትጨነቃለህ፤ ርሱ ግን ዓለምን ሁሉ ለማስተዳደር ይጨነቅ ነበር፤ በኢየሩሳሌም ለነበሩ ድሆች ይጨነቅላቸው የነበረው ርሱ ነው፡፡ በሜቄዶንያ ለነበሩት ያስብላቸው የነበረው እርሱ ነው፤ በየቦታው ለነበሩ ድኾች ይጨነቅላቸው የነበረው ርሱ ነው፤ ያስተዳድራቸው ከነበሩት ሰዎች ከሚሰጡት ይልቅ የሚረዱ ይበዙ ነበር፡፡
◈ ለዓለም ሁሉ ማሰቡ በሁለት ወገን ነበር፤ በአንድ ወገን እንዲሁ የሚበሉት አጥተው እንዳይጐዱ፤ በሌላ ወገን ደግሞ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው ባለጸጐች እንዲሆኑ፤ ስለዚህ አንተ ለልጆችህ ከምታስበው በላይ ቅዱስ ጳውሎስ ለዓለም ሁሉ ያስብ ነበር ብዬ እነግርሃለሁ፡፡
◈ ቅዱስ ጳውሎስ ያስብ የነበረው ለሚያምኑት ልጆቹ ብቻ እንዳይመስልህ፤ ለማያምኑትም ጭምር ይጨነቅላቸው ነበር እንጂ፤ እነርሱ ድነው እርሱ በነርሱ ፈንታ እንዲረገም ይመኝ ነበር፤ እነርሱ የዘለዓለም ሕይወት አግኝተው ርሱ ገሃነም እንዲገባ ይመኝ ነበር። (ሮሜ 9፥1-3)
◈ አንተ ግን ምንም ዓይነት ቁጣ ቢመጣም “እኔ ልራብልህ” ብለህ ስለወንድምህ አትሞትም፤ አንተ ለአንዲት ሚስትህ ብቻ ትጨነቃለህ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ግን “ዕለት ዕለት የሚከብደኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሐሳብ ነው” እንዳለ፤ ይጨነቅ የነበረው በዓለም ሁሉ ላሉት አብያተ ክርስቲያናት ነው፡፡ (2ኛ ቆሮ 11፥28)
◈ ወዳጄ ሆይ ታድያ ለምንድነው ከቅዱስ ጳውሎስ በላይ እንደምታስብ አድርገህ ራስክን የምትመለከተው? በምን ያህል ርቀት እንዳለህስ አታስተውልምን? ስለዚህ ማዘን፣ ማልቀስ የሚገባን በድህነት ውስጥ ስላለን አይደለም፤ ማልቀስ ማንባት የሚገባን በኃጢአት ማጥ ውስጥ ስንገባ ነው፤ የሚገባ ኀዘን ይኸው ነው፤ ከኃጢአት በቀር ለሌላ ማዘን እንዲሁ ተራ ነገር ነው ብዬ በእውነት ያለ ሐሰት እነግርሃለሁ፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
አደገኛ የአንገትና የእጅ ኪታቦች የጨነገፈ ትውልድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ሲለየው || 4ቱ የድህነት መንገዶች | አባ ገብረ ኪዳን መምህር ግርማ 🔥💥🚩🙄
https://youtu.be/HEWILBpoLp0
◈ "የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና።" መዝ. ፴፬፥፲፭ /34፥15/ 💥 እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወርሃዊ የመታሰቢያ በዓል አደረሰን። ምልጃቸው ከእኛ አይለይ፤ በረከታቸው ይደርብን። ◈
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🚩 እድልና አጋጣሚ የሚባል ነገር የለም
◈ ሳምራዊቷ ሴት ወደ ውኃ መቅጃ መጣች ኢየሱስ እንዲህ አላት፤ ውኃ አጠጪኝ አላት ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ለመግዛት ወደ ከተማ ሄደው ነበር፤ ሴቲቱ ጌታን አለችው አንተ አይሁዳዊ ስትሆን ሳምራዊ ከምሆን ሴት ውኃ እንዴት ትለምናለህ ? አይሁድ ከሳምራዊ ጋር አይተባበሩምና። (ዮሐ 4፥7-9)
◈ የሳምራዊቷ ሴት ታሪክ በብዙ መንገድ ሕይወታችንን ይነካል፤ እግዚአብሔር ስለእያንዳንዱ ያለውን ዕቅድ ያመለክተናል፤ መድኃኒታችን ወደ ሰማሪያ መጣ፤ በቀትር ሰዓት ወደ ያዕቆብ ጉድጓድ ደረሰ፤ በጉድጓድ አጠገብ ተቀመጠ ደቀ መዛሙርቱ ምግብ ለመግዛት ወደ ከተማ ሄደው ነበር፤ ይህ አጋጣሚ ነበረን? በዚያ ሲያልፍ ከሴቲቱ ጋር በድንገት የተገናኝ ይመስለናል?
◈ በሕይወታችን ብዙ ድርጊት ይፈጸማል፤ የተፈጸመበት ጊዜ መፈጸም በሚገባው ጊዜ እንደሆነ እየተመለከትን ነገር ግን ከዕድልና ከአጋጣሚው ጋር እናያይዘዋለን፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ድንገተኛና አጋጣሚ የሚባል ነገር የለም ነገሮችን አስቀድመው ከመፈጸማቸው በፊት ያውቃቸዋል።
◈ በሕይወታችን የሚፈጸሙት ክስተቶች በእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ ያሉ እንጂ በድንገት የሚፈጸሙ አይደሉም፤ ለምንፈጽማቸውና በሕይወታችን ለሚደረገው ለውጥ ሁሉ እግዚአብሔር ዕቅድ አለው።
(አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
በመተት እውቀታችንና ዕድላችን ሲወሰድ የምታዩ ምልክቶች ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ! ጸሎትና ስግደትን ሲናቋርጥ || ሕመምና መከራን መታገስ 🚩🔥
https://youtu.be/TJCYwoZL4Bo
ውዶች መዝሙር ተጋበዙልኝ። እንዴት አመሻችሁ፣ እንዴት አደራችሁ እንደሰዓት አቆጣጠራችሁ። ጾሙ ጸሎቱ አንዴት ይዟችኋል። እንበርታ፣ እንጠንክር። እርሱ አባትዬው ጌታችን ይረዳናል ብቻ በእምነት እንሁን። 🚩
🚩የመጠበቅ መሠረታዊ ነጥቦች
፩. በተስፋ መጠበቅህ እግዚአብሔር ለአንተ ባለው ፍቅር ላይ መመሥረቱን ማመን አለብህ። እግዚአብሔር አንተ ራስህን ከምትወድደው በላይ አንተን እንደሚወድህና አንተ ለራስህ ከምትሠራው የበለጠ እርሱ ለአንተ እንደሚሠራልህ ማመን አለብህ፡፡
እግዚአብሔር ሰው ሁሉ እንዲድንና ወደ እውነት እውቀት እንዲደርስ ይፈልጋል። (1ኛ ጢሞ 2፥4) ከዚህ በተጨማሪ በመዳፉ ውስጥ አንተን ከመቅረጹ በላይ በቀኝ እጁ መካከል እንዳለህ ልታውቅ ይገባሃል፤ በማንኛውም ጊዜም። "አልጥልህም አልተውህም" ይልሃል (ኢያ 1፥5)
፪. በተስፋ መጠበቅህ በእግዚአብሔር ጥበብ ላይ እምነት በማሳደር ሊሆን ይገባል።
አንተ ወሰን የሌለው ጥበቡ ከአንተም ሆነ ከሌላ ማንም ሰው እሳቤ እጅግ የራቀና የረቀቀ መሆኑን ልታውቅ ያስፈልግሃል። የእግዚአብሔር ጥበብ አንተ ልታየው የማትችለውን ነገር ማየት ስለሚችል ለአንተ የቱ መልካም እንደሆነ ማወቅ ይችላል። ኢዮብ ይህንን የእግዚአብሔር ጥበብ በመጨረሻው ሊገነዘበው ስለቻለ እንዲህ ብሏል። "ያለ እውቀት ምክርን የሚሰውር ማን ነው? ስለዚህ እኔ የማላስተውለውን የማላውቀውንም ድንቅ ነገር ተናግሬአለሁ" (ኢዮ 42፥3)
ስለዚህ ተረዳኽውም አልተረዳህውም እግዚአብሔር የአንተን ጉዳዮች በጥበቡ እንደሚቆጣጠር ማወቅ አለብህ፤ ስለዚህ ለእርሱ ጥበብ በርህን ከፍተህ ቆይ።
፫. በተስፋ መጠበቅህ በእግዚአብሔር ቃል ኪዳኖች ላይ እንደ ተመሠረተ ማመን አለብህ። አንተ ከዚህ የሚከተሉትን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳኖች ልታምን ይገባሃል። "እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ " (ማቴ 28፥20) "በውኑ ሴት ከማኀጸኗ ለተወለደው ልጅ እስከማትራራ ድረስ ሕጻኗን ትረሳ ዘንድ ትችላለችን? አዎን እርሷ ትረሳ ይሆናል እኔ ግን አልረሳሽም" (ኢሳ 49፥15) "እነሆ እኔ በእጄ መዳፍ ቀርጬሻለሁ" (ኢሳ 49፥16) በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፤ አይዞህ፤ አትፍራ፤ አትደንግጥ፤ ብዬ አላዘዝሁምን? (ኢሳ 1፥9)
"በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም" (ኢያ 1፥5)
"እኔ ከአንተ ጋር ነኝ ማንም ክፉ ሊያደርግብህ የሚነሳብህ የለምና አትፍራ።" (ሐዋ 18፥10)
አቡነ ሺኖዳ ሳልሣዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
🚩 የፍቅር እጦት
◈ ቂም እና ጥላቻን ይፈጥራል፤ ይህ ደግሞ በኃጢአት ሐሴት ማድረግን ያመጣል፤ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ "ጠላትህ ቢወድቅ ደስ አይበልህ በመሰናከሉም ልብህ ሐሴት አያድርግ"። (ምሳ 24፥17)
◈ ሌላው የፍቅር እጦት ውጤት ቁጣ እና ክፋት ነው፤ እንዲህ ያለው ሁኔታ ስድብን፣ ጠብን፣ ግድያን፣ ነቀፋን፣ ማዋረድንና ስም ማጥፋት ማስፋፋትን ያስከትላል፤ ከዚህ በተጨማሪ የፍቅር እጦት ወይም ጉድለት ወደ ቅንዓት ወደ አላዋቂነት፣ ወደ ኩራት፣ ወደ ጽናት ማጣትና ወደ ጭካኔ ይመራል።
◈ ለእግዚአብሔር የሚሆን ፍቅርን ማጣት በብዙ ጉዳዮች ውስጥ ሊገለጥ ይችላል፣ ከእርሱም መካከል ጸሎትን፣ መጽሐፍ ቅዱስንና፣ ቤተ ክርስቲያንን መርሳት ጥቂቶቹ ናቸው፤ በእግዚአብሔር ፊት መቆምን ማጣት እና በእግዚአብሔር መንግሥት ፈጽሞ ሐሴት አለማድረግ ሌሎቹ ጉድለቶች ናቸው።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ጨበረ፣ ራስታ የሚያደርጉ ክፉ መናፍስቶች ቅርብ ሆነን ከቃሉ የራቅን ብዙ ሰው እንዲህ ያስባል || የቤተሰብ ዛር መንፈሶች ፈተና #ethiopia 😭😰🙄
https://youtu.be/QalL2qJr_NI
አቤቱ፥ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል አድምጠኝም፥ ችግረኛና ምስኪን ነኝና። ቅዱስ ነኝና ነፍሴን ጠብቅ፤ አምላኬ ሆይ፥ አንተን የታመነውን ባሪያህን አድነው። አቤቱ፥ ቀኑን ሁሉ ወደ አንተ እጮኻለሁና ማረኝ።
የባሪያህን ነፍስ ደስ አሰኛት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን ወደ አንተ አነሣለሁና። አቤቱ፥ አንተ መሓሪና ይቅር ባይ ነህና፥ ምሕረትህም ለሚጠሩህ ሁሉ ብዙ ነውና። አቤቱ፥ ጸሎቴን አድምጥ፥ የልመናዬንም ድምፅ ስማ። ትመልስልኛለህና በመከራዬ ቀን ወደ አንተ እጠራለሁ።
አቤቱ፥ ከአማልክት የሚመስልህ የለም፥
እንደ ሥራህም ያለ የለም። ያደረግሃቸው አሕዛብ ሁሉ ይመጣሉ፥ አቤቱ፥ በፊትህም ይሰግዳሉ፥ ስምህንም ያከብራሉ፤ አቤቱ፥ ድንቅ የምታደርግ አንተ ታላቅ ነህና፥ አንተም ብቻህን ታላቅ አምላክ ነህና።
አቤቱ፥ መንገድህን ምራኝ፥ በእውነትህም እሄዳለሁ፤ ስምህን ለመፍራት ልቤ ደስ ይለዋል። አቤቱ አምላኬ ሆይ፥ በልቤ ሁሉ አመሰግንሃለሁ፥ ለዘላለምም ስምህን አከብራለሁ፤ ምሕረትህ በእኔ ላይ ታላቅ ናትና፥
ነፍሴንም ከታችኛይቱ ሲኦል አድነሃታልና።
አቤቱ፥ ዓመፀኞች በእኔ ላይ ተነሥተዋል፥
የክፉዎችንም ማኅበር ነፍሴን ፈለጉአት፤
በፊታቸውም አላደረጉህም። አቤቱ፥ አንተ ግን መሓሪና ርኅሩኅ አምላክ ነህ፤ መዓትህ የራቀ ምሕረትህም እውነትህም የበዛ፤ ወደ እኔ ተመልከት ማረኝም፤ ለባሪያህ ኃይልህን ስጥ፥ የሴት ባሪያህንም ልጅ አድን። ምልክትንም ለመልካም ከእኔ ጋር አድርግ፤ የሚጠሉኝ ይዩ ይፈሩም፥ አቤቱ፥ አንተ ረድተኸኛልና፥ አጽንተኸኛልምና። (መዝ.86፡1-17)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
በመስተፋቅር አግብታ ለ13 ዓመታት መውለዷንና ማግባቷን የማታውቀው እህት || የክፉዎች መጨረሻ መክልትህ ምንድነው? አሁን ይሄን ማን ያምናል?
https://youtu.be/Sr54v-6P-TQ
