uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 378 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 573-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 194-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 378 obunachiga ega bo‘ldi.

06 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 32 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 22.44% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.50% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 449 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 461 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 20 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 07 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 378
Obunachilar
-424 soatlar
-257 kunlar
+3230 kunlar
Postlar arxiv
‹‹#ያገለገለህነሰው_ሞት_ቸል_አትበል፡፡›› ሲራክ 38÷26 ( እያዘንን ጻፍንላቹ ) ደብራችንን ለ54 ዓመታት ያገለግሉትነ መሪጌታ ይሁኔ ፈቃዱ አጭር የሕይወት ታሪክ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ #መሪጌታ ይሁኔ ፈቃዱ (አጋፋሪ) #ትውልድ ፣ዕድገት እና ት/ት አጋፋሪ ይሁኔ ፍቃዱ ከአባታቸው መሪጌታ ፍቃዱ ተሰማ እና ከእናታቸው ከ ወ/ሮ ለምለም ወርቁ በ 1933 ዓ.ም በጎንደር ክፍለ ሃገር በ ደራ ወረዳ ልዩ ስሙ ደብረ ሲና ማርያም በሚባል ቦታ ተወለዱ መሪጌታ ይሁኔ ፍቃዱ እድሜያቸው ለትምህርት እንደደረሰ ከ አስኳላው ትምህርታቸው ጎን ለጎን ከ አባታቸው ከ መሪጌታ ፍቃዱ ከ ቁጥር እስከ ዳዊት ተምረዋል በዲቁና ሃገራቸው ያገለግሉ ነበር:: ከዛም በመቀጠል በደብረ ሲና ማርያም ፀዋአቶ ዜማ ተምረው ካጠናቀቁ በኃላ ወደ ምዕራብ ጎጃም አዊ ዞን ጋጋስታ ጊዮርጊስ በመሄደ ከ መምህር ቢንያም ቅኔን ከነ አገባቡ እና ከነጓዙ ተምረዋል ፡፡ አጋፋሪ ይሁኔ ፍቃዱ በ1954ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከመንፈሳዊው ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአስኳላው ትምህርት በመዝለቅ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በማጠናቀቅ በሂሳብ ትምህርት (አካውንቲንግ) ዲፕሎማቸውን ይዘዋል ፡፡ ትምህርት እና #አገልግሎት አጋፋሪ ይሁኔ ፍቃዱ ወደ አዲስ አበባ ከመጡበት ከ1954 ዓ.ም ጀምሮ ማረፊያቸውን በ ታላቁ ደብር ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በማድረግ አቋቋም ከመምህር ገብረ ማርያም ጠንቅቀው በመማር ከዛም ደብራችን እስከ ህልፈተ ሕይወታቸው ቀን ድረስ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ካላቸው የቃለ እግዚአብሔር ፍቅር በቀና አገልግሎት ለ54 ዓመታት በጽናት ሲያገለግሉ ኖረዋል ፡፡ አጋፋሪ ይሁኔ ፍቃዱ ከመንፈሳዊው አገልግሎታቸው በተጨማሪ በተማሩበት የቀለም ት/ት በመንግስት ልዩ ካቢኔ እንዲሁም በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሚኒሊክ ሆስፒታል በዋና ገንዘብ ያዥነት ለበርካታ አመታት በቅንነት እና በታማኝነት ሲያገለግሉ ቆይተው እድሜያቸው ለጡረታ ሲደርስ በክብር ተሸኝተዋል ፡፡ አጋፋሪ ይሁኔ ልዩ በሆነው ድምጻቸው እና የቀጨኔ ደብረሳለም የአቋቋም ይት ባህልን ጠንቅቆ በማወቅ እናም ከሰንበት ት/ቤታችን ጋር በመሆን በድምጽ ተቀርጾ እንዲቀር በማድርቅ፤ በልዩ የዜማ እና የድምጽ ፀጋቸው፤ እናወቃቸዋለን ፤ እናስታውሳቸዋልነ ፡፡ #ሕይወት አጋፋሪ ይሁኔ ከትዳር አጋራቸው 2 ወንድ እና 1 ሴት ልጅ አፍርተው 1 የልጅ ልጅ አይተዋል አጋፋሪ ይሁኔ ቅን ታማኝ እና ልዩ የቃለ እግዚአብሔር ፍቅር ያደረባቸው ከሰው ሁሉ ጋር በፍቅር እና በስምምነት የሚኖሩ ትልቅ ትንሽ ሳይሉ ሁሉን በፍቅር የሚያዩ የትህትና አባት ነበሩ :: #ኅልፈት ለጥቂት ቀናት ብቻ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት ቃለ እግዚአብሔርን ከ አፋቸው ሳይነጥሉ በ80 ዓመታቸው አርፈዋል ሥርዓተ ግብዐተ መሬታቸው ለ 54 ዓመታት ባገለገሉበት እና ብዙ ደቀ መዛሙርትን ባፈሩበት በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም እና ደብረ ትጉኃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በወርኃ ሰኔ ቀን 24 2012 ዓ.ም ተፈጸመ፡፡ ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጆቻቸው እንዲሁም ለዘመናት በአንድ መቅደስ ውስጥ አብረው ሲያገለግሉ ለኖሩት ሊቃውንት እግዚአብሔር መጽናናቱን ያድልንን፡፡ በረከታቸው ይደርብን አጭር ሺድዮ ይመልከቱ https://youtu.be/8ZwyVQwEzUg

‹ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት #ሐምሌ 7/2012 ዓ.ም በሐመረ ኖህ ቅድስት ኪዳነምሕረት ገዳም #በሥርዐተ_ተክሊል ጋብቻህን የፈጸምከው የሰ/ት/ቤታች አባል ወንድማችን #እንዳልካቸው_አወቀ ከእህታችን #መስታዎት_ይርጋለም ጋር የፈጸምከው ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሣራን፤ የይሰሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ÷ ያጣምራቹ ÷ ያዋህዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ #ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኀላ ይከተላቹ፡፡ <<ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንደሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እደዚሁ ጌታ ቤተ-ክርስቲያንን እደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡>> ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበስ ለፓሊካርፐስ በላከው መልእክቱ፡፡ <ከተጋባቸሁ በኋላ ባልና ሚስተ አንድ አካል ናችሁ፡፡ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፈቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፈ ቅዱስ አጼ ዘርአያዕቆብ፡፡

‹ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ ፤ ይህ ነገር ጥልቅ ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው ፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በሐምሌ 5/2012 ዓ.ም በቀ/ደ/ሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ #በሥርዐተ_ተክሊል ጋብቻህን የፈጸምከው የሰ/ት/ቤታች አባል እና #ሰብሳቢ_ዲያቆን_ታምራት_ሙሉነህ እና፤ የሰ/ት/ቤታችን አባል የሆንሽው #ሮማን_ለማ፤ የፈጸማቹሁት ጋብቻ፤ የአብርሃምንና የሣራን፣ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ÷ ያጣምራቹ ÷ ያዋህዳችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ ፤ ቅዱስ ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኃላ ይከተላችሁ፡፡ <<ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንደሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡>> ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፓሊካርፐስ በላከው መልእክቱ፡፡ <ከተጋባቸሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ፡፡ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፈቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ቅዱስ አጼ ዘርአያዕቆብ፡፡