uz
Feedback
Repi primary school

Repi primary school

Kanalga Telegram’da o‘tish

ተማሪነት በሕይወት ውስጥ የማይረሳ እና ተገልጦ የማያልቅ ምዕራፍ ነው። እኛ ደግሞ ከዚህ ተገልጦ ከማያልቅ ምዕራፍ ውስጥ ምርጥ ምርጡን እንሰጣለን። ተማሪዎች በቤታቸው ሆነው ጥያቄዎችን በመስራት ለፈተና የምናዘጋጅበት ቻናል ነዉ:: 📩 Mars@abc ☎ ️ 011 369 4040 0909 61 58 78

Ko'proq ko'rsatish
3 000
Obunachilar
+624 soatlar
+167 kunlar
+2330 kunlar
Postlar arxiv
ምክር ለተፈታኞች ተፈታኝ ተማሪዎች እንኳን በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው ፈተና  በሰላም አደረሳችሁ። ይህ ለእናንተ ወሳኝ ጊዜ ነው። እስካሁን ትምህርታችሁን እያጠናችሁ ቆይታችኋል። መልካም ነው። ነገር ግን በፈተና ወቅት የምታከናውኗቸው ተግባራትም የጥናታችሁን ያህል ውጤታችሁ ላይ ተጽዕኖ አላቸው። ስለዚህ በዚህ ወቅት ምን ማድረግ እንዳለባችሁና ምን ማድረግ እንደሌለባችሁ ጠንቅቃችሁ ማወቅ ይጠበቅባችኋል። ለዚህም ይረዳችሁ ዘንድ የሚከተሉትን ምክሮችን ከወዲሁ ተረድታችሁ ለመተግበር ዝግጁ ሁኑ! ⓵ በዋዜማው ስልክ መዝጋትና ከሚረብሹ ነገሮች ራስን ማራቅ ያስፈልጋል። ስልካችሁን መዝጋት ሀሳባችሁን ሊሰርቁ ከሚችሉ ማህበራዊ ሚዲያዎች መራቅ ይገባችኋል። በዚህ ወቅት ትኩረታችሁን ፈተናችሁ ላይ ብቻ አድርጉ፤ ⓶ በቂ እንቅልፍ ተኙ። በፈተና ዋዜማ ለማንበብ ብላችሁ በፍጹም አታምሹ። ባጭሩ በዚህ ቀን ተጨማሪ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ ተጨማሪ ሰዓት መተኛት የተሻለ ዉጤት አለው። በቂ እንቅልፍ አለመተኛት በፈተና ወቅት ለድብርትና ለራስ ምታት ሊዳርግና ሥራችሁን ሊያበላሽ ይችላል። ጥሩ እንቅልፍ ለመተኛት ከባድ ምግቦችን አለመመገብ፤ ብዙ ቡና አለመጠጣት፤ እና ሌሎች አነቃቂ ነገሮችን አለመውሰድ ይመከራል፤ ⓷ ጠዋት ማልዶ መነሳት: በጊዜ ተነስቶ መዘጋጀት ከመቻኮል ጋር ተያይዞ ከሚመጣ መታወክ ያድናል። በተጨማርም ወደፈተናው አዳራሽ በጊዜ ለመድረስ ያስችላል፤ ⓸ ቁርስ በአግባቡ መብላት: በፈተና ወቅት ቁርስ አለመብላት አእምሮአችን የሚፈልገውን ያህል ኃይል እንዳያገኝ ስለሚያደርግ ለማሰብ አቅም እንዲያንስ ያደርጋል። ስለዚህ ቀለል ያሉ ምግቦችን ተመግባችሁ መሄድ ይኖርባችኋል። ከባድ ምግቦችን መመገብ ደግሞ አእምሮአችን ምግብ የመፍጨት ሥራ ላይ ብቻ እንዲወጠር ስለሚያደርግ ድካምና እንቅልፍ ያመጣል፤ ⓹ ወደ መፈተኛ ቦታው ፈተናው ከሚጀምርበት ሰዓት በፊት ቀድሞ መድረስ ያስፈልጋል። ይህም ለመረጋጋት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አለው፤ ⓺ ከቤት ስትወጡ የፅህፈት መሳሪያዎቻችሁንና የመታወቅያ ካርዳችሁን መያዛችሁን እርግጠኛ ሁኑ። ይህም ከመንገድ ከመመለስና ከማርፈድ ያድናችኋል። ትርፍ እርሳሶችን እና የእርሳስ መቅረጫዎች መያዝ በጣም አስፈላጊ ነው፤ ⓻ ወደ ፈተና አዳራሽ ከመግባት በፊት ወደ መፀዳጃ ቤት መሄድ መልካም ነው። ምናልባት የፈተናው ሰዓት ረዥም ቢሆንና ሽንት ቢይዛችሁ መጨናነቅን ያመጣል። አቋርጣችሁ መውጣት ላይፈቀድላችሁ ይችላል፤ ⓼ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ላይ ስማችሁን በአግባቡ መጻፋችሁን እርግጠኛ ሁኑ። አንድ ፊደል እንኳን ብትሳሳቱ ኋላ የት/ት ማስረጃችሁ ላይ ስለሚቀመጥ ለማስቀየር ዋጋ ያስከፍላል፤ ⓽ መመሪያዎችን (instructions) በአግባቡ ማንበብና መተግበር ያስፈልጋል። በእያንዳዱ ፈተና ወረቀት ላይ ወይም የፈተናው ክፍሎች ላይ የሚሰጡትን መመሪያዎች በአግባቡ ማንበብና መተግበር ይኖርባችኋል፤ ⓾ አትደንግጡ! በደንብ ተንፍሱ! ብዙ ኦክስጂን ወደ ውስጣችን ማስገባት ብዙ ምግብ እንዲቀጣጠልና ኃይል እንዲመረት ስለሚያደርግ ጉልበትና ድፍረት ይጨምርላችኋል፤ ⓫ መልስ መመለስ ከመጀመራችሁ በፊት እያንዳንዱ የፈተና ክፍል ስለያዛቸው የጥያቄ አይነቶች ገረፍ ገረፍ እያደረጋችሁ ብታዩ መልካም ነው። ይህም የተሰጣችሁን ሰዓት በጥያቄው ክብደት ልክ ከፋፍላችሁ ለመጠቀም ያግዛችኋል፤ ⓬  አንዱ ጥያቄ ከከበዳችሁ ዝለሉት፤ አንድ ጥያቄ ላይ ተጠምዳችሁ ብዙ ጊዜ የምታጠፉ ከሆነ ቀጥለው ለሚጠብቋችሁ ጥያቄዎች ጊዜ ሊያጥራችሁ ይችላል። ስትዘሉት ግን የጥያቄ ወረቀቱ ላይ ምልክት ማድረጋችሁን እንዲሁም መልስ መስጫ ወረቀቱ ላይ ከተሰጡት አማራጮች አንዱን መልስ በግምት ማጥቆራችሁን አትርሱ። አጥቁሮ ማለፍ ምናልባት በኋላ የተሰጠው ጊዜ ቢያልቅና ወደ ጥያቄው መመለስ ቢያቅታችሁ መልስ መስጫ ቦታው ባዶ ሆኖ እንዳይቀር ያደርጋል፤ ⓭ ቶሎ ለመውጣት አትቸኩሉ፤ ምንም አይጠቅማችሁም፤ ሰዓታችሁን አሟጥጣችሁ መጠቀማችሁን፤ ሁሉንም ጥያቄዎች በአግባቡ መመለሳችሁንና ማጥቆራችሁን አረጋግጡ። ጊዜ ቢተርፋችሁ ጥያቄዎቹን ለመከለስ ተጠቀሙበት፤ ⓮ ያልገባችሁ ማንኛውንም ነገር ሲኖር ፈታኞችን ለመጠየቅ አትፍሩ (ከመልስ በስተቀር😉)፤ ⓯ ልክ የፈተና ወረቀቱን ከመለሳችሁበት ጊዜ ጀምሮ የዚያ ትምህርት (subject) ነገር ማክተሙን በመገንዘብ ለቀጣዩ ፈተና እራስን ማዘጋጀት ይገባል። እንጂ፤ ስላለፈው ፈተና እያሰላልሰሉ መጨነቅ ለቀጣዩ ፈተና በምታደርጉት ዝግጅት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል።
መልካም ዕድል!!!

ለ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ። ጥብቅ ማሳሰቢያ!!!!!!!!!!!!!! ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል አስፈታኞች በሙሉ:- 1)የልዩ ፍላጎት ተማሪዎች በምዝገባ ጊዜ የተሞላ መረጃ ጋር ክክል መሞላቱን ማረጋገጥ(ዕድሜ ፣ፆታ እና ሙሉ ስም በትክክል መሞላቱን ማረጋገጥ 3)ሁሉም የግል እና የመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ክልላዊ ፈተና ለመፈተን ሲመጡ የየትምህርት ቤቱ ዩኒፎርም ለብሰው እንዲመጡ እና አድሚሽን ካርድ ይዘው እንዲመጡ ማረጋገጥ 4)በሁለቱም መረሃ ግብር ተደባልቀው ሳይሆን ተለያይተው እንደሚፈተኑ ማረጋገጥ 5)የግልም ሆነ የመንግስት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ዓርብ ሻርፕ 3:00 በየመፈተኛ ጣቢያቸው ተገኝተው ክፍል ገብተው ኦሪንቴሽን ይወስዳሉ 6)ልዩ ፍላጎት ተማሪዎች እና መድሃኒት ተጠቃሚ ተማሪዎች  በሀኪም የታዘዘ የሳይት መነፀር እና መድሃኒት መረጃ ይዘው መገኘት አለባቸው 7)አማርኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የሚማሩ ተማሪዎች በአማርኛ፤አፋን ኦሮሞን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የሚማሩ ተማሪዎች በአፋን ኦሮሞ መረጃ እንደሚሞሉ ግንዛቤ መፍጠርና ማለማመድ ያስፈልጋል። 8) ሁሉም ትምህርት ቤቶች ከአለባበስ (የት/ቤቱ ዩንፎርም እና በሰዓት መገኘት እንዲሁም ከአጠቃላይ ስነ ምግባር ጋር በተያያዘ ከወላጅ ጋር መግባባት ያስፈልጋል(ከአቅም በላይ ከሆነ ቶሎ ለወረዳ እና ክ/ከተማ ሪፖርት ማድረግ ያስፈልጋል 9)አድሚሽን ይዞ ያልተገኘ ግቢ መግባት አይችልም ስለዚህ ር/መምህራን ተከታትለው መፍትሄ መስጠት ያስፈልጋል። 10)በግሩፕ ፀብ የተሣተፉ፣ያነሳሱ እና የተቀላቀሉ እርምጃ ይወሰድበታል፣ከፈተናም ይሰረዛል። 11) መጋቢ እናቶች ስልክ ይዞ መገኘት የለባቸውም፣ቁርስ እና ምሳ በጊዜ መዘጋጀቱን ማረጋገጥ፣ምግብ በሜኑ ከቢሮ በወረደው መሠረት ተግባራዊ መደረግ አለበት 12) የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ላይ የልማት ሥራዎች እየተሠራ መሆኑ ይታወቃል፤ቢሆንም በፈተና ሳምንት ከተፈቀደላቸው ውጭ ማንም ግቢ መግባት አይችሉም(ት/ቤት የሜዳ ግንባታ የሚሠሩ ጭምር አይችሉም ለጊዘው ይቆማል ተብሏል።) 13)ተማሪዋች የፈተና ድሲፕሊን መመሪያ መሠረት ተራርቀው እንደሚቀመጡ ማረጋገጥ               መልካም ምሽት የወረዳ 11 ትምህርት ጽ/ቤት

photo content

photo content

photo content

photo content
+2

የ2018 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና የሚወስዱ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ብዛት፣ የፈተና ጣቢያዎች እና በጣቢያዎቹ የተመደቡ ትምህርት ቤቶች ምደባ።

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣ ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

ትኩረት ይደረግ ከወጣው መርሀግብር ውጪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።
ትኩረት ይደረግ ከወጣው መርሀግብር ውጪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን።

photo content

photo content

ውድ የእስልምና እምነት ተከታይ እህት ወንድሞቻችን እንኳ ለአረፋ በዓል አደረሳችሁ መልካም በዓል ይሁንላችሁ ።

ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሳችሁ::
ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሳችሁ::

Check out repi primary and middle school's video! #TikTok https://vm.tiktok.com/ZS9YCFAJHB5su-d08zz/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

ከላይ ያለው ሊንክ የትምህርት ቤታችን የቲክቶ አካውንት ስለሆነ እና መረጃዎችን በቲክቶክ አካውንታችን ስለምንለቅ ሁላችሁም join በማድረግ እንድትገቡ እናሳእቃለን። #ት/ቤቱ

photo content

photo content