uz
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Ko'proq ko'rsatish
2 619
Obunachilar
+324 soatlar
+207 kunlar
+3730 kunlar
Postlar arxiv
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ መወያየታቸው ተገለጸ። ሚያዚያ ፲፭/ ፳፻፲፯ ዓ.ም ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰ
+4
ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን በማስመልከት ባስተላለፉት ትምህርት ዙሪያ መወያየታቸው ተገለጸ። ሚያዚያ ፲፭/ ፳፻፲፯ ዓ.ም ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ማለዳ ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ባለፈው አርብ በስቅለት ዕለት በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በቅድስት ድንግል ማርያም ዙሪያ ያስተላለፉትን ትምህርት በተመለከተ ውይይት መደረጉ ተገልጿል። በብፁዕነታቸው  የተላለፈውን ትምህርት ዝርዝር ሁኔታ በመመርመርም ውሳኔ ለማስተላለፍ  ይቻል ዘንድ ሁሉም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት በምልዓት በተገኙበት  ለረቡዕ ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ/ም ቀጠሮ ተይዟል። በተያያዘ ዜና የሮም ካቶሊክ ቤተክርስቲያን መሪ በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ ፖፕ ፍራንሲስ ስርዓተ ቀብር ላይ፦ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ(ዘአውሮፓ) ቤተክርስቲያናችንን በመወከል እንዲገኙ ተወስኗል። ምንጭ :- የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የደብራችን አገልጋይ የሆኑት ሊቀ መዘምራን አምሐ ነጋሽ (የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የሆኑት የወንድማችን ዮሴፍ አምሐ እና ወ/ሮ ሔለን አምሐ ወላጅ አባት) አርፈው። ሥርዓተ ቀብራቸው
የሐዘን መግለጫ የደብራችን አገልጋይ የሆኑት ሊቀ መዘምራን አምሐ ነጋሽ (የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የሆኑት የወንድማችን ዮሴፍ አምሐ እና ወ/ሮ ሔለን አምሐ ወላጅ አባት) አርፈው። ሥርዓተ ቀብራቸው በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ የተፈጸመ ስለሆነ ቦሌ ቡልቡላ ማርያም ማዞሪያ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን።  የአባታችንን ነፍስ  ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የደብራችን አገልጋይ የሆኑት ሊቀ መዘምራን አምሐ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የሆኑት የወንድማችን ዮሴፍ አምሐ እና ወ/ሮ ሔለን አምሐ ወላጅ አባት አርፈዋል። የአስከሬን ሽኝት ዛሬ ሚ
የሐዘን መግለጫ የደብራችን አገልጋይ የሆኑት ሊቀ መዘምራን አምሐ የሰንበት ት/ቤታችን አባላት የሆኑት የወንድማችን ዮሴፍ አምሐ እና ወ/ሮ ሔለን አምሐ ወላጅ አባት አርፈዋል። የአስከሬን ሽኝት ዛሬ ሚያዝያ 13/2017ዓ.ም ከቀኑ 7:00 በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ተከናውኖ ሥርዓተ ቀብራቸው ከቀኑ 8:00 በደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ የሚፈጸም በመሆኑ መገኘት የምትችሉ አባላት በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን።  የአባታችንን ነፍስ  ይማርልን ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በዓለ ትንሣኤ 2017 ዓ.ም በጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ
+9
በዓለ ትንሣኤ 2017 ዓ.ም በጽ/ጽ/ሐ/ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍሥሓ ወሰላም ትንሣኤ፡- ትንሣኤ ተንሥአ ተነሣ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙ መነሣት
+1
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን አሰሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍሥሓ ወሰላም ትንሣኤ፡- ትንሣኤ ተንሥአ ተነሣ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙ መነሣት ማለት ነው፡፡ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ” ያለ ጌታ በጥንተ ትንሣኤ በዕለተ እሑድ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡ መልአኩም ማር.(፲፮፣፮) “አትደንግጡ የተሰቀለውን የናዝሬቱን ኢየሱስ ትሻላችሁን? እንደተናገረው ተነሥቷል” ብሎ ለቅዱሳት አንስት ነግሯቸዋል፡፡ (ሉቃ.፳፬፣፮) ክርስቶስ ለሙታን ሁሉ በኲር ሆኖ ተነሥቶአል፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ በስሙ ላመኑ ክርስቲያኖች ሁሉ ትንሣኤ ነው፡፡ የሙታንን ሁሉ መነሣት የሚያረጋግጥልን የጌታ ትንሣኤ ነው፡፡ የክርስቶስም ትንሣኤ መርገመ ሥጋ፥ መርገመ ነፍስ፤ ሞተ ሥጋ፥ ሞተ ነፍስ የተሻረበት ርደተ ገሃነም ጠፍቶ፥ በአዳም የተፈረደው ፍርድ ሁሉ ተደምስሶ፤ ፍጹም ነፃነት፣ የተገኝበት ነው። እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ         የፍኖተ ብርሃን ዘጎላ ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ስለሆነም የመጨረሻው ዕድላችን የተንጠለጠለው እምነትን ተከትለን በምንሰራው ስራ ላይ መሆኑን ለኣፍታ እንኳ መዘንጋት የለብንም፤ ዛሬ ከሰው ኣእምሮ በእጅጉ እየራቀ የሚገኘው ይኸው እምነትና ሥነ-ምግባር ነው፤ ሰዎች ከእምነትና መልካም ሥነ-ምግባር በራቁ ቊጥር ሕይወት መራራ እንድትሆን ትገደዳለች፡፡ እኛ ኢትዮጵውያን ከጥንት ጀምሮ በእምነትና ሥነ-ምግባር እየተመራን፣ በደልን በይቅርታ እየዘጋን፣ እስከ ጋብቻ በሚዘልቅ ባህለ-ዕርቅ ደምን እያደረቅን፣ በወንድማማችነት ፍቅር ተስማምተን በሺሕ ለሚቆጠሩ ዘመናት እንዳልኖርን፣ እነሆ ዛሬ ለታላቅነታችን በማይመጥን ሆናቴ መለያየትና መጣላት ብሎም እርስ በርስ መገዳደል ዕለታዊ ተግባራችን ኣድርገን እንገኛለን፡፡ ይህ በጣም ኣሳዛኝ ክሥተት ነው፤ ይህንን ሳናስተካክል የምናከብረው በዓለ ትንሣኤም እዚህ ግባ የሚባል ደስታ ሊያስገኝልን እንደማይችል የታወቀ ነው፡፡ እየሆነ ያለው ሁሉ ማንንም ኣይጠቅምም፤ በዕርቅ፣ በይቅርታና በውይይት የማይፈታ ችግር ያለ ይመስል ይህን ያህል መጨካከን እንዴት እንደ መፍትሔ ተደርጎ ይወሰዳል? አሁንም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የምንማፀነው፡- እባካችሁ እኛው ራሳችን ሸምጋይና ተሸምጋይ ሆነን ችግሮቻችንን ለመፍታት በብርቱ እንስራ፤ መፍትሔም እናምጣ፤ መሳሪያ ኣንሥታችሁ እርስ በርስ በመገዳደል የምትገኙ ወገኖቻችን እባካችሁ ቆም ብላችሁ ኣስቡና ሰላምና ዳቦ ኣጥቶ ለተቸገረው ሕዝባችሁ ስትሉ ለሰላማዊ መፍትሔ ዕድል ስጡ፤ ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገር የሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆኗን በትክክል የሚያረጋግጥ ሰላማዊ መፍትሔ በማስቀመጥ ለአንድነትዋና ለዕድገትዋ አጥብቃችሁ ጣሩ፤ ግጭትና መለያየት ከሚያጠፋን በቀር ምንም ዓይነት ጥቅም ሊሰጠን እንደማይችል ብዙ ማብራሪያ የሚያስፈልገው ኣይደለም፤ ስለሆነም ገዳዩን መሳሪያ ኣስቀምጡና በሃይማኖት፣ በኣንድነት፣ በስምምነትና በጭንቅላት ኃይል ሰላምን ኣምጡ፤ ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ጥሪ ነው፤ በመጨረሻም፡- በልዩ ልዩ ምክንያት ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው በየኣካባቢው በረኃብ ኣለንጋ እየተገረፉ የሚገኙት ወገኖቻችን በትንሣኤው በዓል ተጽናንተውና እፎይ ብለው በደስታ እንዲያሳልፉ ካለን ከፍለን በመመገብና በማልበስ እንድንደርስላቸው በእግዚአብሔር ስም ኣባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤ በድጋሚ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! መልካም በዓለ ትንሣኤ ያደርግልን! “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!            አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ                ተክለ ሃይማኖት፣        ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም             አዲስ አበባ ኢትዮጵያ፣ ©የብጹዕ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

Afework: መልእክተ ፓትርያርክ ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክነት ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት፤ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣ በትንሣኤው የሕይወት መንገድን ያሳየን ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት በዓለ ትንሣኤው በሰላም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ! “ወኣርኣይከኒ ፍኖተ ሕይወት፡- የሕይወትን መንገድ ኣሳየኸኝ” (መዝ.፲፭÷፱-፲፩)፤ ሕይወት በዓለመ ፍጡራን ውስጥ ከሚገኘው ድንቅ ነገር ሁሉ ተወዳዳሪ የሌላት ድንቅ ነገር ናት፤ ሕይወት ኣካልን የማንቀሳቀስ፣ የማመዛዘን፣ የመወሰንና የመስራት ሀብተ ጸጋ ያላት ልዩ ፍጥረት ናት፡፡ በዚህም ምክንያት ሕይወት ወደ እግዚአብሔር የሚቀርብ ወይም የሚመስል ጠባይ ኣላት፤ ሰው የእግዚአብሔር መልክና ኣምሳል ኣለው የሚለው መጽሓፍ ቅዱሳዊ ኣስተምህሮም ከዚሁ ጋር የሚስማማ ነው፤ ሕይወት ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታ የተጣበቀ ወይም የተሳሰረ ግንኙነት ኣላት፤ “ወኅብእት ሕይወትክሙ ምስለ ክርስቶስ፡- ሕይወታችሁ ከክርስቶስ ጋር የተሳሰረች ናት” የሚለው ሐዋርያዊ አባባልም ይህንን ያመለክታል፡፡ ሕይወት ፈጣሪንና የፈጣሪ ርዳታን ስትሻ የመኖርዋ ምስጢርም ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኝ ጸጋ ስላላት ነው፤ ሕይወት መልካም ስትሰራ ደስተኛ፣ ክፉ ስትሰራ ደግሞ ስቅቅተኛ የምትሆንበት ምክንያትም ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኛት ጸጋ ስለሚነግራት ነው፡፡ ምክንያቱም መልካምን መውደድ፣ ክፉን መጥላት የእግዚአብሔር የማይለወጥ ጠባይ ስለሆነ፣ ክፉን ሰርታ ከእርሱ ጋር በደስታና በነጻነት መኖር በፍጹም ኣትችልምና ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው ኣዳም ክፉውን ከሰራ በኋላ ወዲያውኑ መሸሸግና መደናገጥ ሊወረው የቻለው ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላት ውሳጣዊት ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ጋር ኣብራ መቀጠል የማትችልበት ደረጃ እንደደረሰች ስለተረዳች ነው፡፡ ከዚህ ኣንጻር ሕይወት የመኖር ጸጋ ብቻ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ተሳስሮ የመኖር ጸጋም ያላት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡  ሕይወት የማትጠፋ ብትሆንም የመሞት ስጋት ያልተለያት ፍጡር ናት፤ በተለይም እግዚአብሔርን የበደለች ዕለታ ከባድ የሞት ኣደጋ ያጋጥማታል፤ ይህም ሞት የሥጋ ሳይሆን ከእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ከሆነው ሁሉ መለየት ነው፤ የሕይወት ከባዱ ሞትም ይኽ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እኛ ሰዎች በኃጢኣት ጠንቅ ያጣነው ሕይወት እንዳለ ቅዱስ መጽሓፍ “በኣንድ ሰው በደል ኃጢኣት ወደ ዓለም ገባ፤ በዚህም ምክንያት ሰው ሁሉ ሞተ ወይም ከእግዚአብሔር ተለየ” በማለት የእኛ ከእግዚአብሔር መለየት ዋናው ሞት እንደሆነ ያስረዳል፡፡ይህ ገለጻ ከእግዚአብሔር ጋር የመኖር ሕይወታችን በበደል ምክንያት ማጣታችንን የሚያሳይ  ነው፡፡ እኛ በደለኞች ሆነን ከእግዚአብሔር የተለየንበት የመጀመሪያው ምክንያት በደለኞች ከሆኑ ኣዳምና ሔዋን የተገኘን መሆናችን  ነው፡፡ በመሆኑም የሁላችንም ሥጋዊና መንፈሳዊ ኣካል የተከፈለው ከነሱ እንደመሆኑ መጠን ያለን ሁሉ እንደነሱ ቀድሞውኑ የሞተና የተፈረደበት ነው፡፡ በሌላ ኣባባል በጥንተ ኣብሶ ምክንያት ከእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ከሆነው ሁሉ የተለየን ሆን ማለት ነው፤ ስለዚህም ነው በኣንድ ሰው በደል ምክንያት ሁሉም ሞቱ ብሎ እግዚአብሔር ያሳወቀን፤ ጥንተ ኣብሶ ወይም የውርስ ኃጢኣት የሚባለውም ይኽ ነው፡፡ ከዚህም ጋር ከእግዚአብሔር የለየን የውርሱ ኃጢኣት ሳይበቃን በየሰዓቱ በምንፈጽመው ክፉ ተግባር በበደል ላይ በደል እየጨመርን በመቀጠላችን በጨለማ ላይ ተጨማሪ የጨለማ ጥላ ኣክለንበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ ሞታችን ወይም ከእግዚአብሔር መለየታችን የሰፋና የከፋ እንዲሆን ኣድርጎታል፤ የተወዳዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናትና ምእመናት! ከእግዚአብሔር የለያየን ኣበሳ - ኃጢኣት በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ከባድ ቢሆንም እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ያለው ፈቃድ በተስፋ ጭላንጭል ማሳየቱን ኣላቋረጠም፡፡ ይኸውም የበደላችን ዕዳ ከመጀመሪያው ኣንሥቶ የማዳን ተስፋውን በተነገረለት በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛዊ ሞት እንደሚሰረዝ፣ በእርሱም ጽድቅ እንደ ጻድቃን ተቈጥረንና ያጣነውን ሕይወት እንደገና ኣግኝተን ወደ እግዚአብሔር እንደምንቀርብ፣ ይህም ከትንሣኤ በኋላ እውን እንደሚሆን እግዚአብሔር ለእኛ ደጋግሞ ይፋ ኣድርጎኣል፡፡ ይህንን ተስፋ - ትንሣኤ በመንፈስ ቅዱስ የተረዳ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በምስጋና መዝሙሩ እንዲህ ብሎ ይገልጸዋል፤ “ዳግመኛም ሥጋዬ በተስፋው ኣደረ፤ ነፍሴን በመቃብር ኣትተዋትምና፤ ጻድቅህንም በመቃብር ተጥሎ፤ ፈርሶና በስብሶ ይቀር ዘንድ ኣሳልፈህ ኣትሰጠውም፤ የሕይወትንም መንገድ እንዲህ ኣሳየኸኝ” በማለት የሕይወታችን ተስፋ-ትንሣኤን በሚያስደንቅ ኣገላለጽ አስረድቶናል፡፡ ገለጻው የክርስቶስንና የኛን ትንሣኤ እንደሚመለከት በቅዱሳን ሓዋርያት ተርጓሚነት በቅዱስ መጽሓፍ ተብራርቶ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የእኛ መጨረሻ የሚጠናቀቀው በመቃብር ተጥሎ፤ ፈርሶና በስብሶ በመቅረት ሳይሆን እንደገና ተነሥቶና ከእግዚአብሔር ጋር በተሳሰረ ኃይለ ሕይወት ለዘላለም በመኖር እንደሆነ ቃሉ ያስረዳናል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ከትንሣኤ በኋላ የሚሆነውን ይህን ጣዕመ ሕይወትን ነው ኣሳየኸኝ ብሎ የገለጸው፤ ጌታችን የዚህ ሕይወት የትንሣኤ በኵር ሆኖ ተነሥቶኣል፤ ከትንሣኤውም በኋላ ለዘላለም በሕይወት ይኖራል፡፡ በቀጣይም ጊዜው ሲደርስ እኛ ተከታዮቹ የእርሱን ዓይነት ትንሣኤ ተነሥተን በማያልቅ ኃይለ ሕይወት ከሱ ጋር ለዘላለም በሕይወት እንኖራለን፤ ጌታችን ያሳየን የሕይወት መንገድ ይኸው ነው፡፡ ይኽ ሕይወት ከሁሉም ህላዌ - ሕይወት የላቀና የበለጠ ጣዕም ያለው ዘላለማዊና ድንቅ ሕይወት ነው፤ ይኽ ሕይወት ከስጋት፣ ከስሕተት፣ ከቅጣትና ከሞት - ፍርሓት ነጻ የሆነ፣ በፍጹም ነጻነትና ደስታ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም የሚያኖር ሕይወት ስለሆነ ሁላችንም ወደዚህ ሕይወት ለመድረስ በእምነት እንተጋለን፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ዘር ሳይኖር ፍሬ እንደማይገኝ ሁሉ ሕይወታዊ  ትንሣኤም ያለ ሃይማኖትና ሥነ - ምግባር ሊገኝ ኣይችልም፡፡ ጌታችንም ይህንን ኣስመልክቶ ሲያስተምረን “መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ይነሣሉ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይነሣሉ›› ብሎ ኣሳውቆናል፡፡ ከዚህ አኳያ የሕይወትን ትንሣኤ የሚያገኝ  ያመነ፣ የተጠመቀና መልካም ስራን የሰራ እንጂ የተነሣው ሁሉ ኣለመሆኑ ግልጽ ነው፤ መነሣቱ ሁሉም የግድ ይነሣል፤ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ የሚጠብቀን ሕይወት በዚህ ዓለም በሕይወተ ሥጋ ሳለን በሰራነው ስራ የሚወሰን እንደሆነ ጌታችን በማያሻማ ሁኔታ ኣረጋግጦልናል፡፡

በዛሬው እለት ሚያዝያ 11 ቀን 2017 ዓ.ም በዕለተ  ቀዳም ሥዑር የገብረ ሰላመ በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በደማቅ ሁኔታ ተከበረ። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይም በፈጸመው የማዳን ሥራ ለዓለም ድኅነትን መስጠቱ የሚታወጅበት ታላቅ ሃይማኖታዊ በዓል ነው። በኖኅ ዘመን መጥቶ የነበረው ጥፋት ማብቃቱ ርግቧ ይዛ በመጣችው የወይራ ቅጠል እንደታወቀ ሁሉ በአዳም በደል ምክንያት በሰው ልጆች የውድቀት ዘመን ማብቃቱ የሚታወጅበት በዓል ሲሆን ርግቧ በአፏ ይዛ ለመጣችው ለምለም ቅጠል ምሳሌም ለምለም ቄጤማን በቅዱስ ፓትርያርኩ አማካኝነት ለካህናቱና ለምዕመናን የታደለ ሲሆን ለበዓሉ ያሬዳዊ ዜማውን የደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ሊቃውንት እና ሰንበት ት/ት ቤታችን ፍኖተ ብርሃን  አባላት ያሬዳዊ ወረብ ቀርቧል። በበዓሉ ላይ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ፣ብፁዕ አቡነ ሣሙኤል፣ እና ሌሎች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን  የማነ ዘመንፈስ ቅዱሰ እና ሌሎች የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ካህናት ፣ጀግኖች አርበኞች የሰ/ት/ቤት ተማሪዎችና ምእመናን ተገኝቸው በዓሉ ተከብሯል። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com