ar
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

الذهاب إلى القناة على Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

إظهار المزيد
2 754
المشتركون
-124 ساعات
+57 أيام
+4130 أيام
أرشيف المشاركات
''ሥርዓተ ማኅሌት ዘበዓለ ጰራቅሊጦስ'' በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
+6
''ሥርዓተ ማኅሌት ዘበዓለ ጰራቅሊጦስ''   በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ               ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

''ሥርዓተ ማኅሌት ዘበዓለ ጰራቅሊጦስ'' በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
+2
''ሥርዓተ ማኅሌት ዘበዓለ ጰራቅሊጦስ'' በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት

የጎፋ መካነ ሕያዋን ሰንበት ት/ቤት ለመቄዶንያ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ ! በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት በርቀት ከሚያስተምራቸው ተማሪዎች ያሰባሰበውን አንድ ሚሊየን አንድ መቶ ሰባ ሺህ ብር በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ቡራኬ ለመቄዶንያ መሥራች ለክቡር ዶክተር ብኒያም አስረክበዋል፡፡ በኢትዮጵያ ከሚገኙ አገር በቀል  ተቋማት መካከል  በግንባር ቀደምነት የሚጠቀሰው መቄዶኒያ  የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል  ከተቋቋመ ስምንት ዓመታትን  ባስቆጠረው በመቄዶኒያ ከ8,000 በላይ በተለያየ  ዕድሜ  ክልል  ውስጥ  የሚገኙ የተለያዩ ተረጂዎች ይገኙበታል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት “መቄዶንያ ለተቸገሩ ሰዎች የሚረዳ ትልቅ ተቋም ነው፡፡ መንግሥትም የማይችለውን ነው መቄዶንያ የያዘው፤ ለዚህ ተቋም ርዳታ የሚያደርጉ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ትልቅ ዋጋ ያገኛሉ፡፡ ሀብታቸውም ይባረክላቸዋል፡፡ እስከ አሁንም ርዳታ ላደረጉት ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል፡፡” ብለዋል፡፡ ቅዱስነታቸው አያይዘውም “በሀገራችን በተለያዩ ምክንያቶች ችግረኞች እየተበራከቱ በመሆኑ፤ የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት በኩል ለመቄዶንያ የምትችሉትን ርዳታ በመርዳታችሁ በረከት ታገኛላችሁ፤ብዙ ዋጋ ያስገኝላችኋል፤ይሄ በጎ ሥራችሁ ለሁሉም አርአያ በመሆኑ እግዚአብሔር ይባርካችሁ” በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡   የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሰብሳቢ ቀሲስ ዮናስ ኢሳይያስ እንደገለጹት “የጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት ከ6‚500 ተማሪዎች ይገኛሉ፡፡ ሰንበት ትምህርት ቤቱ መደበኛ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች አንዱ በርቀት ትምህርት ማስተማር ነው፡፡ በርቀት ትምህርት የሚማሩት በተሠማሩበት የሥራ ዘርፍ ክርስትናቸውን እንዲገልጹ ማድረግ” መሆኑን አስረድተዋል፡፡ አያይዘውም “በቤተክርስቲያን ተቋማት በርካታ ወጣቶች ይገኛሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ከመንፈሳዊ ትምህርቷ በተጓዳኝ በማኅበራዊ ጉዳይ ተሳታፊ እንዲሆኑ መቄዶንያ አረጋውያንን እንዲረዱ እያደረግን ነው፤ በዚህም መሠረት የሰንበት ትቤቱ የርቀት ትምህርት አስተባባሪዎች ተወካዮች ቅዱስነትዎ ጋር መጥተን ለመቄዶንያም የበኩላችንን አስተዋጽኦ እንድናደርግ አባታዊ በረከትዎን ለመቀበል መጥተናል” ሲሉ ገልጸዋል፡፡ “የካቴድራሉ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ አባ ኃይለ ኢየሱስ ተመስገን እንዳብራሩት “የሰንበት ትምህርት ቤቱ ወጣቶች በርካታ ሥራዎችን እየሠሩ እንደሚገኙ” ገልጸዋል፡፡ በሰንበት ትምህርት ቤቱ ባዘጋጀው የርቀት ትምህርት በርካታ ተማሪዎች ከተለያዩ ቦታዎች መጥተው ይማራሉ፡፡ ዶክተር ቢኒያም በሀገራችን ላይ በየመንገዱ ወድቀው የሚኖሩ ወገኖቻችንን እያነሡ የጀመሩት ራዕይ ተስፋፍቶ አሁን ፍሬ አፍርቷል፡፡ እኛም በበኩላችን ይህን ለምን አንደግፍም ብለን  ካቴድራሉ፣ሰንበት ት/ቤቱ በማስተባበር የገንዘብ ድጋፍ ተደርጓል፤ቅዱስነትዎ ለዶክተር ቢኒያም እንዲሰጡልን” ነው የመጣነው ብለዋል፡፡ አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና በመሰብሰብ “ሰው ለመርዳት ሰው ብቻ መሆን በቂ ነው” የሚል መርህ አንግቦ ከተነሣ ዓመታት ያስቆጠረው መቄዶንያ፤ በእነዚህ ዓመታትም በርካታ አረጋውያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና ሕይወት መታደግ ችሏል፡፡ የተቋሙ መሥራች ክቡር ዶክተር ቢኒያም እንደገለጹት “መቄዶንያ ምንም ገቢ የለውም፡፡ በቀን ከ 2.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የሚያወጣ ማዕከከል ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት  በ46 ከተሞች ላይ ከጎዳና ሰዎች ተነሥተው እየተረዱ ይገኛሉ፡፡” ብለዋል፡፡   “ዛሬ የአንድ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት 1.2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ያደረገው ሌሎችም አብያተ ክርስቲያናትና ሰንበት ት/ቤቶች ተመሳሳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ የሚያነሣሣ ነው፡፡ ሌሎችም ይህን አርአያ አድርገው ተመሳሳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ነው፡፡ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናትም የረዱን አሉ፤ ሌሎችም  ድጋፍ በማድረግ እንዲሳተፉ ቢያደርጉ፤ ድጋፍ የሚያደስፈልጋቸውን እነዚህ መርዳት ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ስለሚያሰጥ ሁሉም ኅብረተሰብ እንዲሳተፍ ቅዱስነትዎ መመሪያ ለሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ቢያስተልላልፉልን” ብለዋል፡፡ ©️ EOTCTV ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

በዓለ ጰራቅሊጦስ '' የቤተክርስቲያን የልደት ቀን '' በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
በዓለ ጰራቅሊጦስ '' የቤተክርስቲያን የልደት ቀን '' በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

በዓለ ጰራቅሊጦስ '' የቤተክርስቲያን የልደት ቀን '' በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።

#መልካም_ዜና በዛሬው እለት በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ የቅዱስ ሚካኤል ማኅበር ልጆች መካከል የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ እስክንድር ወ/ማርያም እና ወንድማችን ሄሎም ተስፋዬ ከባለቤቱ አርቲስት አዚዛ አህመድና ልጆቻቸው ጋር በሰንበት ት/ቤታችን ጽ/ቤት በመገኘት ለሚዲያ ክፍሉ አገልግሎት ማጠናከሪያ የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በድጋፍ አስረክበውናል። በዕለቱ የሰንበት ት/ቤታችን ሰብሳቢ መ/ር ተስፋዬ ተሾመ እና ምክትል ሰብሳቢ ወጣት ካሳሁን እሸቱ እንዲሁም ከስራ አመራር የሚዲያ ክፍሉ ሰብሳቢ ወጣት አፈወርቅ በላቸው ፣የሕጻናት ክፍል ሰብሳቢ ኢ/ር ዳዊት አበበ ፣ እና የሚዲያ ክፍል አባላት ተገኝተው ተረክበዋል።በቀጣይ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቃል የገቡ ሲሆን በተጨማሪም የማኅበሩ አባላት በሆሣዕና አገልግሎት ላይ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦም የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል። በተያያዘ መልካም ዜና የሰንበት ት/ት ቤታችን አባል በሆኑት ዲያቆን ዳንኤል ተክሌ ለሚዲያ ክፍሉ ፕሮጀክተር  ገቢ ተደርጎለታል እንዲሁም በሰሜን አሜሪካ የሚገኙት የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል አቶ ብሩክ ገ/ሥላሴ ከነባለቤታቸው ለሚዲያ ክፍሉ ማጠናከሪያ እንዲሆን የ10,000# (አስር ሺህ ብር) ድጋፍ አድርገውልናል ። ድጋፍ ያደረጉልን ሁሉንም አምላከ ቅዱስ ሚካኤል በነፍስ በስጋ ይጠብቅልን በማለት የሰንበት ት/ቤታችን ሰብሳቢ ምስጋና አቅርበዋል። በመጨረሻም የሰንበት ትምህርት ቤታችን ሚዲያ ክፍል ራሱን ለማደራጀትና ለማሳደግ እያደረገ ላለው የስቱዲዮ ግንባታ እንቅስቃሴ ሁላችንም በገንዘብ ወይም የማቴሪያል ድጋፍ በማድረግ የድርሻችንን አበርክቶ ልንወጣ ይገባል።    የኢ/ያ ንግድ ባንክ - 1000555650594 (media/ሚዲያ) በማለት የበረከቱ ተሳታፊ ይሁኑ እግዚአብሔር ይስጥልን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የእግዚአብሔር ቤት በእግዚአብሔር መንገድ መመራት እንደሚኖርበት አስገነዘቡ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተመረጡት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የአቀባበል መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት የእግዚአብሔር ቤት በእግዚአብሔር መንገድ ብቻ መመራት ይኖርበታል ብለዋል። የእግዚአብሔር ቤት በአምልኮተ እግዚአብሔርና በጸሎት ከመራነው ሁሉም ነገር ቀና ይሆናል ዓለማዊ መንገድ ከተደባለቀበት ግን አደገኛ ነው "ጋሻና ቅል ለየቅሉ ይሰለል።" እንደሚባለው መንፈሳዊነትና ፖለቲካን ለይተን መጎዝ ይኖርብናል።ብለዋል። አያይዘውም ለአዲሶቹ አመራሮች የሁላችንም ድጋፍና ጸሎት ያስፈልጋቸዋል።ስለሆነም ሁላችንም እንደ አንድ ቃል ተናጋሪና እንደ አንድ ልብ መካሪ በመሆን በሀቅና በቅንነት ልናግዛቸው ይገባል ብለዋል።ይህችን ታላቅ ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔራዊ መንገድ ሰርተን ካልጠበቅናት አደጋው የከፋ ይሆናል። ያሉት ቅዱስነታቸው ይህን በመገንዘብም ቤተክርስቲያናችንን በቀና መንገድና በመንፈሳዊነት መምራት ይኖርብናል ብለዋል። ሰላም የሚገኘው ከሰላማዊቷ ቤተክርስቲያን ነው ያሉት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተክርስቲያን ያልተገኘ ሰላም ከየት ሊገኝ ይችላል? የተሰጠን ኃላፊነት መንፈሳዊ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባትም ለአገራችን ሰላም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ለማበርከት በትጋት መስራት ይኖርብናል ብለዋል። ጥላቻ፣ዘረኝነት፣ጎጠኝነት አይጠቅምም እኛ መንፈሳዊያን ነን እግዚአብሔር ሲፈጥረን ንፁሃን አድርጎ ነው የፈጠረን እኛ በራሳችን መንገድ በመጓችን ነው ወርደን ተጠባቂዎች የሆነው። ያሉት ቅዱስነታቸው እኛ ጠባቂዎች መሆናችንን አውቀን የጠባቂነት ሚናችንን ከጥላቻና ከዘረኝነት በራቀ መንገድ በመፈጸም ለሰይጣን ሳይሆን ለእግዚአብሔር ተመችተን መገኘት አለብን ብለዋል። በመጨረሻም አሁን ለተመረጡት አባቶች እግዚአብሔር አምላክ ጽናትንና ብርታትን ይስጥልን።የአገልግሎት ጊዜአቸውን ጨርሰው የተሰናበቱትን አባቶችም እግዚአብሔር አምላክ በቸርነቱ ይጠብቅልን ሥራዎቻቸውን ሁሉ ይባርክ በማለት መርሐ ግብሩን በጸሎት አጠናቀዋል። © የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

        እንኳን ደስ ያላችሁ!! በዛሬው ዕለት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የፍኖት መረዳጃ ዕድር በልዑል እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ መልዓከ ሰላም ቀሲስ እስክንድር ወልደማሪያም ባሉበት ምስረታው እውን ሆኖል። በዕለቱ በርካታ  የዕድሩ መስራች አባላት ተገኝተው የመተዳደሪያ ደንብ ላይ ውይይትና ገለጻ በአቶ አንዱአምላክ ፈቃዱ ቀርቦ ውይይት ከተደረገ በኋላ እድሩን ለሁለት ዓመት የሚያገለግሉ አባላትን መርጧል ። የሰንበት ት/ቤታችን ምክትል  ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ካሳሁን እሸቱ የዕድሩ መመስረት ለዘመናት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረና አሁን ግን አምላከ ሚካኤል ፈቅዶ እውን በመሆኑ የተሰማቸውን ደስታ የገለጹ ሲሆን። ሰንበት ትምህርት ቤቱ አቅሙ በፈቀደ መጠን ከእድሩ ጎን እንደሚቆም ተናግረዋል በመጨረሻም የእድሩ መስራችና አባል የሆኑት መልአከ ሰላም ቀሲስ እስክንድር እድሩ በመመስረቱ የተሰማቸውን ደስታ ከገለጹ በኋላ እድሩን ለመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ለአባላቱ ቃል ገብተዋል። በመጨረሻም አዲስ ለተመረጡት የዕድሩ የኮሚቴ አባላት ጸሎትና ቡራኬ በመስጠት ኮሚቴው የተጣለበትን ኃላፊነት ተግቶ እንዲወጣ አባታዊ ምክራቸውን አስተላልፈዋል። መስራች አባላትም በዕለቱ የቤተሰብ ቅጽ የተሞላ ሲሆን የእድሩን መተዳደሪያ ደንብና የዕድር ደብተር በመውሰድ ተጠናቋል!! እግዚአብሔር ቀሪውንም ያስፈጽመን🙏🙏