uz
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Ko'proq ko'rsatish
2 632
Obunachilar
+124 soatlar
+227 kunlar
+5430 kunlar
Postlar arxiv
ቅድስት ሥላሴ ሐምሌ ሰባት በዚች ቀን ሥሉስ ቅዱስ በአብርሃም ቤት የተገለጡበት ነው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና  በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡ አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የወረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡ ለዚህም ነው አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ ዘፍ 18፥1 ፣ ሮሜ 4፥3፡፡ ቀትር ሰዓት ላይ በድንኳኑ ደጅ ተቀምጦ እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር ታየው ተነጋገረው፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ ዐይኑን አራምዶ በተመለከተ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች ከበላዩ ባለ ተራራ ላይ ቆመው አያቸው፣ ወደ እርሱም ሲወርዱ አይቶ ፈጥኖ ሄዶ ከሰገደላቸው በኋላ ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ ከዚህችም ዛፍ ስር እረፉ..›› እያለ በትሕትና በመጋበዝ ወደ ድንኳኑ አስገብቶ በሚገባ ጋበዛቸው፡፡ ‹‹በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ›› ብሎ አንድነታቸውን፣ ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ›› ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አብርሃም ሚስቱ ሳራን ሦስት መስፈሪያ የተሰቀለ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ ለውሺውም እንጎቻም አድርጊ በማለት የአንድነት ሦስትነት ምስጢርን ገልጧል። ያቺ ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ ሉቃ 1፡35 እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም እና ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው አብዝቶ ለመነላቸው፡፡ የዓለም ገዢ ሥሉስ ቅዱስ በወዳጃቸው በአብርሃም ቤት እንደገቡ በእኛም ቤት ይግቡ በምግባር በሃይማኖት ሆነን ጸንተን እናገለግል ዘንድ በረድኤት ይጠብቁን አሜን።   ኦ ሥሉስ ቅዱስ ተመስገን   ዓለማትን የፈጠርህ እግዚአብሔር ተመስገን   እንኳን ለአብርሃሙ ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ከሐምሌ 22–28/2016 ዓ.ም የጾም እና የጸሎተ ምህላ እንዲደረግ አወጀ። ዛሬ ሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓት
+1
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ  ሲኖዶስ ከሐምሌ 22–28/2016 ዓ.ም  የጾም እና የጸሎተ ምህላ እንዲደረግ አወጀ። ዛሬ ሐምሌ 5 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  በተሰጠው መግለጫ መሰረት የገዳማውያን አንድነት ህብረት በቀረበው ጥያቄ መነሻ መሰረት  ከሐምሌ 22–28/2016 ዓ. ም  ለ7 ቀናት መላው ኦርቶዶክሳዊ በጾምና በጸሎት በምህላ ሱባኤ እንዲያዝ መታወጁን ቋሚ ሲኖዶስ መልእክቱን አስተላልፏል ። በመግለጫውም በዚህ ጊዜ ውሎ ማደር ፣ ወጥቶ መግባት በአንድ አንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል እና የሚለምኑትን ሁሉ የሚሰማ እግዚአብሔር መተላለፋችንን ይቅር እንዲለን ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም ለቤተክርስቲያናችን ፍቅርና አንድነትን ለህዝባችን ደህንነትን እንዲሰጥልን በአንድነት ገዳማት ህብረት በጠየቀው መነሻ ነት  በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ  ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን በጾም ፣ በጸሎት በምህላ  እንዲያሳልፉ  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ጥሪ አስተላልፈዋል።   ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ነገ ቅዳሜ መደበኛ ትምህርት የሚሰጥ ስለሆነ ሐምሌ06/11/2016 ዓ.ም የሚቀጥል ስለሆነ አባላት በሰዓታችሁ እንድትገኙ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

በዛሬው እለት የቅድስት ስላሴ ዩኒቨርሲቲ ሲያስተምራቸው የቆዩትን ተማሪዎች ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
+3
በዛሬው እለት የቅድስት ስላሴ ዩኒቨርሲቲ ሲያስተምራቸው የቆዩትን ተማሪዎች ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እና ሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ያስመረቀ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት የሆኑት ወንድማችን አንድአምላክ ፈቃዱ እና ፈቃዱ ኪሮስ ከቅድስት ስላሴ ዩኒቨርሲቲ በመመረቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ። የፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ምስጢር ትንሳኤ ሙታን)በሚል ርዕስ በመ/ር ዲ/ን ሽመልስ መልአክ ሊሰጥ አንድ ቀን ቀረው አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን
መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ምስጢር ትንሳኤ ሙታን)በሚል ርዕስ በመ/ር ዲ/ን ሽመልስ መልአክ ሊሰጥ አንድ ቀን ቀረው አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን ትምህርት ይማሩ  በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

ሰንበት ትምህርት ቤት 1. የመንፈሳዊ ሕይወት መማሪያ ቤታችን 2. የመንፈሳዊ እውቀት ምንጫችን 3. የነፍስና የስጋ በረከት ማግኛችን 4. የአገልግሎት ሕይወት መነሻችን 5. የንግግርና የተግባቦት ችሎ
+1
ሰንበት ትምህርት ቤት 1. የመንፈሳዊ ሕይወት መማሪያ ቤታችን 2. የመንፈሳዊ እውቀት ምንጫችን 3. የነፍስና የስጋ በረከት ማግኛችን 4. የአገልግሎት ሕይወት መነሻችን 5. የንግግርና የተግባቦት ችሎታ ማሰልጠኛችን 6. የሕይወትና የስራ አመራር ክህሎት መማሪያችን . ........ ተነግሮ የማያልቅ ብዙ ጠቀሜታዎችን ያገኘንባትና የምናገኝባት በቤተክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ያለች የወጣቶች እና የሕጻናት መሰብሰብያ ማዕከል ነች። በዚህች የቤተክርስቲያን ተቋም ስር ከልጅነት ጀምሮ መማርና በውስጧ ማደግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው። ወላጆች ልጆቻችሁን ወደ ሰንበት ት/ቤት በመላክና በማስመዝገብ የነገውን በጎ ትውልድ  ዛሬ እንፍጠር ፈሪሐ እግዚአብሔርን ይማሩ ይወቁ እናንተም የድርሻችሁን ተወጡ ። ለዚህም በጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት የክረምት ወቅትን በመጠቀም ሕጻናትን፣ ማዕከላውያንን እና ወጣቶችን ተቀብለን ለማስተማር በዝግጅት ላይ እንገኛለን። እርስዎም ወጣቶችና ወላጆችም በመምጣት ተመዝግበው መንፈሳዊ ትምህርቶችን እየተማሩ የነፍስ ስንቅ እንዲሰንቁ በአክብሮት ጠርተኖታል።             የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የስራ መደብ:- ሴክሬተሪ እና ሂሳብ ሰራተኛ የት/ደ:- በአካውንቲንግ የተመረቀች የስራ ልምድ :- በስራው ላይ ልምድ ያላት ፆታ:- ሴት ብዛት :- ሴክረተሪ 1 ሂሳብ ሰራተኛ 1 ደሞዝ:- በስምምነት ማሳሰቢያ:- የሰንበት ት/ት ቤታችን አባላት የሆናችሁና የስራ ዕድል ሲመጣልን እንድናገናኝዎ የምትፈልጉ ወይም ይህ መረጃ የማይደርሳቸው ግን የሚያስፈልጋቸውን አባላት የምታውቁ ከታች በተቀመጡ ስልኮች በመደወል እንዲያስመዘግቡ በትህትና እንጠይቃለን። 093114-44-44 ሙሉጌታ ሰማን 0966-25-87-38 ዮሐንስ ትዳሩ 0912-48-65-04 ታምሩ ማሬ             የበጎ አድራት ክፍል ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ምስጢር ትንሳኤ ሙታን)በሚል ርዕስ በመ/ር ዲ/ን ሽመልስ መልአክ ሊሰጥ አንድ ቀን ቀረው አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን
መደበኛ የቅዳሜ ትምህርት (ምስጢር ትንሳኤ ሙታን)በሚል ርዕስ በመ/ር ዲ/ን ሽመልስ መልአክ ሊሰጥ አንድ ቀን ቀረው አባላት ትምህርት መማሯን ማረጋገጫ ከሰ/ት/ቤቱ የሚፈልጉ ከሆነ ተከታታይ የሚሰጠውን ትምህርት ይማሩ  በጊዜ በመገኘት የድርሻችንን እንወጣ። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc

ለውድ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ ከዛሬ ማክሰኞ 18/10/2016 ጀምሮ እስከ ሐሙስ  20/10/2016 ድረስ ለሶስት ቀናት እህታችን ሳምራዊት ቤት የማጽናኛ መርሐግብር የሚከናወን በመሆኑ በመኖሪያ ቤታቸው በማጽናኛ መርሐግብሩ ላይ እንድትገኙ እንድታጽናኑ ይሁን።                         ፍኖተ ብርሃን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ትምህርት ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን ትዕግስት አማረ አያት በስጋ ድካም ስላረፉ መኖሪያ ቤታቸው ልደታ ኮንዶሚኒየም በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የእናታችንን ነፍስ ይማርልን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

‛‛መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?’’ እህታችን ሳምሪ ዘመንሽን በሙሉ ሳትደክሚ ስታገለግይው የኖርሽው አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ነፍስሽን በክብር ይቀበል
‛‛መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው?’’  እህታችን ሳምሪ ዘመንሽን በሙሉ ሳትደክሚ ስታገለግይው የኖርሽው አምላከ ቅዱስ ሚካኤል ነፍስሽን በክብር ይቀበልልን ነገ 4:00  አባላት ጎላ ተገኙ የክብር ልብስ ውሰዱ ስታገለግል የኖረችዋን እህታችንን በክብር  እንሸኛት      ሞት አልተወደድክም በጣም ተጠልተሃል      ትንሹም ትልቁም ያርቀው ይልሃል ነፍስሽን  ይማርልን በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ አጠገብ ያስቀምጥልን። ቸርና መሐሪ የሆነ አምላካችን ለእህታችን ነፍስ ዘለዓለማዊ እረፍትን ይስጥልን።             ፍኖተ ብርሃን ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ዜና ሐዘን ለብዙ ዘመናት በሰንበት ትምህርት ቤታችን ከአባልነት ጀምሮ በተለያዩ ክፍላት ኃላፊነት እንዲሁም በመዝሙር ክፍል በጥንካሬ ስታገለግል የነበረችው እህታችን ሣምራዊት አለሙ አርፋለች። ልባችን
       ዜና ሐዘን ለብዙ ዘመናት በሰንበት ትምህርት ቤታችን ከአባልነት ጀምሮ በተለያዩ ክፍላት ኃላፊነት እንዲሁም በመዝሙር ክፍል በጥንካሬ ስታገለግል የነበረችው እህታችን ሣምራዊት አለሙ አርፋለች። ልባችን ተሰብሯል  ስርዓተ ቀብሯ ነገ ማክሰኞ በ18/10/2016 ከቀኑ 5:00 በቀጨኔ መድኀኔዓለም ቤ/ክ ይፈጸማል አባላት ሁላችሁ ነገ 4:00 ተገኙ የክብር ልብስ ውሰዱ ስታገለግል የኖረችዋን እህታችንን በክብር  እንሸኛት።ነፍስሽን  ይማርልን በቅዱሳኑ እቅፍ ያስቀምጥልን። ማርያም ሐዘነ ልቡና ታቀልል ማርያም የልብን ሐዘን ታቀላለች ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ታላቁ የጰራቅሊጦስ በዓል በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል 16/10/2016
+9
ታላቁ የጰራቅሊጦስ በዓል በደብራችን ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት እና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል 16/10/2016