uz
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

Kanalga Telegram’da o‘tish

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

Ko'proq ko'rsatish
2 617
Obunachilar
+724 soatlar
+207 kunlar
+3530 kunlar
Postlar arxiv
ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ ሀገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው።  ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው።  ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።  መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።  በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው። ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።  ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው።  ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።  ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።  ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው። እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ!  ከቅዱስ ገብርኤል  ከሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስናከእናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በረከት ያሳድርብን

ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ ሐምሌ 19 በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ ሀገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው።  ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው።  ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።  መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።  በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው። ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።  ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው።  ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።  ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።  ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው። እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ!  ከቅዱስ ገብርኤል  ከሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስናከእናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በረከት ያሳድርብን

''ነገረ ማርያም'' የመጨረሻ ክፍል በመ/ር ኢዮብ በቀለ የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 19/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድ
''ነገረ ማርያም''                   የመጨረሻ ክፍል     በመ/ር ኢዮብ በቀለ የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር  የፊታችን ቅዳሜ  ሐምሌ 19/2017 ዓ.ም ከምሽቱ  11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ  ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ። የቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com

ለፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት አባላት በሙሉ የእጩ ጥቆማ ቀን ነገ ይጠናቀቃል። ===================== በቀጣይ የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ሊመሩ የሚችሉ የስራ አመራር አባላትን ለማስመረጥ የአስመራጭ ኮሚቴ መካሄዱ የሚታወስ ነው። ለተመረጠው አስመራጭ ኮሚቴ ከዚህ በታች በተቀመጠው አማራጭ ማለትም በSMS 0986122299 በGoogleform እና በአካል በወረቀት ከሐምሌ 7-18 የእጩ ጥቆማ ስለሚካሄድ ለሰንበት ትምህርት ቤታችን ያገለግላሉ ብለው የሚያስቡትን እጩ እንድትጠቁሙን በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም አደራ እንላለን ። ከዚህ በታች ባለው link ባሉበት ሆነው እጩዎችን ይጠቁሙ👇👇👇👇👇 https://forms.gle/YjBeQFN24ECMyHcKA

ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በተደረገ ጉባዔ የቀጣይ የሰንበት ትምህርት ቤታችንን ሊመሩ የሚችሉ የስራ አመራር አባላትን ለማስመረጥ የአስመራጭ ኮሚቴ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን የተመረጠውም አስመራጭ ኮሚቴ ወደ ስራ የገባ ሲሆን ከዚህ በታች በተቀመጠው አማራጭ ማለትም በSMS 0986122299 በGoogleform እና በአካል በወረቀት ከሐምሌ 7-18 የእጩ ጥቆማ ስለሚካሄድ ለሰንበት ትምህርት ቤታችን ያገለግላሉ ብለው የሚያስቡትን እጩ እንድትጠቁሙን በአምላከ ቅዱስ ሚካኤል ስም አደራ እንላለን ። ከዚህ በታች ባለው link ባሉበት ሆነው እጩዎችን ይጠቁሙ👇👇👇👇👇 https://forms.gle/YjBeQFN24ECMyHcKA

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ልዩ ጉባኤ ለባለትዳር አባላት በሙሉ ======================= ''ኑ የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር '' ታላላቆቻችንን የምናከብ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።         ልዩ ጉባኤ ለባለትዳር  አባላት በሙሉ          ======================= ''ኑ የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር '' ታላላቆቻችንን የምናከብርበት ታናናሾቻችን ልምድ የሚያገኙበት ልዩ ዕለት ሁሉም ሊቀርበት የማይገባ ልዩ ጉባኤ     የፊታችን እሑድ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም                  ከ5:30 ጀምሮ                 የባለትዳር ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ልዩ ጉባኤ ለባለትዳር አባላት በሙሉ ~~~ ''ኑ የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር '' ታላላቆቻችንን የምናከብርበት ታናናሾቻችን ልምድ የሚያገ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።         ልዩ ጉባኤ ለባለትዳር  አባላት በሙሉ          ~~~ ''ኑ የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር '' ታላላቆቻችንን የምናከብርበት ታናናሾቻችን ልምድ የሚያገኙበት ልዩ ዕለት ሁሉም ሊቀርበት የማይገባ ልዩ ጉባኤ     የፊታችን እሑድ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም                  ከ5:30 ጀምሮ                 የባለትዳር ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ልዩ የባለትዳር አባላት ጉባኤ ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ''ኑ የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር '' ታላላቆቻችንን የምናከብርበት ታና
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።         ልዩ የባለትዳር  አባላት ጉባኤ          ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ''ኑ የጋብቻ በዓላችንን በጋራ እናክብር '' ታላላቆቻችንን የምናከብርበት ታናናሾቻችን ልምድ የሚያገኙበት ልዩ ዕለት ሁሉም ሊቀርበት የማይገባ ልዩ ጉባኤ       የፊታችን እሑድ ሐምሌ 20/2017 ዓ.ም                  ከ5:30 ጀምሮ                 የባለትዳር ጉባኤ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12 የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1 የፌስቡክ ገጻችን  https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc የዌብሳይት ገጻችን  https://finotebirhan.com