cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

የኦርቶዶክስ ገድላትና ቀኖናዎች ሲፈተሹ

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
371
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
Ma'lumot yo'q30 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Photo unavailableShow in Telegram
የሚያስረዳን አለ? በሃይማኖተ አበው ገጽ 393 ዘዩሐንስ ም 90 ቁ 25 መሠረት አምላካችሁ ኢየሱስ እድሜው 30 አመት እስኪሆነው ድረስ ጡት ጠብቷል ብላችሁ ነው የምታምኑት? 30 እስኪሞላው ጡት በመጥባት ነበር ያደገው? ለምን? https://t.me/Orthodox_Critic
Hammasini ko'rsatish...
ሰውን በእሳት አቃጥሎ የመግደል ህግ ካሁን ቀደም በዚሁ ቻናላችን 'ኦርቶዶክሳዊ የመግደል ህግና ስርዓት' በሚል ርዕስ ኦርቶዶክስ ጠላት ነው ያለችውን አካል የደገፈና የተባበረ ሰውን መግደል እንደሚገባ መደንገጓን በማስረጃ እንዳስነበብናችሁ ይታወቃል። ለማስታወስ ሊንኩን ተጭነው ማንበብ ይችላሉ። https://t.me/Orthodox_Critic/93 እነሆ አሁን ደግሞ በዛው ተመሳሳይ ቅዱስ የኦርቶዶክስ ህግና ሥርዓት መጽሐፍ ላይ የሰው ልጅ በእሳት ተቃጥሎ መገደል እንደሚገባው የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የደነገገችውን ህግ አብረን እንመለከታለን። ኦርቶዶክስ በ14ኛው ክ/ዘመን እንዳዘጋጀችው በሚነገርላት የፍትሐ ነገሥስ መጽሐፏ የጌታቸውን ህይወት ሊያጠፉ የወደዱ ባሮች በእሳት ተቃጥለው መገደል እንዳለባቸው ትደነግጋለች። "የጌታቸውን ህይወት ሊያጠፉ የሚወዱ ባሮችም ወደ እሳት ይጣሉ።" ፍትሐ ነገሥት 47፥1704 ጥያቄዎቻችን 1) ጠላትን ሳይሆን ጠላትን የተባበረን ከመግደል እስከ ባርያን በእሳት አቃጥሎ መግደል በቅዱሳት መጽሐፍቷ የምትደነግግ ሃይማኖት ስለምንድነው ሁሌ እስልምናን እንደ ጭራቅ አቅርባ ራሷን ስለ ግድያ ሥርዓት ምንም እንደማታስተምር ሁሌ በቤተክርስትያን ሌላ እየሰበከች ይሄን እውነት የምትደብቀው? 2) ፍትሐ ነገሥት የተዘጋጀው ከ14ኛው ክ/ዘመን በኋላ ከሆነና በፍትኃ ነገሥት 'ባርያን' አስመልክቶ ህግ ከተደነገገ፥ በክርስትናው አለም ከ14ኛው ክ/ዘመን ጀምሮም ቢሆን Human Slavery እውቅና የተሰጠው መለኮታዊ መተዳደርያ ህግም የተቀመጠለት ነበር ማለት አይቻልም? 3) የሰውን ልጅ ስለጥፋቱ በእሳት አቃጥላችሁ ግደሉት የተባለው የባርያ ነፍስ ከሰው ስለማይቆጠር ነው ሌላ አይነት የአገዳደል መንገድ ያልተገለጸው ወይስ በኦርቶዶክስ የሰውን ነፍስ በእሳት አቃጥሎ መግደል የተለመደ Normal ነገር ስለሆነ ነው? https://t.me/Orthodox_Critic
Hammasini ko'rsatish...
የኦርቶዶክስ ገድላትና ቀኖናዎች ሲፈተሹ

ኦርቶዶክሳዊ የመግደል ህግና ሥርዓት ብዙ ጊዜ ኦርቶዶክሳውያን ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ጋዜጠኞችና በርካታ የኦርቶዶክስ አማኞች በአማራ ክልል በተለይ በጎንደርና በጎጃም አውራጃዎች በቀጥታና በግልጽ ለግድያና ለጭፍጨፋ እየሰበኩ በተግባርም ሙስሊሙን ሲገድሉና ሲጨፈጭፉት፤ ለምን እንደሆነ ባላውቅም የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የማያዘውንና የማያስተምረውን አስተምህሮ ጥቂት ጽንፈኞች ፈጸሙት፣ እስላም ጠሎች አደረጉት፣ ምንትሴ ቅብርጥሴ እየተባለ በየሚድያው ሲደጋገም የምንሰማው የሃሰት ወሬና መሸፋፈኛን ገንዘባችን አድርገን ይዘነዋል። ግን ለምን? እውነቱን ልንገርህ? ይህ ሁሉ እልም ያለ ቅጥፈት ነው! ቢመርህም ዋጠው ሙስሊሙን የሚጨፈጭፉና የሚገድሉት አካላት ጥቂት ጽንፈኞች ሳይሆኑ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ የህግና ስርአት መጽሐፍ የሆነውን የፍትሐ ነገሥትን ህግ አምነውበት በትክክል ተግባራዊ የሚያደርጉ ትክክለኛ ኦርቶዶክስን የሚወክሉ አማኞችና ምዕመነ ኦርቶዶክስ ብቻ ናቸው! ለመሆኑ ፍትሐ ነገሥት ምን ይላል? በፍትሐ ነገሥት ህግ መሠረት የኦሮቶዶክስ ጠላት ተብሎ የሚታሰበውን ለምሳሌ መንግስት ቢሆን፣ ወይም ኦሮሞ ቢሆን፣ ወይም ጴንጤ ቢሆን ወይም ራሱ ሙስሊም ቢሆን እንኳ ከነዚህ አካላት ጎን የቆመ፣ ቤቱ ደብቆ የመገበና የተከላከለ፣ ለነዚህ አካላት መሳርያም ሆነ መጓጓዣ የሸጠና በማንኛውም መልኩ የተባበረ ሰው #እንዲገደል ከኦርቶዶክስ ቅዱሳት አዋልድ መጽሐፍት መካከል የህግና ሥርዓት መጽሐፍ የሆነው የፍትሐ ነገሥት መጽሐፍ በአንቀጽ 47 ቁጥር 1706 ላይ ይደነግጋል። (ማስረጃዎቹ ከዚህ ጽሑፍ ጋር በምስል ተያይዘው ቀርበዋል ይመልከቷቸው።) ልብ በል ጠላትን ስለመግደል ሳይሆን ከዛ አልፈው ጠላትን የተባበረን በራሱ ጠላት ያልሆነን ስለመግደል ነው ቅዱስ መጽሐፋቸው እያወራ ያለው! ታድያ ወዳጄ፥ የትኞቹን ጥቂት ጽንፈኞች ነው…

Repost from Eliyah Mahmoud
Hammasini ko'rsatish...
religion and phylosophy

ሹብሃ (2) ኢየሱስ ተወለደ ወይስ ተፈጠረ? t.me/religionandphylosophytogether

https://bit.ly/religionandphylosophy

ሰብስክራይብ ማድረጋችኹን አትርሱ

አምልኮተ-ማሪያም 2 ከጥንት ዘመን ጀምሮ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ማሪያምን በግልጽ እና በድብቅ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚያመልኳት የክርስትና ቡድኖች የሉምን ? እስኪ በዐቂዳ (Creed) መፅሐፍቶቻቸው ላይ የተቀመጠውን እውነታ እንመልከት። بأي شيء يجب أن نظهر عبادتنا لمريم العذراء يجب علينا أن نظهر عبادتنا لسيدتنا مريم العذراء بأن نكثر من دعائها ونعيد أعيادها بالبر والتقوى ونسعى في الإقتداء بفضائلها ‟በሁሉም ነገር ለድንግል ማሪያም ያለንን አምልኮት ግልጽ ማድረግ ይኖርብናል። እመቤታችን ድንግል ማሪያምን ማምላካችንን ገሃድ ማውጣት አለብን። ልመናዋን በማብዛት፣ በዓላቶቿን በጽድቅና ቅድስና ለማሳለፍና እርሷን ለመምሰል እንትጋ። [📔Catechism of the Christian: Dominican Fathers (التعليم المسيحي) Page 183] እንደምታዩት ነው ! በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውስጥ ለማሪያም ከእግዚአብሔር ባልተናነሰ መልኩ አምልኮ ይፈፀማል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶም ከዚህ ያልተለየ ነገር ነው የምናገኘው። እንደሚሰግዱላት፣ እንደሚገዙአት እና ለአምላክ የሚቀርበውን የአምልኮ መስዋዕት ለእርሷ እንደሚሰዉ እንዲህ በማለት ይናገራሉ:- ‟...ለአንቺም የምስጋና እጅ መንሻን አቀርባለሁ፣ በመፍራት እገዛልሻለሁ፣ በመስገድም እጅ እነሣሻለሁ፣ የአምልኮ መሥዋዕትንም ለአንቺ እሠዋለሁ...” — እንዚራ ስብሐት ምዕራፍ 12 ቁጥር 98 አላህ ከማህጸን የወጡ ፍጡራንን ከማምለክ ይጠብቀን። ጌታ አምላካችን ለእነዚህ ወገኖቻችንም ልቦና ይስጣቸው። --------------------------------------------- ®Sαlαh Responds ✍️ ▸ t.me/mahircomp123
Hammasini ko'rsatish...
🎯Sαlαh Responds

ይህ ቻናል ሙስሊም ባልሆኑ አካለት እሥልምና ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች ንፅፅራዊ ምላሾችን የሚሰጥ ነው።

የህገ ዝንየት መሠረት በኦርቶዶክስ ዝንየት ማለት ባጭሩ ጸያፍ ህልም ማለት ሲሆን አንድ ወንድ ተኝቶ መጥፎ ህልም በማየትም ይሁን ባለማየት ሳያውቀው በእንቅልፉ የዘር ፈሳሹ ሲፈሰው ማለት ነው። ሙስሊሞች 'ኢህቲላም' የምንለው በእንግሊዝኛ wet dream የሚባለው ነው። የዝንየት ህግ በኦርቶዶክስ ቅዱሳት መጽሐፍት ታሪካዊ አመጣጥና መሠረት እንዳለው በተአምረ ማርያም መጽሐፍ ተአምር ቁጥር 58 ላይ ተጽፎ ይገኛል (የተአምር ቁጥሩ በአንዳንድ የተአምረ ማርያም መጽሐፍት እትሞች ሊለያይ ይችላል ለምሳሌ 41ኛ ተአምር ላይ የምታገኙባቸው ሁኔታዎች አሉ)። ታሪኩ ላይ በአንድ ንጉስ በወርቅ፣ በብርና በሀር የተጌጠች በውስጧ በጣም ብዙ ለታቦቱ ተብሎ ንጉሱ የሰጠው ገንዘብ የተቀመጠባት በማርያም ስም ተሰይማ የተሰራች ቤተክርስቲያን ነበረች(በመሠረቱ አንድን መንፈሳዊ የአምላክ ቤት በጣም ውድ በሆኑ ስጋዊ ጌጦችና ገንዘቦች ማስዋብ ይቻላልን? የሚለው ጥያቄ በውስጥ አዋቂነት ይያዝልኝ)። በቤተክርስትያኗ ውስጥ ያለው በጣም ብዙ ገንዘብ ከመሆኑም የተነሳ ንጉሱ የማያውቀውና በቤተክርስትያን ዙርያ ያሉ የክርስትያን ልጆች የማያውቁት አንድም ሰው ወደዚያች ቤተክርስቲያን አይገባም ነበር። የሚያገለግሏት ካህናት ሁሌ ቀንና ማታ እየተፈራረቁ ይጠብቋትም ነበር ይላል ታሪኩ። ቀጥሎም፥ አንድ ቀን በቤተክርስቲያን ቅጽር ውስጥ ሌሊቱን ሙሉ ሲጠብቁ ካደሩት ካህናት መካከል አንዱ ካህን ዝንየት(wet dream) መታውና የስጋው ዘር ፈሰሰው። ከዛ የማርያም ተአምር ሲገለጥ ሰውየውና በዙርያው ያሉ ወንድሞቹም ማናቸውም ሳያውቁ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ ዝንየት የያዘውን ሰው እንደተኛ ከቤተክርስቲያን ቅጽር 80 ክንድ ያህል አርቆ ወስዶ አሳደረው። ሰውዬውም አድሮ እስኪነቃ ድረስ የት እንዳደረና ዝንየት እንዳገኘው እንኳን አላወቀም ነበር ይላል ታሪኩ። ይህ ክስተት ከተከሰተ በኋላ ከንጉስና ከጳጳስ ዘንድ አዋጅ ነጋሪ ወጥቶ ማንም ቄስ፣ ዲያቆን፣ መነኩሴም ይሁን ምዕመን #ህልመ #ዝንየት #ያገኘው #ሰው #ወደ #ቤተክርስቲያን #ቅጽር #ጊቢ #የገባ #ባባታችን #በሐዋርያት #ቃል #የተወገዘ #ይሁን ተብሎ አዋጅ ተነገረ። በምስሉም በቀይ የተከበበው ቁጥር 21 ላይ እንደምትመለከቱት ከዚህ ገጠመኝ ቀን በኋላ ቢሆን እንጂ ከዚህ በፊት እስከዚች ክስተት ጊዜ ድረስ ይህ ህግና አስተምህሮ ማለትም ዝንየት እዳ መሆኑንና እስከዚህ ገጠመኝ ድረስ የዝንየት ህግና ስርአት ስለማይታወቅ ዝንየት አይቶ ቤተክርስቲያን ከመግባት የተቆጠበ ሰው ኖሮ እንደማያውቅ በጥቅሉ በኦርቶዶክስ ስርአት የዝንየት እዳና ህግ እንደማይታወቅ በግልጽ ይናገራል። ዝርዝሩን ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ላይ ተአምር ቁጥር 58 ወይም 41 ላይ ይመልከቱ። ጥያቄዎቻችን 1) ኢየሱስና ሐዋርያቱ ከኖሩበት 1ኛው ክ/ዘመን ጀምሮ ይህ የዝንየት ህግና ስርአት ምንም ሳይታወቅና ዝንየት የመታው ክርስትያን በተአምረ ማርያም የተጠቀሰው መቸቱ(መቼና የት) እንዲሁም በማን እንደሆነ የማይታወቀው ክስተት እስኪከሰትና በቅዱሳት መጽሐፍት ጸድቆ ለመላው ኦርቶዶክሳዊ ስርአቱ እስኪታወቅ ድረስ ለብዙ ማለትም ለአስራ ምናምን ክ/ዘመናት በቤተክርስትያን የዝንየት ህግ ሳይታወቅ ቆይቶ ተአማኒነቱ ማለትም መቼ፣የትና በማን? የሚሉትን ጥያቄዎችን በማይመልስ አንድ የኋላ ክስተት እንዴት ህግ ተደርጎ ሊጸድቅ ይችላል? ታሪኩ ላይ የባለ ታሪኩን ጨምሮ የማንም ስም እና ክስተቱ የተፈጸመበትን ጊዜ የሚገልጽ ምንም አይነት ማስረጃ አለመኖሩ በራሱ የታሪኩን ታማኝነትና ትክክለኛነት ጥያቄ ውስጥ ሊከተው አይችልም? 2) የዝንየት ስርአትና ህግ በብሉይ ኪዳን መጽሐፍት በኦ. ዘሌዋውያን እና በኦ.ዘዳ በተለያዩ ጥቅሶች ዝንየት የነካው ሰው የተቀደሰን ነገር እንዳይነካና ወደተቀደሰ ነገር እንዳይቀርብ ለ1 ቀን ከሰፈር ሁሉ ርቆ እንዲቆይ በግልጽ [“ከመካከላችሁ ሌሊት ዘር በማፍሰስ የረከሰ ሰው ቢኖር ከሰፈር ወጥቶ እዚያው ይቈይ።”—ዘዳግም 23፥10] ተብሎ ተነግሮ ሳለ፥ በኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ይህ ህግና ስርአት ለብዙ መቶ ክ/ዘመናት አይታወቅም ነበር ስትል ቤተክርስትያኒቱ የብሉይ ህግጋትን ባለማንበቧና ባለማወቋ ነው ወይስ ይህ የብሉይ ህግ በወንጌል ተሽሯል ብላ ስላመነች ነው? 3) የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የብሉይ ኪዳኑ የዝንየት ህግና ስርአት ተሽሮ እንደነበር በማመኗ ከሆነ ለዘመናት ህጉን ያልፈጸመችው፥ ህገ ዝንየት በወንጌል ስለመሻሩ ቤተክርስትያን ማስረጃዋ ምንድነው? 4) ተሽሯል ቢባል ራሱ በኢየሱስና ሐዋርያቱ ወንጌል ለብዙ ዘመናት ተሽሮ የነበረን ህግና ስርአት ከዛ ሁሉ ጊዜ በኋላ መልሶ ህጉንና ስርአቱን የማጽደቅ ስልጣን ለአንድ ማንነቱና መቸቱ የማይታወቅ ካህንና ለገጠመኙ ሲባል እንዴት ሊሰጠው ይችላል? 5) በየትኛውም ዘመን ተአምር ተገለጠ፣ ገጠመኝ ታየ እየተባለ ለዛውም በግልጽ ማንነታቸው፣ መቼና የት እንደሆነ ባልታወቁ ግለሰቦች ምክንያት አዳዲስ ህግጋትና ስርአቶችን ወደ ቤተክርስቲያንና ክርስትና መጨመር በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ይቻላል? https://t.me/Orthodox_Critic
Hammasini ko'rsatish...
ኧረ እኔ አምላኬን አሏህን ለማመስገን ነው የተፈጠርኩት🙄🤔 يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُلُوا مِن طَيِّبَاتِ مَا رَزَقْنَاكُمْ وَاشْكُرُوا لِلَّهِ إِن كُنتُمْ إِيَّاهُ تَعْبُدُونَ [ አል-በቀራህ - 172 ] እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ከነዚያ ከሰጠናችሁ ጣፋጮች ብሉ፡፡ ለአላህም እርሱን ብቻ የምትገዙ እንደኾናችሁ አመስግኑ፡፡ فَكُلُوا مِمَّا رَزَقَكُمُ اللَّهُ حَلَالًا طَيِّبًا وَاشْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ إِن كُنتُمْ إِيَّاهُ تَعْبُدُونَ [ ሱረቱ አል-ነሕል፥ - 114 ] አላህም ከሰጣችሁ ሲሳይ የተፈቀደ ንጹሕ ሲኾን ብሉ፡፡ የአላህንም ጸጋ እርሱን የምትገዙት ብትሆኑ አመስግኑ፡፡ “ቸር ነውና፥ ምህረቱም ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ።” — 1 ዜና 16፥34 “እግዚአብሔርን የምትፈሩ፥ አመስግኑት፤ የያዕቆብ ዘር ሁላችሁ፥ አክብሩት፥ የእስራኤልም ዘር ሁላችሁ፥ ፍሩት።” — መዝሙር 22፥23 “ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤” — መዝሙር 107፥1 ደሞ ማርያም ምን ስለሆነች ነው ፍጥረት ሁሉ ማርያምን ለማመስገን የተፈጠረው?? ወይስ በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ ማርያም ከሦስቱ ሥላሴዎች በተጨማሪ አራተኛዋ አምላክ ናት?? ከላይ በፎው ላይ እንደምትመለከቱት ተአምር ማርያም በሚባለው መጽሐፍ ምዕራፍ ሁለት ላይ ፍጥረት ሁሉ ማርያምን ለማመስገን ነው የተፈጠረው ይለናል። 🙁 👔 👖ሙከሚል ሙሥሊም ልጅ https://t.me/kNDk0
Hammasini ko'rsatish...
ሙከሚል የንፅፅር ቤተ መጽሐፍ

ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ {3:85} ሙከሚል የንፅፅር ቤተ መጽሐፍ

https://t.me/kNDk0

ሀሳብ እና አስተያየት ካላችሁ👇

https://t.me/Mukamil_Hussan

የአባ ሻውዚን ቅጥፈት ምንጭ ሰሞኑን በአጭር ቪድዮ አንድ ባለ ድሬድ ቄስ ቁርአን ላይ የተቀመጠ አረብኛ በማለት ሻውዚን ሻውዚን ምንትሴ ቅብርጥሴ እያለ የማይገባ ቋንቋ ተናግሮ ትርጉሙንም በመተርጎም ማርያምን እና ልጇን ከፍ ከፍ ያደረገበትን ምስል በርካቶች ተመልክተውታል፥ ተቀባብለውታልም። ቄሱ የተናገረውን ንግግር አብዛኞቹ ሰዎች ኦርቶዶክስ የማታስተምረውን አስተምህሮ ቄሱ በራሱ ፈጥሮ የተናገረ ሊመስላቸው ይችላል። እውነታው ግን የቄሱ ንግግር ምንጭ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን "ቅዱሳት አዋልድ መጽሐፍት ናቸው" ብላ ከተቀበለቻቸው መካከል "ተአምረ ጽዮን ማርያም" የተሰኘ መጽሐፍ መሆኑ ነው። ከላይ በምስሉ ቁጥር 4 እና 5 ላይ እንደምትመለከቱት ቃሉ የሚለው፦ ፬ "ሻውዚን ነፋሕነ ነፋሕነ ወረምሃ ላቲ አሕሳነት ኢናበሐ" ይላል። ይህም ማለት፦ "ከሦስቱ አካላት አንዱ ይወርዳል፤ በድንግል ማርያም ማህፀን ያድራል፤ ከድንግል በድንግልና ይወለዳል።" ይህም ማለት ወንድ ሳታውቅ በድንግልና ወለደች ከእሷ ተወለደ ማለት ነው። ይላል መጽሐፉ። አረብኛ የተባለው ቋንቋና የአማርኛ ትርጉሙ መቼም ለጉድ ገዳይ ነው¡😁 እስኪ አሁን አረብኛ ከተባለው ላይ የማርያምን "መርየም" የሚለውን ስም የሚያሳየኝ ይኖራል? እሺ 'ሦስተ' የሚለውን ቃልስ በአረብኛ የሚያሳየኝ አለ? ከሦስት 'አንዱ' የተባለው ላይ የተኛው ቃል ነው "አንዱ" የሚለውን በአረብኛ የወከለው?🤔 ወፍ የለም አልም ያለ ቅጥፈትና አሳፋሪ ውሸት ብቻ ነው! >እንኳን ቁርአን ላይ ቀርቶ እዚሁ አረብኛ ብለው የጻፉት ክፍል እና የአማርኛ ትርጉሙ ሆድና ጀርባ ሆኖ እያለ በዚህ ደረጃ ሲቀጣጥፉ ቁርአኑን አንብቦ ሊያዋርዳቸው የማይችል ይህን ያነበበ ኦርቶዶክሳዊ ብቻ እንዴት ያዋርደናል ብለው አይፈሩም? ለማንኛው በቋንቋውና በትርጉሙ ስቄ ልለፈውና ሀሳቡ የተቋረጠ ስለሆነ ላስረዳችሁ። ባለ ድሬዱ ቄስ ሳይሆን ይህን መጽሐፍ፥ "ቅዱስ አዋልድ መጽሐፍ ነው" ብላ የተቀበለችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በዚህ ክፍል እያለችን ያለችው፤ ከላይ 'አረብኛ ነው' በተባለው ዓ.ነገር የተቀመጠው ቃል፤ አላህ በቁርአን ስለ ኢየሱስ አምላክነት ግልጽ በማድረግ ለነብዩ ሙሐመድ ያወረደው የቁርአን ክፍል እንደሆነና ዲያቢሎስም ሙስሊሞች ይህን ክፍል እንዳያነቡት ለሙሐመድ(ሰዐወ) ይነግራቸውና ነብዩም ክፍሉ እንዳይነበብ ከቁርአን አጠሩት ነው የሚሉት። ከዛም በኋላ ዲያቢሎስ ለሙሐመድ(ሰዐወ) እንዲህ ብለህ አውግዝ ይለዋል "ይህን ክፍል ተደፋፍሮ ያነበበውና የተረጎመው የተረገመ ይሁን፤ ሥራ ሥሩ ይበጣጠስ፤ አጥንቱ ይሰበር፤ ሥጋው ይበጥ፤ ምላሱ ይቆረጥ፤ አይኑ ይታወር።" መሐመድም(ሰዐወ ) ዘመዶቹን እንዲሁ ብሎ በዚህ እርግማን ያወግዛቸዋል። ይላል የሻውዚን ቋንቋ ወ ትርጉም ቅጥፈት አላማው እንግዲህ እዚህ ላይ ነው። በቅጥፈታቸው የነብዩን(ሰዐወ) ስም ማጉደፍና ማንቋሸሽ፤ የዋህ በጎቻቸውን በውሸቶቻቸውና በመሰል ተረቶቻቸው በማወር እንዳያነቡና እንዳያውቁ በተረት ተረት እየነዱ አስተኝቶ ማኖር፤ ከተሳካላቸው አላዋቂ ጃሂል ሙስሊሞችንም በዚሁ ተረት ማጭበርበርና መበከል ወዘተ.. የመሳሰሉት አላማዎች ናቸው። ለዚህ ንግግሬ ማስረጃ ሩቅ ቦታ መሄድ አያስፈልግም። እዚሁ መጽሐፍ ላይ ባያያዝኩት የገጽ ምስል ከስር ነብዩ ሙሐመድን(ሰዐወ) ለማንቋሸሽ የቀጠፏትን የ "ቡና" ወደ ኢትዮጵያ አመጣጥ ትርክት ራሳችሁ እንድታነቡት ጋበዝኳችሁ። የኦርቶዶክስ አዋልድ ቅዱሳት መጽሐፍት ከመንፈሳዊነት በራቁ የሃይማኖትና የዘር ፖለቲካዎች፣ ቅጥፈቶችና ማንቋሸሻ ስድቦች፣ በመንፈስ ሳይሆን በስሜት የተጻፉ ሌላን ሃይማኖት አጉዳፊ ትንኮሳዎች የተሞሉ ናቸው። https://t.me/Orthodox_Critic
Hammasini ko'rsatish...
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.