uz
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Kanalga Telegram’da o‘tish

📈 Telegram kanali የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU analitikasi

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 14 479 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 6 043-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 334-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 14 479 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 530 ga, so‘nggi 24 soatda esa 23 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 39.14% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.20% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 666 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 477 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 33 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Kanal uchun tavsif kiritilmagan.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

14 479
Obunachilar
+2324 soatlar
+1447 kunlar
+53030 kunlar
Postlar arxiv
ሰበር ዜና +++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በሕገ ወጡ ቡድን የጵጵስና ልብስ አልብሶ ሾሜዎታለሁ ካላቸው መነኮሳት መካከል ከኢየሩሳሌም የመጡት "አባ" ንዋየሥላሴ አክሊሉ ቅ
+2
ሰበር ዜና +++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በሕገ ወጡ ቡድን የጵጵስና ልብስ አልብሶ ሾሜዎታለሁ ካላቸው መነኮሳት መካከል ከኢየሩሳሌም የመጡት "አባ" ንዋየሥላሴ አክሊሉ ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ዕድል በመጠቀም በመንበረ ፓትርያርክ በመገኘት አስኬማቸውንና አርዌ በትሩን ለሕጋዊዋ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በማስረከብ ቤተክርስቲያንንና ምእመናንን ይቅርታ ጠይቀዋል። በይቅርታ ደብዳቤያቸውም ሰሞኑን በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ከቅዱስ ሲኖዶሱ እውቅና ውጪ አዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሲካኼድ ከኢየሩሳሌም መጥቼ ከተሾሙት አንዱ ነበርኩ። በዚህ ምእመናንን ባሳዘነ ቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ውግዘት ባስተላለፈበት ሕገ ወጥ ሢመት ውስጥ ባለማወቅና ነገሩን ሳላጣራ የገባሁበት በመሆኑ በእጅጉ የተጸጸትኩና በዚህም ተግባር ያዘንኩ መሆኔን በይቅርታ ልብ ለመግለጥ እወዳለሁ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት ቅዱስ ሲኖዶስ በሠየመው አቀራራቢና በይቅርታ ኮሚቴ አማካኝነት በቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔ መሠረት በተከፈተው የይቅርታና የምሕረት በር ወደ እናት ቤተክርስቲያኔ እና የመንፈስ ቅዱስ አባቶቼ እንዲሁም ምእመናን ለይቅርታ የቀረብኩ ስለሆነ ቋሚ ሲኖዶሱ በምልዓተ ጉባኤው ውሳኔ መሠረት ይቅርታዬን በአባትነት መንፈስ ይቀበለኝ ዘንድ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ ብለዋል። "መከራውን ቤቴ ሁኜ ልቀበል ብለው ስለመጡ ቤተ ክርስቲያን ደስ ይላታል ፤ ሌሎችም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ከእኛ ጋ ናቸው ተብላችሁ ተታላችሁ የሄዳችሁ፤ ፀፀት ውስጥ እንዳላችሁ እናውቃለን። ሌሎች ለመምጣት እየፈለጉ ቁልፍ ተይዞባቸው እንደተቸገሩም ሰምተናል::" ብፁዕ አቡነ አብርሃም ይህንን የተናገሩት በሕገ ወጥ መንገድ ከተሾሙት "ኤጲስ ቆጶሳት" መካከል በቀድሞ ስማቸው አባ ንዋየ ሥላሴ አካሉ የይቅርታ ደብዳቤ በአስገቡ ሰዓት ነው፡፡ ++++++++++

✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram
✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg                              ✍️ Facebook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

🔔በአሁኑ ሰዓት የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ጀምሯል።https://www.youtube.com/live/t4BNPgDVsu8?feature=share

SYNOD 1.pptx1.48 KB

ከነገ ሰኞ ጀምሮ የምናከናውናቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ትዕዛዛት 1. ጠዋት 12 ሰዓት በቤ/ክ ኪዳን እና ምኅላ ማድረስ 2. ቢያንስ በቀን 41 ስግደት 3. ጠዋት 3 ሰዓት፣ ቀን 6 ሰዓት እና 9 ሰዓት በያለንበት ሰላም እለኪና አቡነ ዘበሰማያት መድገም (አላርም በመሙላት ማስታወስ) 4. ቢያንስ እስከ 9 ሰዓት መጦም 5. ሰርክ ከ11-12 ሰዓት በቤ/ክ ተገኝቶ ምኅላ (ቢቻል ከስግደት ጋር) 6. ማታ 3 ሰዓት ከቤተሰብ ጋር በስዕለ ማርያም ፊት በሐዘን እና በእንባ ጸሎት ማድረግ 7. ሌሊት 6 ሰዓት ጸሎት ማድረግ 8. ጥቁር ልብስ እንለብሳለን ለፍጻሜው በክብር ያድርሰን መልስም የምናገኝበት ይሁንልን።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ በተፈጠረው ወቅ
+6
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የሃይማኖት ፣ የቀኖና እና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች ማሳለፉ የሚታወቅ ሲሆን በዚሁ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አተገባበር ላይ የተሠሩ ሥራዎችን በተመለከተ እና ቀጣይ የሥራ ሒደት አቅጣጫዎች ዙሪያ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ የየሰንበት ት/ቤቱ ሥራ አመራር አባላት ጋር በአሁኑ ሰዓት ሥልጠና እና ውይይት እየተደረገ ይገኛል። ሙሉ ዘገባውን የምናደርሳችሁ ይሆናል.... "ሁሉ ነገሯን ለሰጠችኝ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ነገሬን ለመስጠት የተዘጋጀሁ ሰንበት ተማሪ ነኝ‼" #የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

የሰ/ት ቤቶች አንድነት ኅብረት፣ ኦርቶዶክሳዊያን ሽማግሌዎች፣ የተለያዩ የማኅበራት ተወካዮች በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች አተገባበር እና ቀጣይ ሥራዎች ላይ ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት
+1
የሰ/ት ቤቶች አንድነት ኅብረት፣ ኦርቶዶክሳዊያን ሽማግሌዎች፣ የተለያዩ የማኅበራት ተወካዮች  በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች አተገባበር እና ቀጣይ ሥራዎች ላይ ከብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጋር ውይይት አደረጉ።።

ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጡ ወረዳ ከወሊሶ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አሮ ባለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጸመውን  ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ ፤ ሕገ ወጥ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን የጣስ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት  አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ምልዐተ ጉባዔ  ያሳለፈውን ውሳኔ አስመልክቶ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት  የተሰጠ መግለጫ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በረጅሙ ጉዞዋ  በአያሌ ሊቃውንቶቿ በቃልም በመጽሐፍም እያስተማረች፤ በተለያዩ ጊዜያት  የተነሱ መናፍቃንና ሀሰተኛ መምህራንን በእውነተኛ አስተምህሮዋ እየረታች ፤ በሐዋርያት ትምሕርት ጸንታ  ሥርዓተ አበውን  እና ትውፊቷን አስጠብቃ በጥንታዊነቷ እና በአኩሪ  ቅርሶቿ ለዓለሙ ሁሉ ምስክር  እና ተጠያቂ በመሆን ወንጌለ መንግስቱን እያወጀች ትገኛለች። ፈተና ተለይቷት የማያውቀው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እኛ ዘመን የደረሰችው ዶግማዋን ለመበርዝ ፣ ሥርዓቷን ለማፋለስ ታሪኳን ለማጠየም  የተነሱትን መናፍቃን ፊት ለፊት እየተከራከረችና እየረታች ብሉይን ከሐዲስ  ምሥጢረ ሃይማኖትን ከታሪክ ፣እንዲሁም  ሥርዓትን እና ትውፊትን እያስማሙ የመናፍቃንን አፍ በሚያዘጉ ሊቃውንቶቿ ነው።   ወንበር ዘርግታ ተተኪ ሊቃውንትን በማፍራት ከንጹህ ምንጭ የተገኘውን ንጹህ ወንጌል  አቆይታልናለች።  ፈተናውን ተቋቁሟ ተደራሽነቷን ከሀገር አልፋ በመላው ዓለም  በማስፋፋት ልጆቿን በትምህርተ ሃይማኖት እና በሥነ ምግባር  ኮትኩታ ተተኪ ትውልድ በማፍራቱ  ረገድ ሰፊ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች። ፈተና የማይለያት እናት ቤተ ክርስቲያናችን  በእኛ ዘመንም በበርካታ ፈተናዎች ተከባ ትገኛለች :: ይልቁንም ከፈተናዎች ሁሉ የባሰው የሰሞኑ ለአያሌ ዘመናት ተጠብቆ የኖረ ሲኖዶሳዊ አንድነትን ለማዳከም፣ በሂደትም ቤተ ክርስቲያንን ለመከፋፈል የተደረገ የአደገኛ  ሴራ አካል የሆነውን ኢ-ቀኖናዊ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት  አጥብቀን እንቃወማለን :: በመሆኑም   ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ ፤ ሕገ ወጥ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የጣስ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት  በተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ በአስቸኳይ ምልዐተ ጉባዔ  ያስተላለፈውን ውሳኔ አስመልክቶ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከሚገኙ አጥቢያዎች ሰንበት ት/ቤቶች አመራር አባላት ጋር በመሆን በዛሬው ዕለት የሚከተለውን የአቋም  መግለጫ አውጥቷል። 1ኛ ቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በሕገ ወጥ መልኩ ኤጴስ ቆጰሳትን  የሾሙ እንዲሁም የተሾሙትን 25 ኤጲስ ቆጶሳትን ጨምሮ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን መሰረት አድርጐ   የቤተ ክርስቲያን ክብር እና ልዕልና ለማስጠበቅ  የወሰነውን ውሳኔ  በአክብሮት እንቀበላለን ::   2ኛ.   በዚሁ ኢ-ቀኖናዊ ድርጊት  በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ወይም ተባባሪ የሆኑ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞችን በተመለከተ ተገቢውን ክትትል እንዲደረግና አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነውን ውሳኔ የምንቀበል መሆኑን እና  ተከታትለን ለሚመለከተው አካል በማስረጃ  አጠናክረን የምናሳወቅ መሆኑን እንገልጻለን። 3ኛ. በሕገ ወጥ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ምክንያት በውግዘት ከተለዩት ግለሰቦች ጋር በተያያዘ  የቤተ ክርስቲያናችንን ደኅንነት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለዚህ ሕገ ወጥ አድራጎት ልዩ ልዩ ድጋፍ የሚያደረጉ ተቋማት እና ግለሰቦች  አስፈላጊውን ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ ረገድ  የመከላከል ተግባርን  እንደ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት  እንድንወጣ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠውን ውሳኔ በቁርጠኝነት እንተገብራለን :: 4ኛ.  የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ ዝርዝር ጥናት እና የመፍትሔ ሐሳብ የሚያቀርብ አንድ ዐቢይ ኮሚቴ በቋሚ ሲኖዶስ እንዲሰየም ተወስኗል ፤ በመሆኑም በዚሁ ዐቢይ ተግባር ውሰጥ ተሳታፊ በመሆን የልጅነት ግዴታችንን ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን በአጽንዖት ለመግለጽ እንወዳለን። 5ኛ . የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ያፈነገጡትን በውግዘት ከቤተ ክርስቲያን አንድነት የለየ ቢሆንም ፤ የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽተው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምሕረት ደጆች ሁልጊዜ ክፍት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የቤተ ክርስቲያን የምሕረት በር ክፍት ሆኖ እንደሚጠብቃቸው መወሰኑ እጅግ ከፍ ባለ ደስታ  የምንቀበለው እና ተፈጻሚ እንዲሆን  በልጅነት አንደበት ፈጣሪያችንን በጸሎት የምንጠይቅበት ዐቢይ ጉዳይ መሆኑን እንገልጻለን :: 6ኛ.የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ክብር እና አንድነት ፤ ሕገ ቤተ ክርስቲያን ከማስከበር እና በመፈጸም ግዴታው ኢ ቀኖናዊ ተግባራቸው ከቤተ ክርስቲያን አንድነት የለያቸው ግለሰቦችን አስመልከቶ በማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያም ሆነ በብሮድካስት ሚዲያ  ኢ-ክርስቲያናዊ የሆነ ስድብ ፣ዛቻ እና ሥም የማጥፋት ተግባር እንዳይይፈጸም ሁሉም ነገር በማስተዋል እና በጥበብ እንዲሆን በቤተ ክርስቲያን ሥም አደራ ለማለት እንወዳለን :: በመጨረሻም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ያሳለፈውን ውሳኔ የምንደግፍ እና ተግባራዊ እንዲሆን  ሁሉም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ሁሉ የልጅነት ግዴታችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን :: የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት   ጥር 19 ቀን 2015 ዓ.ም

4. በዚህ ጸረ ቤተ ክርስቲያን እና ኢ-ቀኖናዊ ድርጊት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ እየኖሩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ወይም በቦታው በመገኘት የጥፋት ድርጊቱ ተባባሪ የሆኑ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞችን በተመለከተ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን ክትትልና አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥ፤ 5. ይህን ታሪክ ይቅር የማይለውን ሕገ ወጥ አድራጎት እና የቀኖና ጥሰት በሐሳብ፤ በገንዘብ እና በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ድጋፍ ሲያደርጉ የቆዩ እና በማድረግ ላይ ያሉ ማናቸውም ተቋማት እና ግለሰቦች ከዚህ ሕገ ወጥ አድራጎታቸው እንዲቆጠቡ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ እያሳሰበ ይህ ባይሆን በሕግ አግባብ ተገቢው እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 6. በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች፤ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ መነኮሳት፤ አገልጋይ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፤ ልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ማህበራት እና ምእመናን እና ምእመናት ይህን ሕገ ወጥ አድራጎት ከመከላከል እና የቤተ ክርስቲያናችሁን ደህንነት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለዚህ ሕገ ወጥ አድራጎት ልዩ ልዩ ድጋፍ የሚያደረግ ተቋማት እና ግለሰቦችን አስፈላጊውን ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ የመከላከል ሥራችሁን እንድትወጡ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስምን ከፊትም ሆነ ከኃላ በመጨመር እና በመቀነስ በከፊልም ሆነ በሙሉ መጠቀም፤ ዓርማዋን፤ አድራሻዋን፤የአምልኮ እና የሥርዓት መፈጸሚያ የሆኑ ንዋያ ቅዱሳትንና አልባሳት እንዲሁም መጻሕፍት መገልገል የማይችሉ መሆኑ ታውቆ ይህንን ጉዳይ በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት እና የቤተ ክርስቲያኒቱ  የሥራ ኃላፊዎች ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን በተጨማሪም ይህን ውሳኔ ተላልፈው በሚገኙ ማናቸውም ግለሰቦች እና ተቋማት ላይ ተገቢውን ሕግ አግባብ ተከትሎ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለማት የሚያስፈጽም ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች በመመደብ ተገቢውን ሁሉ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 8. አሁን የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ ዝርዝር ጥናት እና የመፍትሔ ሐሳብ የሚያቀርብ አንድ ዐቢይ ኮሚቴ በቋሚ ሲኖዶስ እንዲሰየም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 9. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ያሳለፈውን ውሳኔ ከክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጀምሮ በየደረጃው ላሉት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንዲከናወኑ እና ይህ ውሳኔ ከሸኚ ደብዳቤ ጋር እንዲደርሳቸው ተወስኗል፡፡ 10. ይህን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ክፍለ ዓለማት ለሚገኙ የቤተ ክርስቲኒቱ አገልጋዮች እና ምእመናን የግንዛቤ ማስጨበጫ የንቅናቄ መድረኮች እንዲካሔዱ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በማእከል የአህጉረ ስብከት ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ታላቅ የንቅናቄ እና የግንዛቤ መድረክ እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 11. በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚገኙ መንግስታዊም ሆነ መነግስታዊ ያልሆነ ተቋማት፤ አኃት አቢያተ ክርስቲያናት፤ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት፤ የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት፤ የዓለም አቢያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያት ክርስቲያናት ጉባዔ እና ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት እና የሃይማኖት ጉባኤዎች በሙሉ እነዚህ የተወገዙት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ እና ምንም አይነት የሥራ ግንኙነት የሌላቸው መሆኑ ታውቆ ማናቸውም ግንኙነት በቤተ ክርስቲያኑቱ ስም እንዳያደርጉ በጽሑፍ አንዲገለጽ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 12. እነዚህ ግለሰቦች ከሚሰጡት የተሳሳተ መረጃ አንዱ እኩይ ተግባራቸው የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ እንደሆነ ማስመሰል ሲሆን ይኽ ተግባር ሃይማኖቱን የሚወድ፣ አባቶቹን የሚያከብር እና አስተዋይ የሆነውን የኦሮሞ ሕዝብ የማይወክል፣ የራሳቸውን የሥልጣን ጥማት ለማርካት ያደረጉት ሕገወጥ የቀኖና ጥሰት መሆኑ እንዲታወቅ፤ በተጨማሪም ለሚያሠራጩት የሐሰት አሉባልታ ወደፊት ተገቢው መልስ እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤   እስከ አሁን ድረስ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጎን በመሆን አጋርነታችሁን ያሳያችሁ፣ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት እና ሉዐላዊነት መከበር የበኩላችሁን በመወጣት መግለጫ የሰጣችሁ ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም እያመሰገንን ለወደፊቱም በጸሎታችሁ እና በመልካም አጋርነታችሁ ከጎናችን እንድትሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በጻፈው መልእክቱ በሰፊው ገልጾታል፡፡ (ጢሞ.3፣10፣ ቲቶ፣ 1፣5-7 ፍትሕ መን አንቀጽ 4) - ይህንም ቅዱሳን ሐዋርያት ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በ3ኛው ቀሌምንጦስ “ኤጲስ ቆጶስ የሀገሩ ሰዎች፣ የሀገሩ ጳጳስ፣ ፈቅደውለት ይሾም፤ ቢገኙ ሦስት፣ ባይገኙ ሁለት፣ ኤጲስ ቆጶሳት ሁነው ይሹሙት” ብለዋል፡፡ ይህም ቅዱስ ሲኖዶስ በሌለበት ሀገር፣ ፓትርያርክ በሌለ ጊዜ ምእመናን እንዳይበተኑ ተብሎ የሚደረግ ነው እንጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀመንበርነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራውን የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን በመጋፋት የሚፈጸም ከሆነ ግን ይህን ቀኖና በሕገወጥ መንገድ ለተፈጸመ ድርጊት መጥቀሱ በቅዱስ ወንጌል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል እንደመናገር ተቆጥሮ የማይሠረይ ኃጢአት መሆኑ ሊሠመርበት ይገባል፡፡ (ማቴ.12፣30-32 ሉቃስ 12፣10፣ ማርቆስ 3፡28-29 1ኛ ጢሞ 1፣13) የእነዚህ ሰዎች ተግባር በሥራ ላይ ያለውን በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ሕጋዊ የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ የመፈንቅል፣ የታላቋን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር የመናድ፣ ሕጋዊ ተቋምን የማፍረስ ወይም የመናድ ተግባር በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዟል፣ - ሠለስቱ ምዕትም ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በኒቅያ በጻፉት ቀኖና በዘጠነኛው አንቀጽ አንዱም አንዱ ኤጲስ ቆጶስነት ሊሾም ቢሻ፣ የሀገሩ ሰዎች ቢፈቅዱለት፣ የሀገሩ ጳጳስ ካልፈቀደለት ኤጲስ ቆጶስነት መሾም አይገባውም ይህን አፍርሶ ቢገኝ ሲኖዶስ ያወግዘዋል፤ ሹመቱም ይቀራል” ብለዋል፡፡ ይህም በዚህ ወቅት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲየን ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ስልጣን በመጋፋት በድፍረት ተፈጸመ የተባለው ሹመት  አስቀድሞ በአበው ቅዱሳን የተወገዘ ነው፤  - ከዚህም ጋር ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት በሚፈጸምበት ጊዜ፣ ያለ ቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ ማንም ወደ ቤተ መንግሥት እንዲሔድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አይፈቅድም፡፡ ይህንንም የተላለፈ ቢኖር ከጳጳሳና ከኤጲስ ቆጶሳት ማንም ማን ሊቀጳጳሳቱ ሳይፈቅድለት ወደ ንጉሥ ቤት አይሒድ ወለኲሉ ዘዐለወ ዘንተ ሲኖዶስ ያወግዞ ይህን ትእዛዝ ያፈረሰውን ሲኖዶስ ያወግዘዋል” ተብሎ ስለተወሰነ ዛሬም ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ውጭ የሚደረግ ማናቸውም እንቅስቃሴ ሕገወጥ በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤ - በቀኖና ቤተ ክርስቲያን … ሰው ሁሉ ማዕርጉን ጠብቆ ይኑር እንጅ፣ አንዱ ወደ አንዱ ማዕርግ አይተላለፍ፤ ይህን የሠራነውን ሥርዐት ያፈረሰውን ሰው ሲኖዶስ ያወግዘዋል ተብሎ በተጻፈው መሰረት እነዚህ ሕገወጥ አካላት በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 16 ንዑስ ቁጥር 30 የአጲስ ቀጶሳት መሾም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፣ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት እንዲመረጡና እንዲሾሙ የመወሰን ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን የሚደነግገውን ክፍል በግልጽ የጣሰ በመሆኑ፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 37 ንዑስ ቁ.1 የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የሚፈጸመው ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስፈላጊ መሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲታመንበትና ሲወሰን ብቻ እንደሚፈጸምና መደንገጉ፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 18 ንዑስ ቁጥር 5 የቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ሕግጋትንና ቀኖናን የሚያፋልስ ሊቀ ጳጳስ /ኤጲስ ቆጶስ/ ከአባልነት እንደሚሰረዝ በመደንገጉ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዟቸዋል፡፡ በአጠቃላይ የተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር በሕገ ሰብእም ሆነ በሕገ እግዚአብሔር ሚዛን የተወገዘ ከመሠረተ እምነት የተለየ፣ በአበው ቀኖና፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን እና በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በአጠቃላይ ተቀባይት የሌለው ነው፡፡ ስለዚህ 1ኛ. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 138 መሠረት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጩ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፩ኛ. አባ ሳዊሮስ 2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ 3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በማኅህበራዊ እና በብሮድካስት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ የተረጋገጠ በመሆኑ በዚሁ ድርጊታቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር በመፈጸማቸው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ፤ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ ለይቷቸዋል፡፡ በመሆኑም፡- ሀ. ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የተነሣ ስለሆነ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ፤ ለ. በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡ ሐ. በነዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አውግዞ በለያቸው ግለሰቦች ይመሯቸው በነበሩ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ አገልግሎት በማከናወን ሀገረ ስብከቱን የሚመሩ ብፁዐን አባቶችን ፩. ለደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ፪. ለኬንያ፤ኡጋንዳ፤ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ሀገረ ስብከት ፫. ለኢሉ አባቦራ እና በኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ፬. በሰሜን አሜሪካ ለሜኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፭. ለጉጂ፤ምዕራብ ጉጂ እና ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት ፮. ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም በአባትነት የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደቡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ወስኗል፡፡  ይሁን እንጅ ከላይ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳውቃል፤  2. የቅዱስ ሲኖዶሱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና በመዳፈር እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በተነሳሱ ግለሰቦች አማካኝነት የኤጲስ ቆጶስነት ሺመት አግኝተናል፤ ተሸመናል እያሉ የሚገኙ 25 መነኰሳት በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንን ጥሰው የተገኙ በመሆኑ አስቀድሞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት ተሽሮ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲያን ተለይተዋል፡፡ 3. ከነዚሁ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አባ ጸጋዘአብ አዱኛን ከቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ ስብሰባ በፊት የቀኖና ጥሰቱንና ሕገ ወጥ አድራጎቱን በመረዳትና በመጸጸት ድርጊቱን በመቃወም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ባቀረቡት የይቅርታ አቤቱታ መሠረት ቅዱስ ሲኖዶሱ ይቅርታውን የተቀበላቸው ሲሆን እንደሳቸው ሁሉ ከላይ የተወገዙት 25 ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን እንገልጻለን