uz
Feedback
ቤተ ያሬድ

ቤተ ያሬድ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ንባብ ቅኔ ቅዳሴ በቋሚነት ለመማር @lealem16 (+251934104451) ያናግሩን።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ቤተ ያሬድ analitikasi

ቤተ ያሬድ (@beteyared21) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 186 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 716-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 219-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 186 obunachiga ega bo‘ldi.

12 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 427 ga, so‘nggi 24 soatda esa 6 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.29% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.69% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 841 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 864 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 41 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ንባብ ቅኔ ቅዳሴ በቋሚነት ለመማር @lealem16 (+251934104451) ያናግሩን።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 13 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 186
Obunachilar
+624 soatlar
Ma'lumot yo'q7 kunlar
+42730 kunlar
Postlar arxiv
photo content

The New Normal ስለሚባለው ነገር ታውቃላችሁ? በአማርኛ ቀጥተኛ ትርጉም ላገኝለት አልቻልኩም (አዲሱ መደበኛነት/ አዲስ ልምምድ ሴንስ አልሰጥሽ አለኝ። በተሻለ የሚገልጽ ካለ ወዲህ በሉኝ) ፤ ለማንኛውም ምንድነው የሚለውን ለመግለጽ፦ አንድ ህሊናን የሚሰቀጥጥ ዘግናኝ ግፍ በተደጋጋሚ ሲከሰት፣ የሰው ልጅ አእምሮ ያለማቋረጥ የሚመጣበትን የድንጋጤ ማዕበል መቋቋም ስለሚያቅተው፣ ራሱን ለመከላከል ሲል ሰቆቃውን እንደ መደበኛ የዕለት ዜና ወደ መቀበል ይሸጋገራል። ያልተለመደውና አሰቃቂው ግፍ ቀስ በቀስ የህይወት አካል ሲሆን፣ ትላንት ጎረቤቱ በግፍ ተገድሎና ንብረቱ ወድሞ ያደረ ሰው፣ በማግስቱ ጠዋት ምንም እንዳልተፈጠረ አሜን ብሎ የለመደውን ኑሮውን መግፋት ይጀምራል። ይህ አደገኛ የሞራል ስብራትና የህሊና መደንዘዝ ግለሰብን ብቻ ሳይሆን ስርዓትንም ስለሚቆጣጠር ሚዲያዎች፣ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ሚዛናዊ ነን የሚሉ ጸሐፊዎች ሳይቀሩ የሚፈሰውን የንጹሃን ደም አይተው እንዳላዩ በዝምታ ማለፍን ይመርጣሉ። ከሁሉ በላይ የዚህ አእምሮን የመቆጣጠር ሂደት አስከፊው ማሳያ፣ የህብረተሰቡ የድንጋጤ መለኪያ ከሰው ልጅ ህይወት ክቡርነት ወደ ቁጥር ስሌት መውረዱ ነው። አእምሮው በግፍ የተገራ ማህበረሰብ ንፁሀን ተገደሉ ከሚለው የሰቆቃ ጥልቀት ይልቅ፣ ለመሆኑ ስንት ተገደሉ? የሚለው ስታቲስቲክስ ብቻ ሚዛን ይደፋበታል። በአጭሩ The New Normal ማለት፣ የሰውን ልጅ ህሊና ሰልቦ፣ ሞትን፣ ፍርሃትንና ግፍን አቅፎ በሰቆቃ ውስጥ ዝም ብሎ የመኖር አሳዛኝ ልምምድ ነው። ልልምድ የሚያስከትለው ጭካኔን በጸጥታ እንዲቀበል የሚያስገድድ አስፈሪ የአእምሮ እስር ቤት ነው። ... ዛሬ በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለይም በኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች ላይ የሚደርሰው ተደጋጋሚ ጥቃት፣ የንጹሃን ግድያ፣ ማዋከብ እና የንብረት ውድመት ከብሔራዊ የድንገተኛ አደጋነት ስሜት ወርዶ የተለመደ የዕለት ተዕለት ዜና ሆኗል። ለምን ከመደጋገሙ የተነሳ ተለምዷል። The Normal ሆኗል። የሰው ልጅ መከራና በግፍ የፈሰሰው የንጹሃን ደም ልክ እንደ አቤል ደም ወደ ፈጣሪ እየጮኸ ባለበት በዚህ ዘመን፣ ህብረተሰባችን ግን አደገኛ የህሊና መደንዘዝ ውስጥ ገብቶ ዋነኛ የሞራልና የሃይማኖት መለኪያውን እያጣ ይገኛል። ጠቢቡ ሰሎሞን በመጽሐፈ መክብብ 8፥11 ላይ "በክፉ ሥራ ላይ ፈጣን ፍርድ አይሰጥምና ስለዚህ በሰው ልጆች ልብ ክፉን ነገር ለማድረግ ሞላ" እንዳለው፣ የዚህ የህዝብ ዝምታና የመላመድ አስከፊው ውጤት ወንጀለኞችን እጅግ አደፋፍሯቸዋል። ፍርድና ተጠያቂነት እንደማይመጣባቸው ሲረዱ እብሪታቸው ጣሪያ ነክቶ፣ ዛሬ ላይ አንዳንዶች በፈጸሙት ጭካኔ በአደባባይ ሲፎክሩ ይታያሉ። ቀድሞ ወንጀል ሰርቶ መደበቅ መካድ የነበረው ተረስቶ ምን ታመጣለህ? አጠፋሃለሁ፣ ጨርስሃለሁ ወደሚል ድፍረትና መለማድ ተቀይሯል። የደነዘዘው ማኅበረሰብም ሰምቶ ያልፈዋል። ሲፎክር የነበረው አካል የተናገረውን ነገ ይፈጽመዋል። የርሸና ዜናዎቸን Scroll አደርገን እናልፋቸዋልን። አእምሯችን መሞታችን ምንም አይደል ይለናል። አንገት ቢቆረጥም ዋናው ጤና ነው ፌዝ ቢመስልም እየኖርንበት ነው። ... አንድ Record የተደረገ Video ደርሶኝ እንደ ማኅበረሰብ ምን ላይ እንዳለን ግራ ያጋባል። ወጣቱ ልጅ ''አርሲ ላይ ተገደልን ትላላችሁ? ወላሂ ገና እናጠፋችዃለን። እንኳን ለመኖር ለሰላምታ ራሱ አትቀቁም ቃፊሮች ይላል... ቀጥሎም ምራቁን ይተፋል። ሌላ የደረሰኝ Video ላይ ትላንት Record የተደረገ ነው ተናጋሪዎቹ በግሩፕ ሆነው ''አይደለም በህይወት ያላችሁትን በመቃብር ያሉትን ክርስቲያኖች ሬሳ አውጥተን ነው የምናቃጥለው ይላል አንደኛው ሌላኛው በAfaan Oromoo ምንም ብትንጫጩ እናጠፋቹሃለን ይላል... ቀጣዩ ተናጋሩ አርሲ ከእኛ ጋር ቃፊር አይኖርም። ይላል። ከኖራችሁም ግብር እየከፈላችሁ ትኖራላችሁ ይላል። የሚገርመው ከተናገሪዎቹ ግማሾቹ ፊታቸው እየታየ ነው በሰላምየሚናገሩት ከፊሎቹ ስማቸው። በድፍረት እየተባለ ያለው ለመኖር ብቻ "ልዩ ግብር እና ክፍያ መክፈል አለባቸው" እስከማለት የደረሱ ጽንፈኞች መኖራቸው የህግን መዋረድ ያሳያል። ይሁን እንጂ እዚህ ላይ በግልጽ ሊሰመርበት የሚገባው ትልቅ እውነት፣ ይህንን አጸያፊ ድርጊት የሚፈጽሙት ጥቂት አክራሪዎች ዋሃቢያእንጂ፣ አብሮ በሰላምና በፍቅር የሚኖረው፣ አብሮን ማዕድ የሚካፈለው የሌላው እምነት ተከታይ ወንድማችን አለመሆኑን ነው። ትግላችን ከደም አፍሳሽ ከአሸባሪ እና ከክፋት መንፈስ ጋር እንጂ፣ አብሮን ከኖረው ህዝብ ጋር ፈጽሞ ሊሆን አይችልም። በመጨረሻም እያንዳንዱ ምእመን ቆም ብሎ ራሱን ሊጠይቀው የሚገባ አንድ ጥልቅ ጥያቄ አለ፦ አንድ ማህበረሰብ በእውነት አደጋ ላይ የሚወድቀው መቼ ነው? መጀመሪያ ግፍ ሲታይና ሲፈጠር ነው ወይስ ሰዎች ያንን ግፍ ሲላመዱት? በእውነት ግፍን መላመድ ከግፉ በላይ አጥፊ ነው። ስለዚህ ከዚህ የዝምታ እና የመደንዘዝ መንፈሳዊና ስነ ልቦናዊ እንቅልፍ በአስቸኳይ ልንነቃ ይገባል። በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረው የሰው ልጅ ክብር ይጠበቅ፣ ፍትህ እንደ ወንዝ ትፍሰስ፣ ወንጀለኞች ለፍርድ ይቅረቡ፤ ማንም ሰው በማንነቱና በእምነቱ የተነሳ በገዛ ሀገሩ ላይ ባይተዋር አይሁን። ሁላችንም በጋራ ለፍትህና ለንጹሃን ደህንነት ድምፃችንን ከፍ አድርገን የምናሰማበት ጊዜ አሁን ነው፤ አለበለዚያ ይህ የዝምታ አዲሱ ልምምድ/The New Normal ሁላችንንም ይውጠናል። ... ከታች የተያያዘው ምስል AI ያመረተው ነው። ከጽሁፍ ባሻገር ወገኖቻችን ያሉበትን ሁኔታ በምስል ያሳይልኝ ዘንድ ያዘጋጀሁት ነው። Maryamawit Henok Lemessa

ቅኔ ዘረፋ ተጀምሯል። 👇👇👇👇👇 https://t.me/beteyared22?videochat

photo content
+1

photo content

🌷🌷 የሰምና ወርቅ አመጣጥ፦ (በመ/ር ጽጌ ሲሳይ) ለምሳሌ ዛሬ  የአባ  ተክለ  ሃይማኖት  ወርሓዊ መታሰባያ    ነው፤ የአባ  ተክለ ሃይማኖትን  ታሪክ  ገድላቸው ከጽንሰት  እስከ  ልደት በዘመናቸው  ያከናወኖቸውን ጉዳዮች  ሁሉ   ለኔ  ነገረኝ፤ ከዚህ   ታሪክ  መሀከል  ለቅኔ     ማስነገሪያ  ላውጣበት  ብል፦ ↙️↙️፩ኛ  በሕጻንነታቸው  በአካባቢው  ረኀብ  ሁኖ  የእናት አባታቸውን  ቤት  በበረከት  ማጥለቅለቃቸው፥ ↙️↙️፪ኛ  በተወለዱ በሦስተኛው  ቀን  አሐዱ  አብ ቆዱስ አሐዱ  ወልድ   ቅዱስ ፥ አሐዱ  ውእቱ  መንፈስ  ቅዲስ  ብለው  ማመስገናቸው፥ ↙️፫ኛ  ሰባት  ዓመት  በአንድ  እግራቸው ቁመው መጸለያቸው፥ ↙️↙️፬ኛ  እግራቸው  ብትሰበር  ክንፈ  ጸጋ  ከጌታ መሰጠታቸው፥ በቃ  የመሳሰሉትን  ነቅሼ  ለቅኔ  አወጣሁ።  እነዚህን  ይዤ  ወደ  ሰም  ፍለጋ  እሄዳለሁ፤ 🌷🌷 በነገራችን   ላይ  በቅኔ  ትምህርት  አስጨናቂው ወርቅ  መፈለጉ  አይደለም  ከወርቁ  ጋራ  ተስማምቶ  ቅኔውን  ሕያው  ሊያደርግ  የሚችል  ሰም  ፍለጋው   ነው፥ ወርቅማ  መምህሩ  ከሚተርኩልህ  ታሪክ፤ ከስንክሳሩ፥ ከገድላቱ  እና  መዋዕለ  ዜናው  ከተዘገበበት  አካል ሰምተህ  አንብበህ  የምታገኘው   ነው፥  ሰም  ግን  ወርቁ  በአእምሮህ   ተሸክመህ  ሰም  ፍለጋ  ትሄዳለህ፥ 🌷🌷  በእርግጥ  በጸናው  እና በበለጠው  መናገሬ  ነው  እንጅ  አንዳንድ  ባለ  ቅኔዎች  ሰሙን  ከዓለም  አስቀድመው የሚያመጡም   አሉ፤  ከዚያ በኋላ ያንን ሰም  ይዘው  ኑረው  ለዚያ  ሰም  የሚስማማ  ታሪክ ወይም  በዓላት  በመጡ  ቀን  ያንን ሰም  ከቋሚው ታሪክ  ጋራ ሰድረው  ቅኔ  ያደርጉታል። 🌷🌷ለምሳሌ፦ ወርቁን  ይዞ  ሰም  ፍለጋ  መሄድን  በተመለከት  የቅኔ አመጣጥ ዘዴ፤ በእግራቸው  መሰበር  ምክንያት  ክንፍ ተሰጥቷቸዋል፥  በክንፏ  ብቻ  ቅኔ    እናስብ፤ አሁን እኔ  ቅኔ ቆጠራ  ሂጃለሁ  ብላችሁ   አስቡ፥ ስሄድ  ግን  አንድ  ወሳኝ    ነገር  ይዣለሁ  እርሱም  የአባ  ተክለ  ሃይማኖት  ክንፍ  ነው፥ አሁን  እያሰብኩ   ነው፥ በክንፍ  ምን  ይሠራል? ስለ  ክንፍ  ምን   ይወራል? በክንፍ  ዙሪያ  ምን  አይነት  ብሂሎች  አሉ? ክንፍ   የት  ላይ  ይበቅላል? ስንት  ክንፍ  ሊኖር  ይችላል? በክንፍ ከየት  ወዴት  ይሄዳል? ክንፍ  በመጽሐፍ  ቅዱስ? ክንፍ  በሊቃውንት  መጻሕፍት? ክንፍ  በእንቆቅልሾች? ክንፍ   በተረቶች እና በመሳሰሉት  ቃኘሁ፤ ክንፍ ምንድን   ነው?ብየ  በዓለም  ቃኘሁ። አንድ  ነገር  መጣልኝ፥  ለዶሮዎች  ክንፍ  አላቸው  አንዳንድ ተናታፊ    ዶሮዎች  በክንፋቸው  ሰውን  ይመታሉ፤  ይህንን  አየሁና  ቅኔ  ላደርገው  አሰብኩ። ከዕለቱ  የተክለ  ሃይማኖት  ክንፍ  ጋራ  አነጻጸርኩት፥ እንዲህም  ብየ  ቅኔ  አደርግኩት፤ 🌷🌷   ለተ ክለ  ሃይማኖት   ሕጻን  አመ  ፈቀደ   የኀጦ፥ ገድል  ዶርሆ  ሃይማኖት   በክነፍ     ዘበጦ አልኩኝ፥ ለሰም፦ 🌷🌷አንዳንድ  ሕጻናት  የዶርሆውን  አንገት  እየያዙ  የሚያስቸግሩ   ሕጻናት  አሉ፥ ዶሮው  ሲወጣ  ሲገባ እንነቅህ የሚሉ፤   ታድያ  ደግሞ  ተናካሽ  ዶሮ  ያጋጥማቸዋል፥  በዚህ  ጊዜ  እንይዛለን  ብለው  ሲሮጡ  ዶሮው በክንፉ  ይመታቸዋል።  ይሄ ለሰም  ነው፤  ለወርቅ  ግን  የተክለ  ሃይማኖት  ገድል  ተክለ  ሃይማኖትን  ባለ  ባለ  ክንፍ  አደረገችው  ማለት  ነው፥ ......፪ኛ   🌷🌷 ተክለ   ሃይማኖት   ኀያል  አመ  ፈቀደ ይስጥጣ፤   ለገድል  ኳሔላ  መከራ  በእግሩ  ዘበጣ። 🌷🌷ትርጓሜው፦  ኀያል  ተክለ  ሃይማኖት  መከራ የበዛባት  ገድል  ኳስን  ሊቀዳት  በሻተ   ጊዜ፥ ገድል  ኳስን  በእግሩ  ደበደባት ማለት  ነው፥ ↙️↙️ለሰም፦  ባለ  ኳስ ኳሷን  አጉኖ  ሊጥላት  በፈለገ ጊዜ  በእግሩ  ይመታታልል፥   ለወርቁ  ደግሞ  ተክለ  ሃይማኖት  ተጋድሎውን  በእግር  አደረገ ማለት  ነው። ↙️↙️እነዚህን   ቀለል  ያሉ  ከቅርቡ  ሊመጡ  የሚችሉ  መጽሐፈኛ  ሳዬሆን ከርእዮተ  ዓለም  የሚመጡ ሁለት  የጀማሪ  ቅኔዎችን  ለምሳሌ  የሰጠሁት ከቅርቡ  ወደ ሩቁ  የቅኔ  አቆጣጠር  ወይም  አመጣጥ  ስልት ቀስ በቀስ ልወስዳችሁ   ብየ    ነው፤ ↙️↙️እንግዲህ  ቅኔ  ቆጣሪው  አሁን  የቅኔ  ቆጠራ  ስልቱን  እየተለማመደ   ነው፥ ከላይ  በዘረዘርኳቸው  በክንፍ  ዙሪያ  ሰፋ  ያሉ  ቅኔዎችን  ወደ ማምጣት  ቅኔውን  ያሳድገዋል፤.... @beteyared21 @beteyared21 @beteyared21

photo content

እንኳን አደረሳችኹ። ግንቦት 21 አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ በግልጽ የታየችበት
+1
እንኳን አደረሳችኹ። ግንቦት 21 አምላክን የወለደች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በደብረ ምጥማቅ በስሟ በተሠራች ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ በብርሃን መርከብ ተቀምጣ በግልጽ የታየችበት ዕለት ነው፡፡

💚የምሥራች💚 👉ሐመረ ቅኔ ዘሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው የተሰኘ ታላቅ የቅኔያትና የዕርባታ መጽሐፍ በመጋቤ አእላፍ ቅዱስ ያሬድ ለኅትመት በቅቶ በ22/09/2018 ዓ.ም በድምቀት ይመረቃል። በዕለ
💚የምሥራች💚 👉ሐመረ ቅኔ ዘሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው የተሰኘ ታላቅ የቅኔያትና የዕርባታ መጽሐፍ በመጋቤ አእላፍ ቅዱስ ያሬድ ለኅትመት በቅቶ በ22/09/2018 ዓ.ም በድምቀት ይመረቃል። በዕለቱም የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃምና ብፁዕ አቡነ ዘካርያስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ፣ የአሁጉረ ስብከቶች የየመምሪያ ኃላፊዎች ፣ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና ዳይሬክተሮች፣ የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ የአብነት መምህራን እና እንዲሁም ከልዩ ልዩ ቦታ የተጋበዙ እንግዶች ይታደማሉ ፤ በዕለቱ የተላያዩ መርሐ ግብሮች ይቀርባሉ።

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የቍጥር ውክልና = አነባቡ = አረብኛ -       አልቦ =     0 ፩ =    አሐዱ =  1 ፪ =    ክልኤቱ = 2 ፫ =    ሠለስቱ =    3 ፬ =    አርባዕቱ =   4 ፭ =    ኃምስቱ =5 ፮ =     ስድስቱ =6 ፯ =     ስብዓቱ =7 ፰ =     ስመንቱ =8 ፱ =     ተሰዓቱ =9 ፲ =     ዐሠርቱ =10 ፲፩ =   ዐሠርቱ ወአሐዱ =11 ፲፪ =   ዐሠርቱ ወክልኤቱ =12 ፲፫ =   ዐሠርቱ ወሠለስቱ =13 ፲፬ =   ዐሠርቱ ወአርባዕቱ =14 ፲፭ =   ዐሠርቱ ወሐምስቱ =15 ፲፮ =   ዐሠርቱ ወስድስቱ =16 ፲፯ =   ዐሠርቱ ወሰብዓቱ =17 ፲፰ =   ዐሠርቱ ወስመንቱ =18 ፲፱ =   ዐሠርቱ ወተሰዓቱ =19 ፳ =   እስራ =20 ፴ =  ሠላሳ =30 ፵ =  አርብዓ =40 ፶ =  ሃምሳ =50 ፷ =  ስድሳ =60 ፸ =  ሰብዓ =70 ፹ =  ሰማንያ =80 ፺ =  ተሰዓ =90 ፻ =  ምእት =100 ፻፩ = ምእት ወአሐዱ =101 ፻፪ = ምእት ወክልዔቱ =102 ፻፲ = ምእት ወዐሠርቱ =110 ፻፲ወ፩ =ምእት ዐሠርቱ ወአሐዱ =111 ፻፳ =ምእት ወእስራ =120 ፻፴ =ምእት ወሠላሳ =130 ፻፵ =ምእት ወአርብዓ =140 ፻፶ =ምእት ወሃምሳ =150 ፻፷ =ምእት ወስድሳ =160 ፻፸ =ምእት ወሰብዓ =170 ፻፹ =ምእት ወሰማንያ =180 ፻፺ =ምእት ወተሰዓ =190 ፪፻ =ክልዔቱ ምእት =200 ፪፻ወ፲ =ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ =210 ፪፻፳ =ክልኤቱ ምእት ወእስራ =220 ፫፻ =ሠለስቱ ምእት =300 ፬፻ =አርባዕቱ ምእት =400 ፭፻ =ሐምስቱ ምእት =500 ፮፻ =ስድስቱ ምእት =600 ፯፻ =ስብዓቱ ምእት =700 ፰፻ =ስመንቱ ምእት =800 ፱፻ =ተሰዓቱ ምእት =900 ፲፻ =ዐሠርቱ ምእት =1000 ፳፻ =እስራ ምእት =2000 ፴፻ =ሠላሳ ምእት =3000 ፵፻ =አርብዓ ምእት =4000 ፶፻ =ሃምሳ ምእት =5000 ፷፻ =ሳድስ ምእት =6000 ፸፻ =ሰብዓ ምእት =7000 ፹፻ =ሰማንያ ምእት =8000 ፺፻ =ተሰዓ ምእት =9000 ፻፻ =እልፍ =10,000 ፪፻፻ =ክልዔቱ እልፍ =20,000 ፫፻፻ =ሠለስቱ እልፍ =30,000 ፬፻፻ =አርባዕቱ እልፍ =40,000 ፭፻፻ =ኃምስቱ እልፍ =50,000 ፮፻፻ =ስድስቱ እልፍ =60,000 ፯፻፻ =ሰብዓቱ እልፍ =70,000 ፰፻፻ =ስመንቱ እልፍ =80,000 ፱፻፻ =ተሰዓቱ እልፍ =90,000 ፲፻፻ =ዐሠርቱ እልፍ =100,000 ፳፻፻ =እስራ እልፍ =200,000 ፴፻፻ =ሠላሳ እልፍ =300,000 ፵፻፻ =አርብዓ እልፍ =400,000 ፶፻፻ =ሃምሳ እልፍ =500,000 ፷፻፻ =ስድሳ እልፍ =600,000 ፸፻፻ =ሰብዓ እልፍ =700,000 ፹፻፻ =ሰማንያ እልፍ =800,000 ፺፻፻ =ተሰዓ እልፍ =900,000 ፻፻፻ =አእላፋት =1,000,000 ፲፻፻፻ =ትእልፊት =10,000,000 ፻፻፻፻ =ትልፊታት =100,000,000 ፲፻፻፻፻ =ምእልፊት =1,000,000,000 ወዘተረፈ.... @beteyared21 @beteyared21 @beteyared21

ግሥ አካለ(አባለ) ሰብእ( የሰውነት ክፍል) ርእስ= ራስ ስእርት= ጠጉር ገጽ =ፊት ገጻት= በብዙ ቅርንብ= ቅንድብ ቀራንብት= በብዙ ዓይን =በቁሙ አዕይንት= በብዙ ዕዝን =ጆሮ አዕዛን= በብዙ መልታህት =ጉንጭ መላትሕ =በብዙ አንፍ =አፍንጫ አእናፍ =በብዙ ከንፈር= በቁሙ ከናፍር =በብዙ አፍ =በቁሙ ስን(አጥብቅ) =ጥርስ አስናን = በብዙ ልሳን =አንደበት (ቋንቋ) ቃል =በቁሙ ቃላት =በብዙ እስትንፋስ =ትንፋሽ ጉርዔ =ጉሮሮ ጉራዕው =በብዙ ክሳድ= አንገት ክሳውድ (ድን አጥብቅ) =በብዙ መትከፍት= ትክሻ መታክፍት= በብዙ ዘባን =ጀርባ ዘባናት= በብዙ እንግድዓ= ደረት እንግድዓት =በብዙ ኅጽን =  እቅፍ እድ =እጅ አእዳው= በብዙ መዛርዕ = ክንድ መዛርዕው = በብዙ ኩርናዕ = ክርን እመት =ክንድ እመታት =በብዙ እራኅ =መዳፍ እራኃት= በብዙ አጽባዕት= እጣት አጻብዕ=  በብዙ ጽፍር= ጥፍር አጽፋር = በብዙ ጥብ =ጡት አጥባት =በብዙ ገቦ= ጎን ገበዋት =በብዙ ከርሥ =ሆድ ልብ =በቁሙ ኲልየት=ኩላሊት ኩልያት= በብዙ ሕሊና= ሀሳብ ሕሊናት= በብዙ አምትንት=  ጅማት አማዑት= አንጀት ንዋየ ውስጥ =የሆድ እቃ ንዋያተ ውስጥ= በብዙ ኅንብርት= እምብርት ማኅፀን =በቁሙ ሐቌ= ወገብ ቊይጽ= ጭን አቁያጽ= በብዙ ብርክ =ጉልበት አብራክ= በብዙ ሰኮና=  ሽሆና(ቁርጭምጭሚት) ሰኳንው =በብዙ እግር= በቁሙ አእጋር = በብዙ መከየድ =የእግር ጫማ @beteyared21 @beteyared21 @beteyared21

ቅኔያት ዘሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሺፈራው በእንተ ዕርገት ዘወልድ ዘአምላኪየ አብዝኆ ወልደ አብ ስብሐተ በአፈ መላእክት ትካዜ :: በይነ አይ ወበይነ ደኃሪ ዘኤልያስ ጊዜ :: እስመ ባዕለ ምድር ትካት ለሊሁ ወነዳየ ምድር ይእዜ ፡፡ ትርጉም፦ በመላዕክት አፍ መመስገን ሀዘንን የአብ ልጅ ማብዛት ስለምን ነው ስለኋለኛ የኤልያስ ጊዜ ነው እንጅ እርሱ ድሮ የምድር ባዕለ ፀጋ ነበረና ዛሬም የምድር ችግረኛ ኾኗልና። ዘይእዜ፦ ብእሴ ሕግ ጽኑዕ ዐማኑኤል መጽንዒ ዘሔኖክ ወዘኤልያስ ሥርዐተ:: ክልኤሆሙ ክልኤሆሙ ሞተ አባሁ ወእሞ መቅበርተ፡ ኀዲጎ ተለወ ደመና መስተፃምርተ። ምስሌሃ የሀሉ እስከ አመ ሞተ:: በርሥኣነ ገብርኤል ቃል ሞተ ገብርኤል ስብሐተ፡ ምስሌሃ የሀሉ እስከ አመ ሞተ፡፡ ትርጉም፦ የሁለታቸው ኤልያስና ሄኖክ ስርዓትን የሚያፀና የፀና ሕግ ሰው ዐማኑኤል ሁለት የሚሆኑ ሞት አባቱንና መቃብር እናቱን ትቶ ደመና ሚስትን ተከተለ የገብርኤል ሞት ምስጋናን በገብርኤል እርጅና ቃል እስኪሞት ድረስ ከርሷ ጋር ይኖር ዘንድ፡፡

ይህንን ያውቃሉ ? የአብነት ትምህርት በጥራት በማስተማር እንጂ  በዚህ ጊዜ ይህን የኽል እናስተምራለን ብለን የምንወስነው አይደለም። ምክንያቱም:- ትምህርቱ ለእያንዳንዱ ሰው እንደ ጀመረበት ጊዜና እንደ ትምህርት አቀባበሉ በተናጠል ይሰጣል እንጂ እንደ ዘመናዊ ትምህርት በአንድ እኩል (በባች/batch) ስለማይሰጥ ከዚህ በተጨማሪም መማር የሚፈልጉት እስከ ምን ድረስ ነው በሚለው ይወስናል። ለምሳሌ፦ ከውዳሴ ማርያም እስከ መልክአ ኢየሱስ በቃል ለመያዝና መዝሙረ ዳዊት ለመዝለቅ በአማካይ እስከ ሁለት ዓመት ሊወስድ ይችላል።

ለግእዝ /አብነት ትምህርት ፈላጊዎች፦ ከሀገር ውጪ እየኖሩ የግእዝ ንባብና ሌሎችንም የአብነት ትምህርቶች ለመማር ሰዓት አልመቻች ብሎዎታል ? እንግዲያውስ በሚፈልጉት በጉባኤም ኾነ በግል ለመማር እንዲ
ለግእዝ /አብነት ትምህርት ፈላጊዎች፦
ከሀገር ውጪ እየኖሩ የግእዝ ንባብና ሌሎችንም የአብነት ትምህርቶች ለመማር ሰዓት አልመቻች ብሎዎታል ? እንግዲያውስ በሚፈልጉት በጉባኤም ኾነ በግል ለመማር እንዲችሉ ትምህርት ቤታችን 24 ሰዓት ክፍት አድርገናል። ለበለጠ መረጃ፦ 👉@lealem16 ጠቅ አድርገው በቴሌግራም ያናግሩን። ስልክ፦ +251934104451

ባሕረ ሐሳብ (1).pdf1.44 MB

የግእዝ ቋንቋ ትምህርት..pdf3.29 MB

ለግእዝ /አብነት ትምህርት ፈላጊዎች፦ ከሀገር ውጪ እየኖሩ የግእዝ ንባብና ሌሎችንም የአብነት ትምህርቶች ለመማር ሰዓት አልመቻች ብሎዎታል ? እንግዲያውስ በሚፈልጉት በጉባኤም ኾነ በግል ለመማር እንዲ
ለግእዝ /አብነት ትምህርት ፈላጊዎች፦
ከሀገር ውጪ እየኖሩ የግእዝ ንባብና ሌሎችንም የአብነት ትምህርቶች ለመማር ሰዓት አልመቻች ብሎዎታል ? እንግዲያውስ በሚፈልጉት በጉባኤም ኾነ በግል ለመማር እንዲችሉ ትምህርት ቤታችን 24 ሰዓት ክፍት አድርገናል።
ለበለጠ መረጃ፦
👉@lealem16 ጠቅ አድርገው በቴሌግራም ያናግሩን። ስልክ፦ +251934104451

ለ (1).mp36.46 MB

#የግሥ #ጥናት #ክፍል #ሁለት ፩) ሐለለ=? ፪) ሐመለ=? ፫) ሐሰለ=? ፬) ሐቀለ=? ፭) ኀበለ=? ፮) ሐበለ=? ፯) ሐብለ=? ፰) ሐንበለ=? ፱) ሖለ=? ፲) ሐዘለ=? ፲፩) ኀየለ=? ፲፪) ኄለ=? ፲፫) ሀጕለ=? ፲፬) ሐፈለ=? ፲፭) መሐለ=? ፲፮) መለለ=? ፲፯) መምዔለ=? ፲፰) መሰለ=? ፲፱) መሰለ=? ፳) መበለ=? ፳፩) መዐለ=? ፳፪) መከለ=? ፳፫) ሞጽበለ=? ፳፬) ሰሐለ=? ፳፭) ሳሕለለ=? ፳፮) ሰመለ=? ፳፯) ሰሰለ=? ፳፰) ሰቀለ=? ፳፱) ሰብለ=? ፴) ሰንሰለ=? ፴፩) ሰአለ=? ፴፪) ሰከለ=? ፴፫) ሶለ=? ፴፬) ሰደለ=? ፴፭) ሰገለ=? ፴፮) ሰፈለ=? ፴፯) ረመለ=? ፴፰) ሮለ=? ፴፱) ረገለ=? ፵) ቀለ=? ፵፩) ቈልቈለ=? ፵፪) ቈስለ=? ፵፫) ቀበለ=? ፵፬) ቀብለ=? ፵፭) ቀተለ=? ፵፮) ቀፈለ=? ፵፯) ብህለ=? ፵፰) በልበለ=? ፵፱) በሰለ=? ፶) በቈለ=? ፶፩) ብዕለ=? ፶፪) ቤዐለ=? ፶፫) በአለ=? ፶፬) ቤወለ=? ፶፭) በጠለ=? ፶፮) በጸለ=? ፶፯) ትሕለ=? ፶፰) ተልዕለ=? ፶፱) ተማሕለለ=? ፷) ተመዝጎለ=? ፷፩) ተሠሀለ=? ፷፪) ተሰአለ=? ፷፫) ተሰነአለ=? ፷፬) ተቀበለ=? ፷፭) ተቀጸለ=? ፷፮) ተበቀለ=? ፷፯) ተንበለ=? ፷፰) ተአንተለ=? ፷፱) ተዐገለ=? ፸) ተከለ=? ፸፩) ተኬወለ=? ፸፪) ተወከለ=? ፸፫) ተድሕለ=? ፸፬) ተደንገለ=? ፸፭) ተዳወለ=? ፸፮) ተጋደለ=? ፸፯) ተፋወለ=? ፸፰) ንኅለ=? ፸፱) ነቀለ=? ፹) ነዐለ=? ፹፩) ነደለ=? ፹፪) ነጸለ=? ፹፫) አሕመልመለ=? ፹፬) ዐለለ=? ፹፭) አመስቀለ=? ፹፮) አማዕቀለ=? ፹፯) አማዕበለ=? ፹፰) አማእከለ=? ፹፱) አመድበለ=? ፺) አስተሰነአለ=? ፺፩) አቍጸለ=? ፺፪) አብዐለ=? ፺፫) ዐበለ=? ፺፬) አንሳሕለለ/አንዛሕለለ=? ፺፭) አንቀልቀለ=? ፺፮) አንበልበለ=? ፺፯) አንኮለለ=? ፺፰) አንጦለለ=? ፺፱) አከለ=? ፻) ዐዘለ=? ፻፩) ዔለ=? ፻፪) ዐገለ=? ፻፫) አገንጰለ=? ፻፬) አጰንገለ=? ፻፭) አጽለለ=? ፻፮) አጽደልደለ=? ፻፯) ክህለ=? ፻፰) ኵሕለ=? ፻፱) ከለለ=? ፻፲) ከፈለ=? ፻፲፩) ወዐለ=? ፻፲፪) ዝሕለ=? ፻፲፫) ዘለለ=? ፻፲፬) ዘበለ=? ፻፲፭) ዘወለ=? ፻፲፮) ደለለ=? ፻፲፯) ደበለ=? ፻፲፰) ገልገለ=? ፻፲፱) ገንጰለ=? ፻፳) ገደለ=? ፻፳፩) ጥሕለ=? ፻፳፪) ጠለ=? ፻፳፫) ጠቀለ=? ፻፳፬) ጤቀለ=? ፻፳፭) ጠብለለ=? ፻፳፮) ጸሐለ=? ፻፳፯) ጸለለ=? ፻፳፰) ጸለለ=? ፻፳፱) ጸበለ=? ፻፴) ጸንጸለ=? ፻፴፩) ጸዐለ=? ፻፴፪) ጽእለ=? ፻፴፫) ጸደለ=? ፻፴፬) ፈሐለ=? ፻፴፭) ፈልፈለ=? ፻፴፮) ፈተለ=? ፻፴፯) ፈደለ=? @beteyared21 @beteyared21 @beteyared21

#የግሥ #ጥናት #ክፍል #ሁለት    ግእዝ=አማርኛ ፩) ሐለለ=አረረ፣በራ፣ተቃጠለ ፪) ሐመለ=ለቀመ፣ቀነጠሰ ፫) ሐሰለ=ለበበ (የልጓም) ፬) ሐቀለ=ቀማ ፭) ኀበለ=ተደፋፈረ ፮) ሐበለ=ታታ ፯) ሐብለ=ዋሸ ፰) ሐንበለ=ጫነ (የኰረቻ) ፱) ሖለ=ቀላቀለ፣አደባለቀ ፲) ሐዘለ=አዘለ ፲፩) ኀየለ=በረታ ፲፪) ኄለ=መነጨ ፲፫) ሀጕለ=ጠፋ ፲፬) ሐፈለ=ቁንጥር ቁንጥር አለ (የስካር) ፲፭) መሐለ=ማለ ፲፮) መለለ=ላገ፣ጠረበ፣አለሰለሰ (የእንጨት) ፲፯) መምዔለ=ወነጀለ ፲፰) መሰለ=መሰለ ፲፱) መሰለ=ጣዖት ሠራ ፳) መበለ=ብልጭ አለ ፳፩) መዐለ=ወነጀለ ፳፪) መከለ=ቆረጠ ፳፫) ሞጽበለ=ሞረደ ፳፬) ሰሐለ=ሳለ (የብረት) ፳፭) ሳሕለለ=ደረቀ ፳፮) ሰመለ=አለዘበ (የጠባይ የእንጨት) ፳፯) ሰሰለ=ወገደ ፳፰) ሰቀለ=ሰቀለ ፳፱) ሰብለ=ዘረዘረ ፴) ሰንሰለ=አያያዘ፣አቆራኘ ፴፩) ሰአለ=ለመነ ፴፪) ሰከለ=አፈራ ፴፫) ሶለ=ሸተ፣ጮረቃ ፴፬) ሰደለ=መዘነ ፴፭) ሰገለ=ጠነቆለ ፴፮) ሰፈለ=መታ፣ቀጠቀጠ (የዱቄት የብረት) ፴፯) ረመለ=ጠነቆለ ፴፰) ሮለ=በሳ፣ቀደደ ፴፱) ረገለ=ቀዘፈ ፵) ቀለ=ቀለለ ፵፩) ቈልቈለ=ዘቀዘቀ ፵፪) ቈስለ=ቆሰለ ፵፫) ቀበለ=ሸኘ ፵፬) ቀብለ=ጎደለ፣አነሰ ፵፭) ቀተለ=ገደለ ፵፮) ቀፈለ=ለበጠ፣ሸለመ ፵፯) ብህለ=አለ ፵፰) በልበለ=አረጀ፣አለቀ (የልብስ) ፵፱) በሰለ=በሰለ ፶) በቈለ=በቀለ ፶፩) ብዕለ=ባዕለጸጋ ሆነ ፶፪) ቤዐለ=ወደደ ፶፫) በአለ=እንቢ አለ ፶፬) ቤወለ=ወደደ ፶፭) በጠለ=ጠፋ ፶፮) በጸለ=ቦጨቀ ፶፯) ትሕለ=ቀላወጠ ፶፰) ተልዕለ=ከፍ ከፍ አለ ፶፱) ተማሕለለ=ምሕላ ያዘ ፷) ተመዝጎለ=ተከራከረ ፷፩) ተሠሀለ=ይቅር አለ ፷፪) ተሰአለ=ተጠያየቀ፣ጠየቀ ፷፫) ተሰነአለ=ተስማማ ፷፬) ተቀበለ=ተቀበለ ፷፭) ተቀጸለ=ተቀዳጀ ፷፮) ተበቀለ=ቂም ያዘ፣ተበቀለ ፷፯) ተንበለ=ለመነ ፷፰) ተአንተለ=ቸል ቸል አለ ፷፱) ተዐገለ=ቀማ ፸) ተከለ=ተከለ ፸፩) ተኬወለ=ወደኋላ አላ ፸፪) ተወከለ=ታመነ ፸፫) ተድሕለ=ኮበለለ ፸፬) ተደንገለ=ተጠበቀ፣ድንግል ሆነ ፸፭) ተዳወለ=ተዳካ፣ተዋሰነ ፸፮) ተጋደለ=ተጋደለ ፸፯) ተፋወለ=አሟረተ ፸፰) ንኅለ=ፈረሰ ፸፱) ነቀለ=ነቀለ ፹) ነዐለ=ተጫማ ፹፩) ነደለ=በሳ ፹፪) ነጸለ=ለየ፣ነጠለ ፹፫) አሕመልመለ=ለመለመ፣አለመለመ ፹፬) ዐለለ=ጎለተ፣ርስት ጉልት አደረገ ፹፭) አመስቀለ=አመሳቀለ ፹፮) አማዕቀለ=ጥልቅ አደረገ ፹፯) አማዕበለ=ማዕበል አደረገ ፹፰) አማእከለ=መካከል አደረገ ፹፱) አመድበለ=አከማቸ ፺) አስተሰነአለ=አስማማ፣ተስማማ፣ ተሰነባበተ ፺፩) አቍጸለ=ለመለመ፣አለመለመ ፺፪) አብዐለ=አከበረ ፺፫) ዐበለ=አሰኘ ፺፬) አንሳሕለለ/አንዛሕለለ=አለ ዘለል አለ (ሥራ የመፍታት) ፺፭) አንቀልቀለ=ተነዋወጠ፣አነዋወጠ ፺፮) አንበልበለ=ነበልባል አደረገ ፺፯) አንኮለለ=ዱብ ዱብ አደረገ ፺፰) አንጦለለ=ለየ ፺፱) አከለ=በቃ፣ልክ ሆነ ፻) ዐዘለ=በረታ ፻፩) ዔለ=ዞረ፣ተንከረተተ ፻፪) ዐገለ=አቆመ፣በገረ፣አስበገረ፣ ደረደረ ፻፫) አገንጰለ=ጻፈ፣ገለበጠ ፻፬) አጰንገለ=ተረጎመ፣ጻፈ ፻፭) አጽለለ=አረፈ፣አሳረፈ ፻፮) አጽደልደለ=አበራ ፻፯) ክህለ=ቻለ ፻፰) ኵሕለ=ኳለ ፻፱) ከለለ=ጋረደ ፻፲) ከፈለ=ከፈለ ፻፲፩) ወዐለ=ዋለ ፻፲፪) ዝሕለ=ዛገ፣አደፈ፣ሻገተ (የወርቅ የብረት) ፻፲፫) ዘለለ=ጠመቀ፣ዘለለ (የጠላ) ፻፲፬) ዘበለ=ተናጻ ፻፲፭) ዘወለ=አቀለመ፣አጠቆረ ፻፲፮) ደለለ=ከፈከፈ፣ደለለ (የቤት የሰው) ፻፲፯) ደበለ=ሰበሰበ፣አከማቸ ፻፲፰) ገልገለ=ገላገለ ፻፲፱) ገንጰለ=ገለበጠ ፻፳) ገደለ=ጣለ (የጥንብ) ፻፳፩) ጥሕለ=አተለ (የሚያትል ሁሉ) ፻፳፪) ጠለ=ለመለመ ፻፳፫) ጠቀለ=በነገር ነካ ፻፳፬) ጤቀለ=ጻፈ ፻፳፭) ጠብለለ=ጠቀለለ ፻፳፮) ጸሐለ=ሠራ (የብረት) ፻፳፯) ጸለለ=ጋረደ ፻፳፰) ጸለለ=ተንኳፈፈ ፻፳፱) ጸበለ=ትቢያ ሆነ ፻፴) ጸንጸለ=መታ ፻፴፩) ጸዐለ=ሰደበ ፻፴፪) ጽእለ=ቆሰለ ፻፴፫) ጸደለ=በራ ፻፴፬) ፈሐለ=ቁንጥር ቁንጥር አለ ፻፴፭) ፈልፈለ=መነጨ ፻፴፮) ፈተለ=ፈተለ ፻፴፯) ፈደለ=ጻፈ                       ። ከBetremariam Abebaw  @beteyared21 @beteyared21 @beteyared21