uz
Feedback
መዝገበ እውነት Mezgebe Ewnet

መዝገበ እውነት Mezgebe Ewnet

Kanalga Telegram’da o‘tish

እንኳን ወደ መዝገበ እውነት በደህና መጡ... በመዝገበ እውነት ላይ ስለ ጥንታዊ የብራና መጽሃፍት፣ ስለ መጽሃፈ ሄኖክ ፣ስለ ኔፍሊሞች ፣ስለ ጥንታዊ ሰዎች ስልጣኔ፣ስለ የረቀቀ ቴክኖሎጂ፣ ስለ ስነ ከዋክብት እና መሬታችን ፣ ስለ ድብቅ ማህበራት ሴራ፣ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ፣ ስለ ቤተክርስቲያን እና መጽሃፍ ቅዱስ ወዘተ ያልተነገሩ እና ያልተሰሙ አስገራሚ ድብቅ እውነታዎችን በስፋት እንዳሣለን፡

Ko'proq ko'rsatish
5 440
Obunachilar
-424 soatlar
-137 kunlar
-6730 kunlar
Postlar arxiv
👆👆👆 ጥሩ ትምህርቶች ናቸው ቢደመጡ

ተመልከቱ! "የግብፆች ቅዳሴ 3 ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን 14 ቅዳሴዎች አሏት" ተብሎ በሌላ መምህር በተሰጠ ትምህርታዊ ቪድዮ ሥር የተሰጠ አስተያየት ነው። "ይኼ ኹሉ ቅዳሴ የዘለዓለም ሕይ
ተመልከቱ! "የግብፆች ቅዳሴ 3 ብቻ ነው። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን 14 ቅዳሴዎች አሏት" ተብሎ በሌላ መምህር በተሰጠ ትምህርታዊ ቪድዮ ሥር የተሰጠ አስተያየት ነው። "ይኼ ኹሉ ቅዳሴ የዘለዓለም ሕይወት ያሰጣል ወይ?" ብሎ ይጠይቃል። አይገርምም? የእግዚአብሔር የምስጋናው ድርሰቱ እንዲጠፋ ነው የሚፈልጉት። የዚህ የዚህማ፡ ግብፆችስ፡ ሦስት ቅዳሴ ምን ያደርግላቸዋል? አንድ አይበቃቸውም ነበር? የግብፅን ቤተክርስቲያን በኹሉ ነገር መለኪያችን እንድናደርግ የሚወተውቱን መናፍቃን ተሃድሶዎችና ካቶሊኮች ናቸው። ለግብፅም፥ ለኢትዮጵያም ቤተክርስቲያን እውነተኛ ፍቅር የላቸውም። እግዚአብሔርንም አይወዱትም። እነርሱ ያላቸው አንድ ነገር ብቻ ነው። እሱም ምሥጢራዊ ሰይጣናዊ አፍራሽ ተልዕኮ ብቻ!

(...ከላይ የቀጠለ) ከ15 ዓመታት በፊት፡ በፎረማቸው ከሚያደርጉት ውይይት እንደተረዳሁት፡ "British Zionism" የሚባለውን የተሃድሶ እንቅስቃሴ በቤተክርስቲያናቸው በጣም አለ። ተሃድሶ ማለት የፕሮቴስታንት ዛዮኒስት እንቅስቃሴ ነው። ጽዮናውያን፡ በኹለቱም ጽንፍ ይጫወታሉ። በአንደኛው ጽንፍክርስትናውን ትተው፡ ሙሉ ለሙሉ ወደኦሪቱ መመለስና የኦሪትን ነገሮች ከክርስቲያናዊ ትርጉማቸው ማላቀቅ ይፈልጋሉ። ለምሳሌ፡ ታቦተ ጽዮን፡ በኢትዮጵያ እንደሚደረገው፡ ከቅድስት ድንግል ማርያም እና ከልጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ተያይዛ እንድትተረጎምባቸው አይፈልጉም፤ ከኦሪት ሕግጋትና ከነቢያት ጋር ብቻ እንጂ። አሁን ያለው "የብሉይ ኪዳን ታቦትና የሐዲስ ኪዳን ታቦት የተለያየ ነው" የሚለው ወሬ፡ ለዚሁ ዓላማ የተፈጠረ ውዥንብር ነው። በሌላኛው ጽንፍ ደግሞ፡ ራሳቸው ጽዮናውያን (ተሃድሶዎች)፡ በ "ሐዋርያዊነት" ወይም በ"ሐዲስ ኪዳን" አሳበው፡ የብሉይ ኪዳን ትውፊቶችንና ሥርዓቶችን ይቃወማሉ፤ ማለትም ታቦትን፥ ግርዛትን፥ ቀዳሚት ሰንበትን፥ በኦሪት የተከለከሉ እንስሳትን አለመብላትን፥ ወዘተ...። ኹለቱንም ጽንፍ የሚጫወቱት እነሱ ናቸው። ኹለት ባሕሪ ማለት ይኽ ነው። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን፡ ብሉይን ከሐዲስ ሳትነጣጥል አስተባብራ ስለያዘች፡ አትመቻቸውም። ግብፆችን ግን የጓሮ ጎመናቸው አድርገዋቸዋል። ለዚያ ነው የነርሱን ፈለግ እንድንከተልና ብዙ ግራ መጋባቶቻቸውን እንድንወርስ የሚወተውቱን። እኛኑ መስለው፡ ከእኛ በላይ ለኦሪየንታል አብያተ ክርስቲያናት የተቆረቆሩ እያስመሰሉ፡ "ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት መነጠል የለብንም" ይላሉ። እውነታው ግን፡ የአኃት አብያተ ክርስቲያናትን በሙሉ "Reformed Global Christianity" በሚል የቫቲካን እና የእንግሊዝ ጽዮናውያን ዓለም አቀፍ የተሃድሶ "ክርስትና እምነት" ውስጥ ሊከቷቸው ስለሚፈልጉ እንጂ፡ ስለአንድነታችን ገዷቸው አይደለም። በመሠረቱ፡ ስለአንድነታችን መጨነቅ ያለብን እኛ ነን። ካቶሊክና ጽዮናውያን ተሃድሶዎች ምንም አያገባቸውም። ዛሬም፡ የተለያዩ አሰልቺና ተደጋጋሚ ጥያቄዎች በማምጣት፡ ነገረ ሃይማኖትን ለማራከስ የሚፈልጉ፡ በቤተክርስቲያን ተመሳስለው የቆሙ፡ ተሃድሶዎችና ካቶሊኮች ናቸው። በውጭው ዓለም እያለሁ፡ ከእኛው ጋ እያስቀደሱና እየቆረቡ፡ መልሰው ደግሞ "ወፈፍ" እያደረጋቸው የሚያነሡትን መከራከሪያ አስታውሳለሁ፦ - "መቅደስ ውስጥ ገብተው ልጆቻችን ሥርዓቱን ቢያዩ ምናለበት?" - "ለምንድነው የቤተመቅደሱ ሥርዓት በመጋረጃ የሚሸፈነው? ምሥጢር አድርጎ መያዝ ለምን አስፈለገ?" - "ቅዱስ ቁርባኑ በጠረጴዛ ተደርጎ ለምን አይቀደስም?" - "የግብጾችን ትርጓሜ ለምን አንማርም? የኢትዮጵያው ትርጓሜ ችግር አለበት" ወዘተ ይላሉ። እነዚህ፡ መናፍቅ ናቸው እንጂ፡ የተዋሕዶ እምነት ተከታዮች አይደሉም። Reformed Global Christianity የዐውሬው እንቅስቃሴ ነው። በአሁን ሰዓት፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ቅዱሳንና ሊቃውንት ከተነተኑልን ነገረ ሃይማኖትና ከሠሩልን ሥርዓት ውጪ፡ ሌላ ቁም ነገር ከሌላው ይገኛል ብላችሁ አታስቡ። እሱኑ የሚያጠናክር ከኾነ እሰየው። (እንደ ምሥጢራዊ የ Utopia ድርሰቶች)። ከኢትዮጵያዊው ሥርዓት የሚጻረር አስተሳሰብ ግን፡ በ"አኃት አብያተ ክርስቲያናት" ስም እየተከሸነ ቢመጣም፡ ምንጩ ቫቲካንና ጽዮናውያን መኾናቸውን መረዳት ያስፈልጋል። እነርሱ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ አኃት አብያተ ክርስቲያንን አታለሉና፡ እኛም "ስለአንድነት" ብለን የግድ ልንታለል አይገባም። ቢቻል ሌሎችን ከስኅተት ልንመልስ ያስፈልገናል። ካልኾነም፡ ከስኅተታቸው ለመመለስ ወደኛ የሚያማትሩበት ጊዜ ይመጣል። እስከዚያው፡ ብዙ የራሳችን የቤት ሥራ ስላለብን፡ እዚያ ላይ እናተኩር።

"Reformed Global Christianity" ምንድነው? ከዐሥራ አምስት ዓመታት በፊት፡ በአንድ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መወያያ ገጽ ላይ ገብቼ ጥያቄዎች ጠየቅሁ። "ለምንድነው ቤተክርስቲያናችሁ፡ ቅዳሴ ማርያምን የማትጠቀመው?" አልኩ። አንድ ካህን፡ "በውስጡ ያለው ምሥጢረ ሥላሴ ላይ ስኅተት ስላለበት ነው፤ ፖፕ ሽኖዳ ጥቅም ላይ እንዳይውል አግደዋል" አለኝ። "ደራሲው አባ አባ ሕርያቆስ እኮ ግብፃዊ ነው" አልኩት። "እኛ አናውቅም፤ ሊኾን ይችላል" አለኝ። "ግን፡ ቅዳሴ ማርያምን ባንቀድሰውም፡ አንዳንድ በዕድሜ ትልልቅ ሰዎች፡ እንደ ግል ጸሎት ያነቡታል" አለኝ። "ቅዳሴ ዮሓንስ ወልደ ነጎድጓድንስ፡ ለምንድነው የማትቀድሱት?" አልኩት። "እሱ የኢትዮጵያ ቅዳሴ ነው" አለኝ። "የኢትዮጵያ ስለኾነ ነው የማትፈልጉት?" ልለው ብዬ፡ ንግግራችን እንዳይሻክርና ሌላ ጊዜ ጥያቄ መጠየቅ እንዳያቅተኝ ተውኩት። በቅዳሴ ማርያም ውስጥ ከተገለጸው ምሥጢረ ሥላሴ ጋር ምን ችግር እንዳለባቸው ጥያቄ ኾኖብኝ ሳለ፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በኋላ፡ የአባ ተስፋ ሥላሴ ሞገሥን "ቅዱስ ማርቆስ ኢትዮጵያዊ ነው" የሚለውን መጽሓፍ አግኝቼ አነበብኩት። በዚያ መጽሓፍ ውስጥ፡ አባ ተስፋ ሥላሴ፡ ከአገር ውጪ በተካኼደ ውይይት፡ ከግብፅ ጋር፡ በምሥጢረ ሥላሴ እምነት ላይ፡ ልዩነት እየመጣ እንዳለ ጠቅሰው፡ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ይኽን ጉዳይ እንድትመረምረው ያሳሰቡበትን ክፍል አነበብኩት። በዚያ ክፍል ውስጥ፡ የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፡ ሥላሴ "ሦስት አካል አላቸው" ብላ እንደማታምን፡ "አካል ያለው ወልድ ብቻ ነው" እንደምትል ጠቅሰው፡ ሌሎቹ ግን በስማቸው ብቻ እንደሚጠቀሱ አስረድተዋል። ለዚህ ደግሞ፡ በአፀፋው፡ "አካል የሌለው ስም የለም፤ አካል የሌለው ስም፡ ዝርው ነው" የሚል ትንታኔ በምላሽነት ሰጥተዋል። አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስን፡ በፀሓይ መስሎ፡ በቅዳሴ ማርያም ያወደሳቸው አባ ሕርያቆስም፡ ግብፃዊ ሳይኾን፡ ኢትዮጵያዊ የዋልድባ አባት መኾኑን በመጽሓፋቸው ገልጸዋል። በዚህ መነሻነት፡ እየቆየሁ፡ አንዳንድ ነገሮችን ስታዘብ፡ በግብፅ ያለችው የካቶሊክ ቤተክርስቲያንም፡ እንደ Coptic ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፡ ሦስቱን ቅዳሴዎች ብቻ እንደምትጠቀም ተረዳሁ። "ኦርቶዶክሶቹ፡ ከካቶሊክ ጋር አንድ ዓይነት ለመኾን ብለው ነው ወይ፡ ከ14ቱ ቅዳሴያት፡ 11ዱን ትተው፡ሦስቱን ብቻ ይዘው የቀሩት?" የሚል ጥያቄም ፈጠረብኝ። * * * ወደ ኢትዮጵያ ከተመለስኩ በኋላ፡ አንድ ፀጋ እግዚአብሔር ያደረባቸውን እናት፡ በዚሁና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄዎች ጠየቅኋቸው። በግብፆች የሚሠሩ መንፈሳዊ ፊልሞችን እንደሚመለከቱና በጥቅሉ ጥሩ መኾናቸውን ገልጸው፡ ብዙ ነገራቸው ግን ወደካቶሊክ እየኼደባቸው መኾኑን እንደታዘቡ ገለጹልኝ። የቀድሞ ጥርጣሬዬን የሚያረጋግጥ ኾኖ ስላገኘሁት፡ ይበልጥ እንዲያብራሩልኝ ጠየቅኋቸው። ግብፆች ከካቶሊክ ለመመሳሰል እየኼዱ ያሉበት ርቀት፡ እዚህ ጋ ለመጻፍ የማይመቹ ብዙ ፈናዎችን እያመጣባቸው መኾኑን አብራሩልኝ። ብዙዎች ወደቅድስናውና ወደብቃቱ ከፍ ያሉ ግብጻውያን ግን፡ ይኽን ከካቶሊክ ጋ እየተደረገ ያለ አንድነት እንደማይወድዱትና የግብፅ ቤተክርስቲያን ብዙ ፈተና ውስጥ እየገባች እንደምትመጣ አስቀድመው እንደሚያውቁ፤ ከዚህም የተነሣ፡ ተስፋቸው የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እንደኾነች ገለጹልኝ። ብዙዎች ሥውራንም የሚመጡት፡ ወደ ኢትዮጵያ ገዳማት እንጂ፡ ወደ ሮም እንዳይደለ አሳሰቡኝ። * * * ይኽን እያሰብኩ፡ ወደኋላ፡ በግብፆቹ መወያያ ፎረም አንብቤያቸው የነበሩትንና በወቅቱ ገርመውኝ የነበሩ አንዳንድ ጉዳዮችን ማስታወስ ጀመርኩ። "እኛ የግብፅ ኦርቶዶክሶች፡ ለምንድነው አይሁድንና ከአይሁድ ጋ የተያያዘ ነገርን ኹሉ የምንጠላው?" የሚል ጥያቄ አንዱ አንሥቶ፡ በሥሩ የተጻፉለትን መልሶች ለማስታወስ ሞከርኩ። "እኔም ይገርመኛል" ብሎ ሌላኛው መለሰለት። "ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አይሁዳዊ ነው፤ እናቱ ድንግል ማርያም፥ ወንድሞቹና ደቀመዛሙርቶቹም፡ አይሁዶች ኾነው በአይሁድ እምነትና ትውፊት ያደጉ ናቸው። እኛ ግን፡ ቤተክርስቲያናችን 'አይሁዳዊት' (Judaiser) ሳትኾን 'ሐዋርያዊት' ናት እንላለን፤ የአይሁድ ልማዶችንም በጣም እናወግዛለን፤ ሐዋርያት ራሳቸው አይሁዶች መኾናቸውን ረስተናል..." እያለ የመለሰውን ምላሽ ማንበቤን አስታወስኩ። ይኽ ክርር ያለ የአይሁድ ልማዶችን ያለመውደድ ዝንባሌ (ለምሳሌ፦ ግርዛትን መቃወም፥ ቅዳሜን እንደሰንበት አለማክበር፥ የሚበሉና የማይበሉ ምግቦች አለመለየት፥ ወዘተ...) በራሷ በግብፅ ቤተክርስቲያን ውስጥ እንዴት ሥር እንደሰደደ እንኳ እንደማያውቁና ለምን እንደዚያ ሊኾን እንደቻሉም መልስ እንደሌላቸው ነው፡ በወቅቱ የተረዳሁት። * * * እያደር ግን መልስ አግኝቻለሁ። ጥንት፡ በግብጽ ያለው ክርስትና፡ ከኢትዮጵያዊው ክርስትና ጋር ልዩነት አልነበረውም። ምክንያቱም፡ የእስክንድርያው መንበር መሥራች፡ ቅዱስ ማርቆስ፡ ኢትዮጵያዊ ነው። በእስራኤል በአይሁድ እምነት ከነበሩ ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች የተገኘ ነው። ብዙዎች የመጀመሪያዎቹ ሊቃውንት፡ ወይ ሙሉ በሙሉ (እንደ አትናቴዎስ)፥ አልያም በከፊል (እንደ ዲዮስቆሮስ)፡ ኢትዮጵያውያን ናቸው። በአስቄጥስ ገዳም የነበሩ መናንያንም፡ ብዙዎቹ ኢትዮጵያውያን ነበሩ። ቁስቋምም በቀጥታ የኢትዮጵያውያን መናንያን ይዞታ ነበረች። ስለኾነም፡ ግብጽ ውስጥ ያለችው ቤተክርስቲያን እና፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለችው ቤተክርስቲያን ማለት፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለችው ቤተክርስቲያን እና ኤርትራ ውስጥ ያለችው ቤተክርስቲያን ማለት ናቸው። ወይም፡ ጎንደር ውስጥ ያለች ቤተክርስቲያን እና፡ ሸዋ ውስጥ ያለች ቤተክርሰቲያን ማለት ናቸው። የሚለያቸው ድንበር ብቻ ነው። በእምነትም፥ በትውፊትም አይለያዩም ነበር። እያደር ግን፡ የግብፅ ቤተክርስቲያን፡ በካቶሊክ አስተሳሰብ ክፉኛ ተመርዛለች። በአሕዛብም ብዙ ይዞታዎቿ ተነጥቀው፡ ብዙ ጊዜም ምዕመኖቿ እየተገደሉና ጳጳሳቷ እየታሠሩ፡ የቁጥር መመናመንና የሥርዓት መፋለስ ገጥሟቸዋል። ቢኾንም፡ የኢትዮጵያ ነገሥታት በተለያየ ጊዜ እየዘመቱና እየተዋጉ ነፃ አውጥተዋቸዋል። ይዞታዎቻቸውንም ያስመልሱላቸው ነበር። የእምነት ውይይትና የመጻሕፍት ልውውጥም ስላለ፡ በአብዛኛው በመሠረታዊ ዶግማዊ ጉዳዮች ላይ፡ ሳይነጣጥሉ ቀጥለዋል። አሁን ግን፡ ልዩነቱ ከዚህም በላይ እየሰፋ እንዳይመጣ ያሠጋል። አሁን ያለው "የኢትዮጵያን ቅዳሴ አንፈልግም" የሚለው ካቶሊካዊ አቋማቸው መቼ እንደተፈጠረ እንጃ። የብሉይ ኪዳን መሠረት ያሏቸውን ትውፊቶችና ሥርዓቶችንም "ቤተክርስቲያን ሐዋርያዊት እንጂ አይሁዳዊት አይደለችም" በማለት ይቃወሟቸዋል። ቀዳሚት ሰንበትን ከማክበር ወደአለማክበር ከመጡ ሰነባብተዋል። "እኛ የጌታን ቀን እሑድን እንጂ የአይሁድ ሰንበትን አናከብርም" ይላሉ። ከዚያ ይልቅ፡ "ኹሉም ቀናት የጌታ ናቸውና፡ እለት እለት ለጌታ ስለመኖር ማሰብ አለብን" የሚል የተድበሰበሰ መልስ በመስጠት፡ የቀዳሚት ሰንበትን ነገር ማለፍ ይቀናቸዋል።

ቅዳሴው ወደፊት እንደዚህ እንዲሆን ነው የሚፈልጉት https://youtu.be/PnQVH4eKpT0?si=h1MoOLgXIf4EVXKn

ቅዳሴው፡ ከቅድስተ ቅዱሳኑ ውጪ፡ ፊት ለፊት፡ ሕዝቡ ፊት እንዲኾን፤ የመሥዋዕቱ ኅብስት፡ በጠረጴዛ ላይ፡ እንደ አምባሻ ወይም እንደዳቦ፡ ፊት ለፊት እንዲቀመጥ፥ ሙሉ ቅዳሴው ሲቀደስ፡ ሕዝብ እያየው እንዲቀደስ፤ በቁርባን ሰዓት፡ ካህናቱና ዲያቆናቱ፡ ሕዝቡ ፊት ከኅብስቱ ቆርሰው እንዲበሉ፤

"በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ያለውን ታቦት አንፈልግም፥ በውጭ ቅድስቱ ላይ ያለውን ጠረጴዛ ብቻ ነው የምንፈልገው" የሚሉት፡ "ገና በውጪ ያለን፥ በእኛና በእግዚአብሔር መካከል ያለው የኃጢአት መጋረጃ ያልተቀደደልን፥ ከሊቀ ካህናቱ ከክርስቶስ ጋር በሰማያት በአብ ቀኝ ያልተቀመጥን፥ ውስጣዊ ልቦናችንን በሰማይ ያላኖርን፥ በኖኅ መርከብ ውስጥ፡ ከታች ከእንስሳትና ከአራዊት ጋር ያለን፥ ወደላይኛው ክፍል ግን ወደታቦቱ ያልገባን፥ መንፈሳዊ የልቦና ክፍል የሌለን፥ ለምሥጢር ያልበቃን ንዑሰ ክርስቲያኖች ነን" እያሉ በራሳቸው ላይ ምንፍቅናቸውን እየመሠከሩ ነው።

ሃይማኖታቸው ተዋህዶን መጠሪያቸው ውስጥ ለምን አያስገቡበትም? ኦርቶዶክስ ብቻ መጠሪያ አይሆንም አይሁድም ኦርቶዶክስ አለው እስላምም ኦርቶዶክስ አለው እኮ።
ሃይማኖታቸው ተዋህዶን መጠሪያቸው ውስጥ ለምን አያስገቡበትም? ኦርቶዶክስ ብቻ መጠሪያ አይሆንም አይሁድም ኦርቶዶክስ አለው እስላምም ኦርቶዶክስ አለው እኮ።

የዘመኑ ተሃድሶዎች እና የካቶሊክ ምልምል የቤተክርስቲያን አስተማሪዎች የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን ከ አኃት አብያተ ከሚሏቸው ጋር ማወዳደር ከዛም የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያንን ብዙ አላስፈላጊ ነገር ጨማምረን ይዘን እንደምጓዝ ለማስተማር ይፈልጋሉ... የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከብሉይ ዘመን ጀምራ የሰበሰበቻቸው የመጻህፍት፣ በስርዓት ፣ በትውፊት ፣ የአለባብሰ የአመጋገብ ስርዓቶች ብቻ ሁሉም ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ልማዶች ሁሉ ምንም ጥቅም የላቸውም ይላሉ፣ አኃት የሚባሉት ከሌሏቸው እኛም ጋር ሊቀሩ ይገባል የሚል አደገኛ፣ ባህልን ፣ ታሪክን እና ማንነትን የሚያጠፋ አስተምህሮ ይዘው በሰፊው ያስተምራሉ... ይህንን ካስጣሉ ቡሃላ ሁላችንም አኃት አንድ ነን እንቀላቀል ይላሉ... ቀጥለው ኦርቶዶክስ ሁሉም አንድ ነው ብለው (ከከሃዲዎቹ ከነሩሲያ ከነግሪክ ) ጋር ያቀላቅላሉ.... በስተመጨረሻም ከካቶሊክ ጋርም ልዩነት የለንም ብለው የአንድ ሃይማኖት ስርዓትን ( ecumenism ) ለማምጣት ቀላል ይሆንላቸዋል ማለት ነው... ይህንንም ለማሳካት አኃት የሚባሉት ሁል ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከመቅረብ ይልቅ ከካቶሊክ ጋር ለመቀራረብ ከፈተኛ ጥረትን ያደርጋሉ..... እንደ እውነታው ከሆነ ግን አኃት የሚባሉት፣ ከኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቢማሩ... ስርዓትን ሊወስዱ፣ የጎደላቸውን መጻህፍት ወስደው ቢሞሉ፣ ሌሎች ሌሎች የጎደሏቸውን ስርዓቶች ሞልተው እራሳቸው ቢያሳድጉ ጥሩ ነው ... ሲጀመርም በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እና አኃት የሚባሉት ጋር ያለው የሃይማኖት ርቀት ሲታይ የአያት እና የልጅ ልጅ እንጂ ትክሻ ለትከሻ የሚያስለካካ የእህትነት ደረጃ ራሱ የላቸውም... እስኪ አኃት ቤተክርስቲያን የሚባሉት እውነተኞች ከሆኑ ልክ እንደ ኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የሚያምኑበትን ሃይማኖት ይጠሩበት... ስማቸው ውስጥ ተዋህዶ የሚለውን በቋንቋቸው ተርጉመው ይክተቱ እና ይጠሩበት እስኪ.... እስኪ ከኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ጋር በሃይማኖት አንድ ከሆኑ እነ መጽሐፈ ሄኖክን እና መጽሐፈ ኩፋሌን የመሳሰሉትን መጻህፍት ወስደው ከመጽሐፍ ቅዱሳቸው ውስጥ እስኪ ይጨምሩ

እኔ እንደተረዳሁት ከሆነ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓቷ እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ አይደለም ከጥንት ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ ሲያያዝ የመጣ ሲሆን፤የሌሌቹ ግን በሐዲስ ኪዳን የጀመረ ነው ስለዚህ ሥርዓታችን፣ወጋችን ሊመሳሰል አይችልም።እናም እንደለመዱት የእነሱን ብቻ ትክክል ብቻ እንደሆነ እንድናስብ እና የኛውን ሥርዓት ቆርጠን በነሱ ልክ እንድንሰፋው ይፈልጋሉ፣ካዛ እኛ ስንጥለው እነሱ ሊያነሱት ማለት ነው😂😂😂።ታቦትን በመሠዊያ ለመተካት የተፈለገበት ዋና ዓላማ ታቦተ ጽዮንን እሷ እኮ የብሉይ ኪዳን ታቦት ናት አሁን ላይ ጥቅም የላትም ብልው እኛን ለማስጣል እና እነሱ ለመውሰድ ነው።እድሜ ላንቺ መምህርት አሁንማ ነቅተናል።እኛ ከሌሎች አኃት አብያተ ክርስቲያናት ጋር ስርዓታችን ስለማይመሳሰል ቆርጠን የምንጥለው ነገር የለንም ምክንያቱም the latest version የእኛው ነው ከፈለጉ እነሱ የጎደላቸውን እየሞሉ ወደኛ ይደጉ።

የቀደመውን የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ታሪክ ጨርሶውኑ ለማጥፋት ነው። አባቶቻችን ያስረከቡንን ህያው ምስክር በማጥፋት ጥንታዊ ነን ብለው የታሪክን ይዘት ወደ ራሳቸው ለመገልበጥ እንዲመቻቸው ነው። አንድም ዓለም ኢትዮጵያን ከታሪክ መዝገብ ካወጣትና ከረሳት። ታቦተ ጽዮንንም በቀላሉ የግላቸው ለማድረግ።

እኛ ታቦቱን ስናስብ በፊቱ መስገድ እንዳለብን፣ በፍርሐት መቆም እንዳለብን ፣ እናስባለን ። እንሰግዳለንም። ታቦት በሌላቸው እንደ ካቶሊክ ዐይነት አቢያተ ክርስቲያናት ግን ማንኛውም ሰው ከነጫማው ሳይቀር ፣ በልቶም ሳይበላም እንደፈለገ ይገባል፣ ይወጣል። እንደውም በአውሮፓ የምናያቸው የካቶሊክ አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ ቀን ክፍት ናቸው። ግን ማን ጧት ጧት እየተነሳ የሚከፍታቸው ይመስላችኋል? የሚከፍተው የመንግሥት አካል / የቀበሌ ፖሊስ ነው። ምክንያቱም ቦታዎቹ ለአምልኮ ሳይሆን ለጎብኚዎች ተከፍተው የሚውሉ ናቸው። የሚያምንም የማያምንም በማንኛውም ሰዓት ገብቶ ይጎበኛል፤ አንዳንዱ ሻማ ያበራል፣ አንዳንዱም ዝም ብሎ አረፍ ብሎ ይወጣል። መቅደሱ ከ አምልኮና ጸሎት ቤትነት ወደ ተራ የሕዝብ ንብረት (በመዘጋጃ ቤት የሚተዳደር ሁኗል)። በካቶሊክ አማኞች ቁጥጥር ያሉት አብያት ክርስቲያናትም ተገልጋይ ምእመን ስለጠፋ በየጊዜው ለሽያጭ እየቀረቡ ናቸው። እኛንም አሁን ታቦትን ጠረጲዛ አስደርገው፣ ፈሪሐ እግዚአብሔርን በመጀመሪያ ከውስጣችን እንድረሳ ካስደረጉን በኋላ፣ ቀስ እያለ ሁሉም እየተደፋፈረ ሲመጣ ቅዱስ ቁርባኑም ምሳሌ ነው፣ ብትቀበለው ባትቀበለው ባንተ ላይ ምንም ለውጥ አያመጣም ወደሚሉት አለማምደው ወደ ለየለት ክህደት ሊጨምሩን ይመስለኛል።

የእግዚአብሔርን ማደሪያ ከማደሪያው ለይቶ ቤተክርስቲያንን ከእግዚአብሔር ኃይልና ጥበቃ ለማውጣትና ክርስቶስ የሌለበት ግን የሚመስል ክርስትና የመፍጠር ጉዞ ነው።