መዝገበ እውነት Mezgebe Ewnet
Открыть в Telegram
እንኳን ወደ መዝገበ እውነት በደህና መጡ... በመዝገበ እውነት ላይ ስለ ጥንታዊ የብራና መጽሃፍት፣ ስለ መጽሃፈ ሄኖክ ፣ስለ ኔፍሊሞች ፣ስለ ጥንታዊ ሰዎች ስልጣኔ፣ስለ የረቀቀ ቴክኖሎጂ፣ ስለ ስነ ከዋክብት እና መሬታችን ፣ ስለ ድብቅ ማህበራት ሴራ፣ ስለ ሃገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ ፣ ስለ ቤተክርስቲያን እና መጽሃፍ ቅዱስ ወዘተ ያልተነገሩ እና ያልተሰሙ አስገራሚ ድብቅ እውነታዎችን በስፋት እንዳሣለን፡
Больше5 376
Подписчики
+224 часа
-127 дней
-4730 день
Архив постов
+2
የጥንት የእስራኤላውያን ዘንድ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ወደ ጦርነት የመዝመት ልምድ ነበራቸው እነዚሁ እስራኤል በኢትዮጵያ ምድር ሲኖሩ ያንኑ የቀደመ ልማዳቸውን በመከተል በጦርነት ጊዜ ታቦትን ይዘው ሲዘምቱ ይታያል...
እነዚህ እና ሌሎችም በጣም ብዙ የኢትዮጵያውያን ባህሎች እና ልማዶች ስር መሠረታቸው መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንደሆ እንጂ ከጊዜ ቡሃል የተጨመሩ ወይ ከሌላ ሰዎች በትምህርት የተወረሱ እንዳይደሉ ያረጋግጡልናል። ኢትዮጵያውያን እነዚህን ልማዶችን ወደ ሃገራቸው ከገቡ ጥቂት ሰዎች ተምረውት ሳይሆን ቀድሞም ይኖሩበት የነበረ የራሳቸው ማንነታቸው መገለጫ እንደነበሩ ነው።
+1
ብዙ ኢትዮጵያውያን ከእመቤታችን ቀጥሎ ለቅዱስ ሚካኤል ጥልቅ የሆነ ፍቅር እና አክብሮት አላቸው ይሄ አክብሮት ከባዶ የመነጨ ሳይሆነ በጥንት ጊዜ ለእስራኤል ጠባቂ ሆኖ የተሾመው እስራኤልንም ከጠላት ሲጠብቅ የኖረ መልአክ በመሆኑ ያ ታሪክ በህዝቡ ውስጥ ውስጥ በመኖሩ የተነሳ ነው...
አሁን እይሁድ ነን የሚሉትን ፈረንጆች እንኳን በወርሃዊ እና በዓመታዊ በዓላት ሊያከብሩት ቀርቶ ስሙን እራሱ አያውቁትም። ይሄ የሚያሳየው የጥንቱ የእራኤል ባህል የአሁኖቹ ኢትዮጵያውያን ባህል መሆኑን እንጂ የፈረንጆቹ እንዳልሆነ ነው።
+1
የተጣላ ሰውን ለማስታረቅ እና ለትዳር ሽማግሌዎሽን መላክ መነሻው ሥላሴ ወደ አብርሃም ቤት የመግባታቸው ነው። ይሄም ልማድ በኢትዮያውያን ዘንድ የተለመደ በአሁኖቹ የሃተኞቹ እስራኤላውያን የሌለ ነው፣ ይሄም የመጽሐፍ ቅዱሱ ታሪክ የኢትዮጵያውያን እንጂ የፈረንጆቹ እንዳይደለ ያስረዳልናል
ከላይ ካየናቸው ተጨማሪ በእስራኤላውያን ዘንድ ብቻ የሚፈጸሙ ሌሎች ህዝቦች ተምረው ሊፈጽሟቸው ከማይችሏቸው ልምዶች እና ባህሎች መካከል።
ሌላው ትልቅ ማስረጃ በኢትዮጵያ የሚገኙት ቤተ እስራኤላውያን ናቸው... ቤተ እስራኤላውያን በቀጥታ በዘር እስራኤላዊ እንደሆኑ ሁለም የሚያምነው ሲሆን እነዚህን ሰዎች በመልክ፣ በአለባበስ ፣ በቋንቋ ከሌላው ኢትዮጵያዊ የሚለያቸው ነገር ሳይኖር እነሱ በዘር እስራኤላዊ ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ እስራኤላዊ የማይሆንበት ምንም ምክንያት የለም።
በታሪክም ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ ከመግባቱ በፊት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልክ እንደ አሁኖቹ ቤተ እስራኤላውያን በኦሪት ብቻ በመከተል ሲኖር የነበረው... ክርስትና ከገባ ቡሃላ ግን ክርስትናን ያልተቀበሉት ቤተ እስራኤል ተብለው ሲጠሩ ፣ ክርስትናን የተቀበሉት ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ተብለው መጠራት ጀመሩ እንጂ ቤተ እራኤላውያን ከሌላው ክርስትናን ከተቀበለው ህዝብ ጋር ምንም አይነት የዘር ልዩነት የላቸውም።
+2
እኛ ኢትዮጵያውያን የጥንቶቹ እስራኤላውያን መሆናችንን በዐይን የሚታይ፣ በእጅ የሚዳሰስ፣ በመጻህፍት የሚመሰከር፣ በታሪክ የሚረጋገጥ እውነት ኖሮን ሳለ... እነዚህ ፈረንጆቹ ሱፋቸውን ገድግደው ይመጡና አንድ የታሪክ ማስረጃ ሳይኖራቸው እኛ ነን የጥንቶቹ እስራኤል ሲሉን አዎ ብለ እንቀበላልን።
በተመሳሳይም የኢትዮጵያውያን ባህል የሆነው፣ ሰው መንገድ ሲሄድ መሸኘት መገኛው ከመጸሕፍ ቅዱስ አዳም ከገነት ሲሰደድ አአዋፍ እና አንስሳት ሸኝተውት እንደተመለሱ በማስታወስ ነው።
እነደነዚህ አይነት በኢትዮጵያውያን ዘንድ በጣም ስር የሰደዱ መጸሕፍ ቅዱሳዊ ባህሎች ምንጫቸው ቀድሞም የኢትዮጵያ ህዝብ ማለት ኦሪትን እና መጽሐፍ ቅዱስን የተሰጡት እውነተኞቹ እስራኤል ሰልሆነ ነው እንጂ ከውጪ የመጡ ጥቂት ሰዎች የሚያስተምሩት ትምህርት የተኝኙ አንዳልሆኑ ማረጋገጥ ይቻላል።
ጥቃቅኑ የኢትዮጵያውያን ባህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ የሚያስረዳን በመጽሐፈ አክሲማሮስ ላይ አዳም ሄዋን ባሳሳተችው ጊዜ እንጨት አንስቶ አማታለሁ ሲል ዘላ ከአትክልት ውስጥ ተደበቀች እሱም ተከትሎ ገብቶ አልመታትም... ይሄ መጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ዘንድ አስካሁን ልምድ ሆኖ አለ ባል እና ሚስት ሲጣሉ ባል ሊማታ ሲል ሚስት ወደ ማጀት ከገባች ባል ተከትሎ ገብቶ አይማታም ይሄም ልምድ ሆኖ እስካሁን አለ።
+1
በጥንት እስራኤላውያን የሚደረጉ ህግ ያልወጣላቸው በመጽሐፍ ያልተጻፉ ልምዶች ሁሉ በኢትዮጵያውያን ዘንድ መደረጋቸው ኢትዮጵያውያን ኦሪትን ከሊሎች ሰዎች በትምህርት ተምረውት ሳይሆን ቀድሞውንም የራሳችን ባህሎች መሆናቸውን የሚያሳይ ነው።
+1
ጉልባን እስራኤላውያን ከባርነት በወጡ ጊዜ አቡክተው፣ ጋግረው መብላት አለመቻላቸውን ያስታውሰናል። በወቅቱ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መመገብ፤ ንፍሮ ቀቅለው ስንቅ መያዝ የመንገድ ተግባራቸው ስለሆነ ይህን ታሪክ ለማሰብም ጉልባን እና ንፍሮ በኢትዮጵያውያን ባህል የተለመደ ነው፣
የራሳቸው ታሪክ ካልሆነ ኢትዮጵያውያን ይሄንን መዘከር ምን ያደርግላቸዋል ?
የዮፍታሄ ታሪክ እና ያአሸንዳ ባህል መገናኝት፣ እስራኤላውያን ላልሆኑት ኢትዮጵያውያን ይሄንን በዓል ማክበር ምን ያደርግላቸዋል የራሳቸው ታሪክ ካልሆነ በስተቀር?
1. ኢትዮጵያውያን የኦሪት ስርዓትን የሚፈጽሙት ወደ ሃገራቸው ከመጡት እስራኤላውያን ተምረውት እንደሆነ አስረግጦ የሚናገር ነው።
እንደ ክብረ ነገሥቱ ታሪክ መሠረት ኢትዮጵያ ህገ ኦሪትን የተቀበለችው ከሰሎሞን ጋር የመጡት 12,000 የእስራኤላውያን የበኩር ልጆች ምክንያት መሆኑን ለማስረዳት ይሞክራል።
ከላይ በጥቂቱ ለማንሳት እንደሞከረነው የኦሪት ህግጋት እና ስርአት የተሰጡት ለእስራኤላውያን ብቻ እና ብቻ ነው፣ ሌላው የዓለም ህዝብ ይህንን ህግ እና ስርዓት የመከተል ምንም ግዴታ የለበትም፣ የኦሪትን ህግጋት እና ስርዓት የሚሰበኩ፣ ወደ ሌላው ህዝብ የሚተላለፉ አይደሉም። የብሉይ ኪዳን መጻህፍትም ይህንን እውንት ይመሰክራሉ።
ክብረ ነገሥት ግን የኢትዮጵያውያ የኦሪት ህግጋትን መከተል ምንጩ ከሚኒሊክ ጋር በመጡት 12,000ዎቹ የበኩር ልጆች ምክንያት ነው ይላል። ይሄ ፈጽሞ ከብሉይ መጻህፍት እና ሌሎች የታሪክ ተመራማሪዎች ግኝቶች ጋር የሚቃረን ነው።
እዚህ ላይ ብዙ ጥያቂዎች ሊነሱ ይችላል
* እስራኤላውያን በስደት በግብጽ፣ በባቢሎን እና በተለያዩ ሃገራት የሲኖሩ ሲሆን ኦሪትን አስተምረው አህዛብን ቀይረው አያውቁም እንደውም እነሱ ጣኦት ማምለክን ይማራሉ እንጂ፣ ወደ ኢትዮጵያም ሲመጡ ሊሆን የሚገባው ይሄ ነበር
* እስራኤላውያን ለ4,500 በብሉይ ዘመን ሲኖሩ፣ የእስራኤልን ባህል ተምረው ወደነሱ ማህበረሰብ የተቀላቀሉ በጣም ጥቂት በጣት የሚቆጠሩ ሰዎች ብቻ ናቸው (ረዓብ ፣ ሩት እና ኬጢያዊው ኦርዮ ናቸው)፣ ሙሉ ማህበረሰቦችን ቀይረው አያውቁም
* 12000 ሰዎች እስራኤላውያን መጥተው ከሆነ የራሳቸውን ኦሪት እራሳቸው ይከተሉታል እንጂ ለሌላው ኢትዮጵያዊ አያስተምሩም ነበር ለምሳሌ ግርዛት ለአብርሃም ዘር የተሰጠ ነው ታዲያ ኢትዮጵያውያን የአብርሃም ዘር ሳይሆኑ ቢገረዙ ባይገረዙ ምን ያደረግላቸዋል? የሚበሉ እና የማይበሉ ነገሮችን መምረጥ እስራኤላዊ ላልሆኑት ለኢትዮጵያውያን ምን ያደርግላቸዋል? እስራኤል ከግብጽ የወጡበትን የፋሲካን በዓል ማክበር ለኢትዮጵያውያን ምናቸው ነው?
* 12000 ሰዎች እንዴት የአንድን ሃገር ማህበረሰብ ልማድ እና ባህል ሙሉ ለሙሉ ሊቀይሩ ይችላሉ?
* ኢትዮጵያውያን በዚህ መልኩ ኦሪትን ከተማሩ ቀድሞ ከነበራቸው የጣኦት አምልኮ ጋር ቀላቅለው ሲፈጽሙት ይታያል እንጂ ሙሉ ለሙሉ የቀድሞውን ትተው ኦሪትን ብቻ ሲፈጽሙ አይገኙም ነበር
* ኢትዮጵያውያን 12000 ሰዎች ኦሪትን ተማሩ ካልንም ከላይ ከላይ ያሉትን ዋና ዋና ህግጋት ይማራሉ እንጂ በባህላቸው ውስጥ ስር በሰደደ መልኩ አይማሩም አይፈጽሙትም ነበር...
ዋና ዋናዎቹን የኦሪትን ህግጋት እና ስርዓትን (ታቦተ ጽዮን ፣ የኦሪት መጻህፍት መኖር፣ የሰንበት አከባበር ፣ የሚበሉ እና የማይበሉ እንስሳት መለየት ፣ ግርዛት ፣ የበዓላት አከባበር፣ የቤተ ክህነት መገልገያ እቃዎች እና ስርዓት፣ የዜማ መሳሪያዎች (በገና ማሲንቆ)፣ ) ሁሉ ትተን ጥቃቅን የኦሪት እና የመጽሐፍ ቅዱሳዊ ልማዶች በኢትዮጵያውያን ባህል ምን ያህል ስር የሰደዱ እንደሆነ እንመልከት
