ግጻዌ
የየዕለቱን ግጻዌ የቅዳሴ ጊዜ ምንባባትና ምስባክ በዚህ ቻናል ያገኛሉ።
Ko'proq ko'rsatish9 462
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
-217 kunlar
-6130 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
Photo unavailableShow in Telegram
እጅህ ላይ ባለው ነገር ከታመንህ እግዚአብሔር አምላክ በእጁ ውስጥ ያለውን ነገር ይሰጥሃል።
በውስጥህ ያለውን አቅም መጠቅም ከቻልህ እግዚአብሔር የአንተ ያልሆነ ተጨማሪ አቅም ይሰጥሃል።
ከእግረኞች ጋር ሳትደክም እኩል መራመድና መቅደም ከቻልህ እግዚአብሔር ፈረስን ለውድድር ይሰጥሃል። ኤር. 12፥5
የሚታዩ ኃጢአቶችን ለመዋጋት ታምነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የተሸሸጉና የማይታዩ ኃጢአቶችን ድል እንድትነሣ ይሾምሃል።
በሕፃንነትህ በልጅነትህ ለእግዚአብሔር የታመንህ ሆነህ ከተገኘህ እርሱ በወጣትነትህ በምታደርገው ውጊያ ውስጥ ታማኝነትን ያድልሃል።
በሲና ምድረ በዳ ለመቀመጥ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር አምላክ የተስፋይቱን ምድር ከንዓንን ያወርስሃል።
በዚህ በተወሰነና አጭር ሕይወት ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር መጨረሻ የሌለውን ዘላለማዊ ሕይወት ያድልሃል።
ትልቁ ቁም ነገር በእጅህ ውስጥ የገባው ነገር ትንሽም ይሁን ጥቂት በእርሱ መታመን መቻልህ ነው። ስለሆነም ባለህ አንድ መክሊት ታምነህ ስትገኝ እግዚአብሔር አምስት መክሊቶችን በአደራ ይሰጥሃል።
አንተ በሚታዩት ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ እርሱ በማይታዩት ነገሮች ላይ ይሾምሃል።በመሆኑም ዓይን ያላየችውን ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልብ ያልታሰበውን መንግሥቱን ያወርስሃል። 1ኛ ቆሮ 2፥9
(#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ)
❤ 17
+ "እንዳትበድል አትቅና" +
............................................................
የሰው ልጅ በፍጹም አምኖ ሊቀበል የማይችለው ነገር ቢኖር መቅናቱን ነው። መንፈሳዊ ቅንዓት ከሆነ ቀንቻለሁ ማለት ላይከብድ ይችላል። ያ ምቀኝነት የተሞላበት ሰይጣናዊ የሆነው ቅንዓት የያዘው ሰው ግን ቅንዓቱን በፍጹም ቅንዓት ብሎ refer ሊያደርገው አይችልም።
ቅዱስ ዳዊት "እንዳትበድል አትቅና" ብሎ የተናገረው ቅንዓት በጊዜው በቁጥጥር ሥር ካልዋለ ለብዙ በደል መጀመሪያ እንደሆነ ሲነግረን ነው። ሰዎች ከእኛ ሲበልጡ እያዩ ለእነርሱ በሙሉ ልብ መደሰትና አለመረበሽ መቻል ትልቅ ጸጋ ነው። እውነተኛው ትሁት ልብ ያለው ሰው ካልሆነ በቀር ማን ከሰው ማነሱን አምኖ የሚቀበል አለ? ሰዎች ከእኛ በላይ ጸጋ፣ ሀብት፣ ሞገስን ሲያገኙ አለመቅናት መቻል ትልቅ መንፈሳዊ ማንነት ይጠይቃል።
ምን ይደረግ ይህ ትህትናና መንፈሳዊ ማንነት ስለሌለን ግን ሰዎች ከእኛ በልጠው ስናይ የሚቀላ እንጂ የሚፈካ ዓይን ብዙዎቻችን የለንም። ቅዱስ ዳዊት ቅናት ለብዙ በደሎች መግቢያ በር እንደሆነ ስለነገረን ታዲያ እንዴት በሩን እንዝጋው?
1) መቅናታችንን ማመን!
ከራሱ ጋር እውነትን ብቻ መነጋገር የሚችል ሰው የማይደርስበት ከፍታ አለ ብዬ አላስብም። ቀንተህ ከሆነ መቅናትህን ለራስህ ማመን አለብህ። ሰይጣን በቅናት አዳምን አስቶ ጥሎታል። አንተንም በሰዎች ላይ እንድትቀና አድርጎ ብዙ በደሎችን ሲያሰራህ ለራስህ መቅናትህን እንዳታውቀው አድርጎ ነው። ስለዚህ እኔ እገሌ ላይ የምቀና ከሆነ እንደምቀናበት በሚገባ ማወቅ አለብኝ። መቅናቴን ካወኩኝ፣ እንዴት ከቅናቴ እንደምወጣም መንገዱ አይጠፋኝም።
2) የምንቀናበትን ሰው ሄዶ ማድነቅና ስለእሱ መጸለይ
የምንቀናበትን ሰው ሄደን ስለምንቀናበት ነገር ማድነቅና ማወደስ አንድ ቅናታችንን የሚያስተነፍስልን ነገር ነው።... ሰይጣን ገና ስታየው በቅናትህ ምክንያት እንድትጠላውና እንድትናደድ ያሰበውን ሰው ሄደህ በንጹሕ ልብ ተንኮል ሳታስብ ስታደንቀውና ስታሞግሰው ሲያይ ግራ ይገባዋል። እርሱ በሰው ልጅ ላይ ቀንቶ ያደረገውን ስለሚያውቅ፣ አንተ ቀንተህ እንዲህ ፍቅር ስታሳይ ጥያቄ ይፈጠርበታል። ከማድነቅም በላይ ደግሞ እግዚአብሔር ፊት ለጸሎት በቆምክ ጊዜ ስለምትቀናበት ሰው ከፍታ ብትጸልይ እግዚአብሔር ስለፍቅርህ ብቻ ያንተን ቅናት አስወግዶ ለእርሱ የሰጠውን ጸጋ ላንተም ይሰጥሃል።
እንደ ቅናትና ምቀኝነት የእግዚአብሔርን ጸጋ የሚያሸሽ ነገር የለም። እግዚአብሔር አምላክ ለአንድ ሰው ጸጋ የሚሰጠው ከሌላው ሰው ቀምቶ አይደለም። አንተ ከፍ እንድትል ሌላ ሰው መዘፈቅ የለበትም። እግዚአብሔር አንተንም የምትቀናበትንም ሰው የማዋረድም የማክበርም ሥልጣን ያለው እርሱ ነው። አንተ ቀንተህ በማዋረድህ የሚወሰድብህ እንጂ የሚጨመርልህ አንዳች ጠብታ የለም። ቅናትና ምቀኝነት እንደ አረም ሰው ወደሚፈልግበት ቦታ እንዳይደርስ አንቅሮ የሚይዙ የሰይጣን ተክሎች ናቸው። እግዚአብሔር አምላክ ከዚህ ክፉ በሽታ ይፈውሰን፣ ይጠብቀን!!
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
ሰኔ 25/2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
.
.
👍 4❤ 2👏 1😢 1
በጣም የሚያስጨንቃችሁ፣ ዕረፍት የሚነሳችሁ፣ ሁሌ የምታለቅሱበት ችግር እና ጭንቀት ካለባችሁ ስለእርሱ እግዚአብሔርን አመስግኑ። እግዚአብሔር በደስታችን ጊዜ እንደማንፈልገው በሚገባ ያውቃል። እርሱ ትዝ የሚለን ሲከፋንና ሲቸግረን እንደሆነ በሚገባ ይረዳል። ስለዚህ ከፍቅሩ የተነሳ ጥለነው እንዳንሄድ፣ እንዳንክደው፣ እንዳንሸሸው ወደ ራሱ የሚያቀርብ ችግር ይሰጠናል።
ጌታ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 21 ላይ ከትንሣኤው በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ሊነጋጋ ሲል ለሐዋርያቱ ተገልጦላቸው ነበር። ቅዱስ ጴጥሮስን ሶስት ጊዜ ትወደኛለህን ብሎ ከመጠየቁ በፊት ሌሊቱን ሙሉ ዓሣ ሲያጠምዱ አድረው አንዲት አሣ እንኳን ያልያዙትን ደቀ መዛሙርት "ልጆቼ ሆይ አንዳች የሚበላ አላችሁን?" ብሎ ጠየቃቸው። ምንም ዓሣ እንዳልያዙ እያወቀ ለምን ጠየቃቸው ቢሉ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ሲል ይመልሳል...
"የልጆቹ ሥጋዊ ፍላጎት እንደሚያሳስበውና የርኅራሄ አባት እንደመሆኑ የሐዋርያትን ሥጋዊም መንፈሳዊም ፍላጎታቸውን አሟልቶላቸዋል። ከሞት የተነሳው ክርስቶስ አሁንም በእያንዳንዱ ክርስቲያን ቤት ማለፉን ይቀጥላል፤ በተለይ የተቸገሩትንና የሚረዳቸው ያጡትን ቀርቦ 'ልጆቼ ሆይ አንዳች የሚበላ አላችሁን' ብሎ ይጠይቃቸዋል። ምንም የሚበላ እንደሌላቸው ቢያውቅም በእምነት የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እርሱ እንዲጸልዩ ያነሳሳቸዋል። እርሱም በፍቅሩ ምንጮች ምግባቸውን ሰጥቶ ያጠግባቸዋል። የልባቸውን ዓይን ከፍቶ እርሱን እንዲያዩትና ረቂቅ አሠራሩን እንዲያውቁ ያደርጋቸዋል።"
ወደ እርሱ መጸለይን፣ በእርሱ መመካትን ሊያስተምራቸው ለሐዋርያቱ ጉድለታቸውን፣ ችግራቸውን አስታወሳቸው።
እውነት እንነጋገርና፣ ጸሎታችን ሁሉ ከመ ቅጽበት ቢመለስልንና የጠየቅነው ሁሉ ቢደረግልን ማን ወደ እግዚአብሔር ደጅ ቀንና ሌሊት ይመላለሳል? ማንስ እርሱን በማገልገል ይጸና ይሆን? ስንቶች ችግራቸው እንዲፈታላቸው ወደ እግዚአብሔር ቤት መጥተው አገልጋይ ሆነው ቀሩ?.... ስንቶች ጭንቀታቸው እንዲቀልላቸው ወደ እግዚአብሔር ቀርበው የቅድስና ሕይወትን ያዙ??
ከእግዚአብሔር ጋር ያጣበቀችን የአንዲት ጸሎት አለመመለስ የሆነች ስንቶቻችን ነን? እግዚአብሔር ከእርሱ የምንርቅበትን መንገድ በችግሮች ያጥርብናል። ታዲያ ለዚህም ልናመሰግነው አይገባምን?
እርሱን ደጅ የምንጠናበትን ችግርን፣ ጭንቀትን፣ ፈተናን ያላሳጣን እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
.
.
ዲያቆን ዮሐንስ ደረጀ
ሰኔ 18,2016 ዓ.ም
አዲስ አበባ
👇👇👇👇👇👇
👉 @gitsawe👈
👉 @gitsawe👈
👉 @gitsawe👈
👉 @gitsawe👈
👆👆👆👆👆👆
❤ 8🙏 6👍 2
Repost from ያሬዳውያን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ሥርዓተ ማኅሌት ዘሰኔ ሚካኤል
🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸🌸
ሥርዓተ ነግሥ:-
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሥላሴ፦
ሰላም ለጒርኤክሙ ስቴ አንብአ ሰብእ ዘኀሠሠ: ብኡላነ ሞገስ ሥላሴ ኢታንድዩኒ ሞገሰ: እመትትኃየዩኒሰ ኢትኅድጉኒ ጽኑሰ: ሚካኤልኑ ለአውጽኦ ስጋየ ጌሠ: ወእመ አኮ ገብርኤል ወሀበኒ ነፍሰ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ኢይጽሕቅ ዘይመክሮ ወኢየኀሥሥ ዘይመክሮ: አልቦቱ ጥንት ወኢተፍጻሜት: ኢየኀልቅ መንግሥቱ ወአልቦ ዘይክል መዊዓ ኀይሉ: ወአልቦ ኁልቊ ለሠራዊተ መላእክት እለ ይትለአክዎ: አንተ ውእቱ አቡሃ ለጥበብ: ገባሬ ኲሉ ፍጥረት ወገባሪሃ ለሕግ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ነግሥ
ሰላም ለልሳንከ መዝሙረ ቅዳሴ ዘነበልባል: ወለድምፀ ቃልከ ሐዋዝ ቀርነ መንግሥቱ ለቃል: ሞገሰ ክብሩ ሚካኤል ለተላፊኖስ ባዕል: አልቦ ዘይትማሰለከ በልማደ ምሕረት ወሳሕል: እንበለ ባህቲታ እኅትከ ማርያም ድንግል።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
አመ ይነፍህ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ: ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ፀሃፈ: ሶበ እጼውእ ስመከ ከሢትየ አፈ: ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል በከመ ታለምድ ዘልፈ: ለረዲኦትየ ነዓ ሠፊሐከ ክንፈ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ዓቢተነ በመድኃኒትከ: ጸግወነ ንጸውዕ ስመከ: ኖላዊነ ኄር ትጉሕ ዘኢትነውም ሰላመከ ሀበነ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
ሀበነ ሰላመከ ንጸውዕ ስመከ/፪/
ዘኢትነውም ትጉሕ "ኖላዊነ ኄር"/፪//፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለልሳንከ በነቢበ ጽርፈት ዘኢተኃበለ: በእንተ ስጋሁ ለሙሴ አመ ምስለ ሰይጣን ተበኃለ: ሚካኤል ክብርከ እምክብረ መላእክት ተልዕለ: ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ: በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዓኒ ቃለ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
ቀዊምየ ቅድመ ስዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ/፪/
"በብሂለ ኦሆ"/፪/ ፍጡነ አስምአኒ ቃለ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
አመ ይነፍሕ ሚካኤል ቀርነ በደብረ መቅደስየ: አሜሃ ይትነሥኡ ሙታን: ይትፌሥሁ መላእክት በዕርገቱ: በፍሥሃ ወበሰላም አዕኮትዎ ለንጉሠ ስብሐት።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ዕብል ለአስናኒከ ዘመንፈስ: ዘኢይረክቦን ጥረስ: ሚካኤል ረዳኢ ለእለ ውስተ ባሕር ወየብስ: እስመ ረሰይከ ካህነ ምሥዋኡ ክርስቶስ: መፍትው ሊተ ትተንብል ቀሲስ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ ምስሌሁ: ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ: ዮም ሰማያዊ በምድር አስተርአየ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
ባሕራንኒ ይቤ ዘነገደ ባሕረ/፪/
ርኢክዎ ለሚካኤል ወስዕንኩ ጠይቆቶ ስዕንኩ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሚካኤል
ሰላም ለእስትንፋስከ ቁሱላነ ነፍስ ለአጥዕዮ: ዘይነፍሕ ፄና አንህዮ: ሚካኤል ነዓ ኲናተከ በተረስዮ: ለገቢር ከመ ቀዳሚ ለአርዌ አመፃ ደርብዮ: እስመ ኢኃደገ እንከ ዘትካት እከዮ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ወከሢቶ ረከበ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ: ወእከስተ ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን: ወእፈውስ ሎሙ ለቁሱላነ ልብ: ወእሰምዮ ለባሕራን ኅሩየ: ዝኬ ዘተነግረ በመዋዕለ ትካት: ለ፳ኤል ኅብስተ መና ዘአውረደ በገዳም: ወርእየቱ ከመ ተቅጻ ወከመ አያያተ መዓር ጥዑም ፈድፋደ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
"ወከሢቶ ረከበ"/፪/ ኀበ ይብል እዜንዎሙ ለነዳያን ፈነወኒ/፪/
ወእስብክ ሎሙ ግዕዛነ ለጼውዋን ወእስምዮ ለባሕራን ኅሩየ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሚካኤል፦
ሰላም ለአጻብኢከ መጽሐፈ እለ ለክዑ: ዕጒለ አባግዕ እምኖሎት በጊዜ ተመልዑ: ሚካኤል አንተ ለንጉሠ ነገሥት ካህነ ምሥዋኡ: አሣዕነ መድኃኒት ለእገርየ አጻብኢከ ይቅጽዑ: ከመ በፍናውየ የኀዝ ለሰላም ቅብዑ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
ቅዱሳት አጻብኢከ ለጽሒፈ መጽሐፍ እለ ተቀንያ: ወብጹዓት አዕይንቲከ ምስጢረ መለኮት ዘርእያ: ሚካኤል መልአክ ወሐዋርያ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
ምስጢረ መለኮት ዘርእያ አዕይንቲከ/፪/
ሚካኤል መልአክ መልአክ ወሐዋርያ ሚካኤል መልአክ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
መልክዐ ሚካኤል፦
አምኃ ሰላም አቅረብኩ ለመልክዕከ ኲሉ: ለለአሐዱ አሐዱ ዘበበክፍሉ: ሚካኤል ክቡር ለልዑል መልአከ ኃይሉ: ተወኪፈከ አምኃየ እምኑኃ ሰማያት ዘላዕሉ: ዕሴተ ጸሎትየ ፈኑ ወአስብየ ድሉ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ዚቅ
መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል: ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ: አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ ዓቢይ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
መልአከ ሰላምነ/፬/
ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል በእንቲአነ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
አንገርጋሪ
አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ: ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ: ፀሐይ ጸልመ ወወርኅ ደመ ኮነ: ወሪዶ እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ።
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
አመላለስ
ወሪዶ እመስቀሉ/፪/
እመስቀሉ አብርሃ ለኲሉ/፬/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
ወረብ
አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእነ/፪/
ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ/፪/
@EOTCmahlet
@EOTCmahlet
እስመ ለዓለም፦
ይቤሎሙ ኢየሱስ ለአርዳኢሁ: አዓርግ ሰማየ አቡየ ወአቡክሙ: ኀበ አምላኪየ ወአምላክክሙ: ዘንተ ይቤሎሙ ዓርገ ውስተ ሰማያት: ካዕበ ይመጽእ በዘዚአሁ ስብሐት: ሠርጎሙ ለሐዋርያት ብርሃኖሙ ለእለ ውስተ ጽልመት: መድኃኔ ነገሥት ክብሮሙ ለመላእክት ኖላዊሆሙ።
ዓዲ እስመ ለዓለም-
እምድኅረ ተንሥአ እሙታን ዓርገ ውስተ ሰማያት በስብሐት አምላከ ምሕረት: ወተቀብልዎ አዕላፋ አዕላፋት: ወሚካኤል ሊቀ መላእክት በንፍሐተ ቀርን እምኀበ እግዚአብሔር: ስብኩ ትንሣኤ ውስተ ኲሉ ምድር።
🇪🇹👇👇👇👇👇🇪🇹
👉@EOTCmahlet👈
👉@EOTCmahlet👈
👉@EOTCmahlet👈
🇪🇹👆👆👆👆👆👆🇪🇹
👍 11🙏 2❤ 1
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
ብዙዎች በሰርጋቸው ቀን "የአገራችን ባሕል ነው" የዘፈን ድግስን ያዘጋጃሉ። ወይም ደግሞ "ቤተሰብ እሺ አይልም" በማለት እንደሚቸገሩ ይናገራሉ። ነገር ግን ይህን የቅዱስ ዮሀንስ አፈወርቅ ቃል ማስታወስ ይገባል
"ጋብቻ ዝሙትን የምናጠፋበት መድኃኒት ነው። ስለዚህ በዲያብሎስ ስራ (በዘፈን) ጋብቻን አናቃልል። ከዚህ ይልቅ አሁን የሚያገቡ ሰዎች በቃና ዘገሊላ እንደ ኾነው ያድርጉ። በመካከላቸው ጌታችን ክርስቶስ እንዲኖር ያድርጉ። "እንዴት ይህን ማድረግ ይችላሉ? ብሎ የሚጠይቅ ሰው ሊኖር ይችላል። ካህናትን በመጥራት! 'እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል' ይላልና (ማቴ 10:40)። ስለዚህ ዲያብሎስን አርቁት። የሴሰኝነት ዘፈኖችን፣ የርኵሰት ዜማዎችን፣ ሥርዓት የለሽ ጭፈራዎችን፣ የሚያሳፍሩ ቃሎችን፣ ዲያብሎሳዊ ትርኢቶችን፣ ሁከቶችን፣ቅጥ ያጡ ሳቆችን፣ ሌሎች እነዚህን የመሰሉ አግባብ ያይደሉ ነገሮችንም አስወግዱ። በእነዚህ ፈንታም የጌታችን ክርስቶስ ቅዱሳን አገልጋዮችን ጥሩ ፣ በእነርሱም በእውነት ያለ ሐሰት ከእናቱና ከወንድሞቹ ጋር በሰርጋችሁ ላይ ይገኛል። " በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነው" ብሏልና (ማቴ 12:50)።
አንዳንድ ሰዎች እንደዚህ ያሉ ተግሣጻትን ስለምናገርና የጥንት ባሕሎችን ስለማስቀር አሰልቺና አስቸጋሪ እንደ ኾንኩ አድርገው እንደሚያስቡ ዐውቃለው። ነገር ግን እነርሱ ስለ ተቃወሙኝ በፍጹም አልጨነቅም። እኔ የምፈልገው በእናንተ ዘንድ ተቀባይነትን ማግኝት ሳይኾን የእናንተን ጥቅም ነውና። ከዚህ ጥበብ ጥቅምን እንድታገኙ እንጂ እንድታመሰግኑኝ አልፈልግምና። ስለዚህ "ይህ ባሕል ነው" ብሎ አንድ ሰውስ እንኳ አይንገረኝ። ኀጢአት በድፍረት የሚፈፀምበት እስከ ኾነ ድረስ ባሕሉን እርሱት። ክፉ ሣራ የሚሰራባቸው እስከ ኾኑ ድረስ ባህሎቹ የቱንም ያህል ጥንታውያን ቢሆኑ ከእናንተ አስወግዷቸው። ክፉ ስራ የማይሰራባቸው ከኾኑ ግን ያልተለመዱ እንኳን ቢሆኑ ተቀበሏቸው።
❤ 27👍 2🙏 1
Boshqa reja tanlang
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.