uz
Feedback
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"

ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"

Kanalga Telegram’da o‘tish

ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" analitikasi

ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" (@wahidcom) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 61 851 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 822-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 515-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 61 851 obunachiga ega bo‘ldi.

11 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 1 276 ga, so‘nggi 24 soatda esa 53 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 19.95% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.74% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 12 339 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 6 026 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ...

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 12 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

61 851
Obunachilar
+5324 soatlar
+3047 kunlar
+1 27630 kunlar
Postlar arxiv
“ደጃል” دَّجَّال የሚለው ቃል “ደጀለ” دَجَلَ ማለትም “አጭበረበረ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “አጭበርባሪ” ወይም “ሐሳዌ” ማለት ነው፥ ቀደምት ሠለፎች ይህንን አሰር ለእኛ አስተላልፈውልናል። "አሰር" أَثَر የሚለው ቃል "አሰረ" أَثَرَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ትውፊት" "ቅብብሎሽ" "ቅሪት" ማለት ነው፥ "ሠለፍ" سَلَف የሚለው ቃል "ሠለፈ" سَلَفَ ማለትም "ቀደመ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ቀደምት" ማለት ነው፦ 9፥100 ከስደተኞቹ እና ከረዳቶቹም ሲኾኑ "የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች" እነዚያም በበጎ ሥራ የተከተሏቸው አሏህ ከእነርሱ ወዷል እነርሱም ወደዋል፡፡ በሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘለዓለም ነዋሪዎች ሲኾኑ ለእነርሱ አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል ነው፡፡ وَالسَّابِقُونَ الْأَوَّلُونَ مِنَ الْمُهَاجِرِينَ وَالْأَنصَارِ وَالَّذِينَ اتَّبَعُوهُم بِإِحْسَانٍ رَّضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ وَأَعَدَّ لَهُمْ جَنَّاتٍ تَجْرِي تَحْتَهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ "የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! እነዚህም "ሰሓቢይ" صَحَابِيّ ሲባሉ የነቢያችን”ﷺ” ውድ “ባልደረባ”companion” ናቸው፥ "የተከተሏቸው" የተባሉት ሁለተኛው ትውልድ "ታቢዒይ" تَابِعِيّ እና ሦስተኛው ትውልድ "ታቢዑ አት-ታቢዒን" تَابِع التَابِعِين ናቸው። እነዚህ ሦስት ትውልድ ሠለፍዩን ናቸው፦ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 83, ሐዲስ 72 ዒምራን ኢብኑ ሑሰይን እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ከእናንተ ምርጡ የእኔ ትውልድ ነው፥ ቀጥሎ ያሉት እነርሱን የሚከተሉት ነው፥ ለጥቆ ያሉት የሚከተሉትን የሚከተሉ ናቸው”*። قَالَ سَمِعْتُ عِمْرَانَ بْنَ حُصَيْنٍ، يُحَدِّثُ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ خَيْرُكُمْ قَرْنِي، ثُمَّ الَّذِينَ يَلُونَهُمْ، ثُمَّ الَّذِينَ يَلُونَهُم ዐሊሞች ከተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሐዲስ እና ከሠለፎችን አሰር በደሊል ሲያንቆራጥጡት ረሻድ ኸሊፋህ፦ "የሙሐመድ"ﷺ" ሐዲስ ሆነ የሠለፎችን አሰር የሚባለውን ነገር አልቀበልም፥ ቁርኣን በቁርኣን ብቻ ይፈሠራል" ብሎ አረፈው። የእርሱ ፈለግ የሚከተሉ ዛሬ ላይ በመላው ዓለም ሲኖሩ አሥራ አራት ትውልድ በቅብብሎሽ የመጣውን የቁርኣን አረዳድ ሙሉ ለሙሉ አይቀበሉም። ቁርኣኒይ የሚባሉት ሙናፊቁን "ቁርኣን በቁርኣን እንጂ አይብራራም፥ ቁርኣንን የሚያብራራ መጽሐፍ ሆነ ሰው የለም" ብለው የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ንግግር ሆነ የሠለፎችን አረዳድ አይቀበሉም፥ የሚያጅበው ግን እራሳቸው በራሳቸው መንገድ ቁርኣን ፈሣሪዎች እና የተፍሢር መጽሐፍ ማዘጋጀታቸው ነው። ይህ አባባላቸው የሰፈር ጉልቤዎች ትዝ አሉኝ፥ የሰፈር ጉልቤዎች "እቃውን ማንም ማውረድ አይችልም" ይለሉና እራሳቸው በወሰኑት ሒሣብ ያወርዳሉ። በተመሳሳይ ቁርኣኒይ የሚባሉት ሙፍሠዲን "ቁርኣን የተብራራ ነው፥ ማንም ማብራራት አይገባውም" ይሉክና እራሳቸው አብራሪ ሆነው ታገኛቸዋለህ። ቁርኣኒያዎች አቋማቸው "ተውራት ለሙሣ አልተወረደም፥ ለማን እንደወረደ ቁርኣን አይገልጽም። እስራኤል ያዕቆብ አይደለም፥ ያዕቆብ ማን እንደሆነ ቁርኣን አይገልጽም" ይላሉ፥ ከዚያ የሐዲስ እና የሠለፎችን ተፍሢር ስታስቀምጥ አይቀበሉም። እነዚህ ሰዎች በመላው ዓለም ላይ ኢኽቲላጥን አስፋፊዎች ናቸው፥ "ኢኽቲላጥ" اِخْتِلَاط ማለት "መደባለቅ" ማለት ሲሆን ወንድ እና ሴትን በትምህርት፣ በጉባኤ፣ በአምልኮ ቦታ ደባልቀው የሚያስተምሩ እና ትውልድን የሚያበላሹ ናችው። ይህ ፈሣድ አገራችን ላይ እንደ ሰደድ እሳት በድብቅ እየተስፋፋ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ግን ጭንብሉን ገልጦ በግልጽ በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን እየተስፋፋ ይገኛል፥ ይህንን ጉዳይ ስናስጠነቅቅ ትውልዱን በፈሣድ እንዳይበከል እና የእሳት እራት እንዳይሆን እንጂ የሰዎችን ግላዊ ስብዕና ለመንካት በፍጹም እና በጭራሽ አይደለም። አውቀው ይሁን ሳያውቁ የቁርኣንያን እሳቤ የሚያራምዱትን አምላካችን አሏህ ሂዳያውን ይወፍቃቸው! እኛንም ከቁርኣኒያህ ፈሣድ እና ኒፋቅ ይጠብቀን! አሚን። ✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም

ቁርኣኒያህ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፥ ነገር ግን የአሏህ መልእክተኛ እና "የነቢያት መደምደሚያ" ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ "ቁርኣኒያህ" قُرْآنِيَّة ማለት "ቁርኣን ብቻ" የሚል እና የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሐዲስ ሆነ የሠለፎችን አሰር የማይቀበል እሳቤ ሲሆን ይህንን እሳቤ የሚያራምዱ ሰዎች "ቁርኣኒይ" قُرْآنِيّ ይባላሉ፥ ቁርኣኒያን የጀመረው እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ከ 1933 ድኅረ ልደት እስከ 1990 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ግብፃዊ እና አሜሪካዊ ረሻድ ኸሊፋህ ነው። ረሻድ ኸሊፋህ፦ "እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ" ብሎ ሲያውጅ በወቅቱ የነበሩት ዐሊሞችን የአሏህን ንግግር ጠቀሱበት፦ 33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፥ ነገር ግን የአሏህ መልእክተኛ እና "የነቢያት መደምደሚያ" ነው። አሏህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا እርሱም፦ "የነቢያት መደምደሚያ" እንጂ "የመልእክተኞች መደምደሚያ" አይልም" በማለት እርሱ ነቢይ እንዳልሆነ እና መልእክተኛ እንደሆነ ተናገረ፥ ዐሊሞችንም፦ "መልእክተኛ እራሱ ነቢይ ሳይሆን መልእክተኛ መሆን አይችልም" ሲሉት "መስፈርቱን አልቀበልም" አለ። ይህንን የተረዱት ዐሊሞችን የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሐዲስ ጠቀሱለት፦ ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 2272 አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”በእርግጥም መልእክተኛነት እና ነቢይነት ተዘግቷል። ከእኔ በኃላ መልእክተኛም ነቢይም የለም"። حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ” إِنَّ الرِّسَالَةَ وَالنُّبُوَّةَ قَدِ انْقَطَعَتْ فَلاَ رَسُولَ بَعْدِي وَلاَ نَبِيَّ ነቢያችን"ﷺ" በሡናህ መልእክተኛ እና ነቢይ እንደማይመጣ እንቅጩን ፍርጥ አርገው እንዲህ ነግረውናል፥ ነገር ግን የመጨረሻይቱ ሰዓት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 108 አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “የመጨረሻይቱ ሰዓት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ”። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لاَ تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يُبْعَثَ دَجَّالُونَ كَذَّابُونَ قَرِيبٌ مِنْ ثَلاَثِينَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ رَسُولُ اللَّهِ

ካቶሊክ፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ፣ የጽብሓውያን ኦርቶዶክስ እና ጥቂት የፕሮቴስታንት ጎጥ እና አንጃ ይህንን ጥቅስ ተንተርሰው "ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛ አለን" ቢሉም ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን "ታቦት ነው" አይሉም፥ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ውጪ ያሉት ባለ ጠረጴዛ አብያተ ክርስቲያናት ባለ ሳጥኑ ታቦት "በአዲስ ኪዳን ቀርቷል" የሚል አቋም አላቸው። ከዚያ ይልቅ ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን "መሠዊያ" ይሉታል፦ ዕብራውያን 13፥10 መሠዊያ አለን፥ ከእርሱም ሊበሉ ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ መብት የላቸውም። እዚህ አንቀጽ ላይ "መሠዊያ" እያለ ያለው ሙሴ እያየ ሢሠራ የነበረው ሰማያዊ መሠዊያ ነው፥ በሰማይ ካለው መሠዊያ ከሱራፌልም አንዱ በእጁ በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ፦ ኢሳይያስ 6፥6 ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እኔ መጣ፥ በእጁም ከመሠዊያው በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ። "ፍሙ" "ጉጠቱ" "መሠዊያው" ቁሳዊ እንዳልሆነ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ሰማይ ላይ መሠዊያ እንዳለ ብዙ ጥቅስ አለ፦ ራእይ 9፥13 ራእይ 6፥9 ራእይ 14፥18 ተመልከት! ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ የብሉይ ኪዳን ሌዋውያን ከሰማያዊ መሠዊያ ሊበሉ መብት የላቸውም፦ ራእይ 19፥9 ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው። ራእይ 3፥20 ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል። "መሠዊያ" መሥዋዕት ማቅረቢያ ከሆነ የምስጋና መሥዋዕት በክርስቶስ ለእግዚአብሔር አብ እንደሚቀርብ የሚናገረው ጥቅስ ተንተርሰው "መሠዊያ" እራሱ ክርስቶስ ነው" የሚሉ እንደ "Clarke's Commentary" ያሉ አብራሪዎች አሉ፦ ቆላስይስ 3፥17 እግዚአብሔር አብን በእርሱ(በክርስቶስ) እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት። ዕብራውያን 13፥15 እንግዲህ ዘወትር ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት፥ ማለት ለስሙ የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ፥ በእርሱ(በክርስቶስ) እናቅርብለት። "ከእርሱም ሊበሉ" ሲል "ከክርስቶስም ሊበሉ" ማለት ነውና ከእርሱ እራት ሊበሉ ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ የብሉይ ኪዳን ሌዋውያን መብት የላቸውም በሚል ይረዱታል። ሆነም ቀረ ሰርግ፣ እራት፣ ምግብ፣ መሠዊያ ፍካሬአዊ እንጂ እማሬአዊ ትርጉም ከሌለው "መሠዊያ አለን" ያለውም ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን በጭራሽ አይደለም፥ "መሠዊያ አለን" ያለውም "ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን ነው" ቢባል እንኳን "መሠዊያው ታቦት ነው" የሚል አሳብ በአዲስ ኪዳን ላይ አናገኝም። ዋና መነሻችን "አክሱም ውስጥ የብሉይ ኪዳን ታቦት የለም" "በአዲስ ኪዳንም ታቦት የሰው አካል እንጂ ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛ ወይም መሠዊያ ታቦት ነው" የሚል የለም" የሚል ነው። ሕዝቡን አትዋሹት! አታጭበርብሩት! ሰው የማያነብ ይመስላችኃል? ቅጥፈታችሁ ሰው እያወቀ ሲመጣ ጥሏችሁ ወደ ዲኑል ኢሥላም ይመጣል። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም

የአዲስ ኪዳን ታቦት ክፍል ሁለት በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 5፥115 አሏህ፡- «እኔ ማዕድዋን በእናንተ ላይ አውራጅዋ ነኝ፡፡ በኋላም ከእናንተ የሚክድ ሰው እኔ ከዓለማት አንድንም የማልቀጣውን ቅጣት እቀጣዋለሁ» አለ፡፡ قَالَ اللَّهُ إِنِّي مُنَزِّلُهَا عَلَيْكُمْ ۖ فَمَن يَكْفُرْ بَعْدُ مِنكُمْ فَإِنِّي أُعَذِّبُهُ عَذَابًا لَّا أُعَذِّبُهُ أَحَدًا مِّنَ الْعَالَمِينَ "ማኢዳህ" مَائِدَة ማለት "ማዕድ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ወደ አሏህ «ጌታችን አሏህ ሆይ! ለእኛ ለመጀመሪያዎቻችንና ለመጨረሻዎቻችን በዓል የምትኾንን ከአንተም ተአምር የኾነችን ማዕድ ከሰማይ በእኛ ላይ አውርድ፡፡ ስጠንም፡፡ አንተ ከሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነህና» አለ፦ 5፥114 የመርየም ልጅ ዒሣ አለ፡- «ጌታችን አሏህ ሆይ! ለእኛ ለመጀመሪያዎቻችንና ለመጨረሻዎቻችን በዓል የምትኾንን ከአንተም ተአምር የኾነችን ማዕድ ከሰማይ በእኛ ላይ አውርድ፡፡ ስጠንም፡፡ አንተ ከሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነህና» አለ። قَالَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ اللَّهُمَّ رَبَّنَا أَنزِلْ عَلَيْنَا مَائِدَةً مِّنَ السَّمَاءِ تَكُونُ لَنَا عِيدًا لِّأَوَّلِنَا وَآخِرِنَا وَآيَةً مِّنكَ ۖ وَارْزُقْنَا وَأَنتَ خَيْرُ الرَّازِقِينَ "ዒድ" عِيد ማለት "በዓል" ማለት ሲሆን ይህም በዓል ፋሲካ ነው፥ በዚህ በዓል ከሰማይ የወረደው ማዕድ ኢየሱስ ሳይሆን በተአምር ከሰማይ የመጣ ማዕድ ነው፦ 5፥115 አሏህ፡- «እኔ ማዕድዋን በእናንተ ላይ አውራጅዋ ነኝ፡፡ በኋላም ከእናንተ የሚክድ ሰው እኔ ከዓለማት አንድንም የማልቀጣውን ቅጣት እቀጣዋለሁ» አለ፡፡ قَالَ اللَّهُ إِنِّي مُنَزِّلُهَا عَلَيْكُمْ ۖ فَمَن يَكْفُرْ بَعْدُ مِنكُمْ فَإِنِّي أُعَذِّبُهُ عَذَابًا لَّا أُعَذِّبُهُ أَحَدًا مِّنَ الْعَالَمِينَ ስለዚህ ከሰማይ የወረደው ማዕድ ኢየሱስ ሳይሆን ለኢየሱስ እና ለሐዋርያት ለበዓሉ እንዲበሉት የተሰጠ ማዕድ ነው፥ ቁርኣን ባይብል ላይ የገባውን የተሳሳተ "የጌታ ማዕድ" በዚህ መልኩ አስተካክሎታል። "ፋሲካ" በሚባል "በዓል" ላይ በመሸም ጊዜ ኢየሱስ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ እንደተቀመጠ ይናገራል፦ ማቴዎስ 26፥20 በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ። Ὀψίας δὲ γενομένης ἀνέκειτο μετὰ τῶν δώδεκα μαθητῶν "ጠረጴዛ" የሚለው የግዕዙ ቃል እራሱ "ማዕድ" ወይም "ገበታ" ማለት እንጂ ባለ አራት እግር ያለው "ጻሕል(ሳሕን) ወይም "ወጭት" ማለት አይደለም፥ "ጠረጴዛ" የሚለው የግዕዙ ቃል እራሱ "ትራፔዛ" τράπεζα ከሚል ግሪክ ኮይኔ የመጣ ሲሆን "ማዕድ" ማለት ነው። ለምሳሌ፦ የሐዋርያት ሥራ 16፥34 ወደ ቤቱም አውጥቶ ማዕድ አቀረበላቸው። ἀναγαγών τε αὐτοὺς εἰς τὸν οἶκον παρέθηκεν τράπεζαν, እዚህ አንቀጽ ላይ "ማዕድ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛን" τράπεζα እንደሆነ ልብ አድርግ! "ትራፔዛን" τράπεζα የተባለው ምግቡ እንጂ ምግቡ የሚቀመጥበት ወጭት አይደለም፦ መዝሙር 77(78)፥19 አምላክን እንዲህ ብለው አሙት፦ "አምላክ በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ይችላልን? καὶ κατελάλησαν τοῦ Θεοῦ καὶ εἶπαν· μὴ δυνήσεται ὁ Θεὸς ἑτοιμάσαι τράπεζαν ἐν ἐρήμῳ; እዚህ አንቀጽ ላይ "ማዕድ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛ" τράπεζα ሲሆን በዐረቢኛ ባይብል ላይ "ማኢዳህ" مَائِدَة ነው፥ "ማዕድ" የተባለው የተሰናዳው ምግብ እንጂ ከእንጨት ወይም ከድንጋይ የተዘጋጀ ዝርግ ነገር በፍጹም አይደለም። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ይህንን ጥቅስ እንመልከት፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥20 ነገር ግን አሕዛብ የሚሠዉት ለአማልክት እንዲሆን እንጂ ለአምላክ እንዳይሠዉ እላለሁ፤ ከአማልክትም ጋር ማኅበረተኞች እንድትሆኑ አልወድም። ἀλλ’ ὅτι ἃ θύουσιν, δαιμονίοις καὶ οὐ Θεῷ θύουσιν· οὐ θέλω δὲ ὑμᾶς κοινωνοὺς τῶν δαιμονίων γίνεσθαι. "ዳይሞን" δαίμων ማለት በግሪክ ኮይኔ "አምላክ" ማለት ነው፥ የዳይሞን ብዙ ቁጥር ደግሞ "ዳይሞንዮን" δαιμονίων ሲሆን "አማልክት" ማለት ነው፦ የሐዋርያት ሥራ 17፥18 "አዲሶችን አማልክት የሚያወራ ይመስላል" Ξένων δαιμονίων δοκεῖ καταγγελεὺς εἶναι· ኢስጦኢኮች ከተባሉት ፈላስፎች "አማልክት" ለሚለው የተጠቀሙበት ቃል "ዳይሞንዮን" δαιμονίων እንደሆነ ልብ አድርግ! "አሕዛብ" የተባሉት ግሪካውያን እና ሮማውያን የሚሠዉት ለአማልክቶቻቸው ነው፥ አሕዛብ የሚያቀርቡት ምግብ "ማዕድ" ተብሎአል፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥21 የጌታን ጽዋ እና የአማልክትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፥ ከጌታ ማዕድ እና ከአማልክት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም። οὐ δύνασθε ποτήριον Κυρίου πίνειν καὶ ποτήριον δαιμονίων· οὐ δύνασθε τραπέζης Κυρίου μετέχειν καὶ τραπέζης δαιμονίων. "የጌታ ማዕድ" የተባለው በባዶ ጥቅስ "ታቦት" ካላችሁት አሕዛብ ለአማልክት የሚያቀርቡት የአማልክትን ማዕድ "ትራፔዛ" τράπεζα ተብሎአልና ለምን "ታቦት" አትሉትም? "የጌታ ማዕድ" ሆነ "የአማልክት ማዕድ" የተባሉት የሚበሉ ምግብ እንጂ የሚቀርብበት እና የሚሰናዳበት ዝርግ ሳሕን በፍጹም አይደለም። "የጌታን ጽዋ" እና "የአማልክትን ጽዋ" የሚጠጡ እንጂ የሚጠጣበት ዕቃ እንዳልሆነ ሁሉ "የጌታ ማዕድ" ሆነ "የአማልክት ማዕድ" የሚካፈሉት ምግብ እንጂ ጣውላ ሳሕን አይደለም። የጥቅሱ ዐውድ "ማዕድ" የሚለው "ጣውላ ነው" ብልን እንኳን ጣውላውን "ታቦት ነው" የሚል ንግግር ዐውዱ ላይ የት አለ? "የጌታን ታቦት" እና "የአማልክትን ታቦት" ወደሚል ውስብስ እረመጥ ውስጥ ያስገባችኃል።

የአዲስ ኪዳን ታቦት ክፍል አንድ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 58፥22 እነዚያ በልቦቻቸው ውስጥ እምነትን ጽፏል፡፡ أُولَـٰئِكَ كَتَبَ فِي قُلُوبِهِمُ الْإِيمَانَ ሙሴ ድንኳኒቱን እና በውስጧ ያሉት ሥርዓት ሊሠራ ሳለ እንደ ተረዳ ለሰማያዊ ነገር ምሳሌ እና ጥላ የሚሆነውን ነው፥ ፈጣሪ በተራራው "እንደ ተገለጠልህ ምሳሌ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ተጠንቀቅ" ብሎት ነበርና፦ ዘጸአት 25፥40 በተራራ ላይ እንዳሳየሁህ ምሳሌ እንድትሠራ ተጠንቀቅ። ዕብራውያን 8፥5 እነርሱም ሙሴ ድንኳኒቱን ሊሠራ ሳለ እንደ ተረዳ ለሰማያዊ ነገር ምሳሌ እና ጥላ የሚሆነውን ያገለግላሉ። በተራራው "እንደ ተገለጠልህ ምሳሌ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ተጠንቀቅ" ብሎት ነበርና። የዚህ ዓለም ድንኳኑ ለሰማያዊው ድንኳን "ጥላ"Typology" ነው፥ ሙሴ ሢሠራው የነበረው ድንኳን በሰማይ ላይ ያለውን ድንኳን እያየ ነበር፦ የሐዋርያት ሥራ 7፥44 "እንዳየው" ምስል አድርጎ ይሠራት ዘንድ ሙሴን ተናግሮ እንዳዘዘው፥ የምስክር ድንኳን ከአባቶቻችን ዘንድ በምድረ በዳ ነበረች። እስራኤላውያን ከግብጽ ሲወጡ አምላክ የብሉይ ቃል ኪዳን እንደገባ ሁሉ አዲስ ቃል ኪዳን ከእስራኤል ቤት እና ከይሁዳ ቤት ጋር እንደሚገባ ተናግሮ ነበር፦ ኤርምያስ 31፥31 "እነሆ ከእስራኤል ቤት እና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል" ይላል ያህዌህ። ዕብራውያን 8፥8 "እነሆ ከእስራኤል ቤት እና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ኪዳን የምገባበት ወራት ይመጣል" ይላል ጌታ። አምላክ በብሉይ ቃል ኪዳን እስራኤላውያን ከግብጽ ሲወጡ በድንጋይ ጽላት ላይ ሕጉን እንደ ጻፈ ከእስራኤል ቤት እና ከይሁዳ ቤት ጋር አዲስ ቃል ኪዳን ሕጉን በልብ ጽላት ላይ እንደሚጽፍ ይናገራል፦ ኤርምያስ 31፥33 ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ፥ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል። ዕብራውያን 8፥10 ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑልኛል። አሮጌው ኪዳን ሕጉ በድንጋይ ጽላት ላይ መጻፍ ሲሆን አዲሱ ኪዳን ሕጉ በልብ ጽላት ላይ መጻፍ ነው፥ አዲስ እና አሮጌ ልዩነቱ ይህ ነው፦ ዕብራውያን 8፥13 አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፥ አሮጌ እና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል። 2ኛ ቆሮንቶስ 3፥3 ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት ያልተጻፈ እና በእኛ የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው። የድንጋይ ጽላት ቁሳዊ ነገር ሲሆን የልብ ጽላት መንፈሳዊ ነገር ነው፥ በድንጋይ ጽላት መጻፍ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት ሲሆን የተሻረ ኪዳን ነው፦ 2ኛ ቆሮንቶስ 3፥7 ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ "ስለ ተሻረው" ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት በክብር ከሆነ። "ስለ ተሻረው" ብሎ የተሻረውን "ያ" በማለት በአመልካች ተውላጠ ስም "በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ" በማለት ይገልጸዋል፥ ያ ይሻር የነበረው በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸው በክብር ከሆነ በልብ ጽላት ላይ የተጻፈው ጸንቶ የሚኖረውማ እጅግ ይልቅ በክብር ሆኖአልና፦ 2ኛ ቆሮንቶስ 3፥11 ያ ይሻር የነበረው በክብር ከሆነ ጸንቶ የሚኖረውማ እጅግ ይልቅ በክብር ሆኖአልና። ስለዚህ በአዲስ ኪዳን የድንጋይ ሆነ የጣውላ ጽላት የለም፥ ከዚያ ይልቅ የአዲስ ኪዳን ጽላት የልብ ጽላት ብቻ እና ብቻ ነው። በልብ ላይ መጻፍ ቃል በቃል አይደለም፥ አምላካችን አሏህ ኢማንን በልብ ላይ ይጽፋል፦ 58፥22 እነዚያ በልቦቻቸው ውስጥ እምነትን ጽፏል፡፡ أُولَـٰئِكَ كَتَبَ فِي قُلُوبِهِمُ الْإِيمَانَ በተመሳሳይ በልብ ጽላት ላይ ሕጉ ቢጻፍ በግንባር ቋንቋ አማራዊ ሳይሆን በውስጠ ወይራ ቋንቋ ፍካሬአዊ እንደሆነ እንረዳለን። ልብ በአካል ውስጥ የሚኖር ስለሆነ የአዲስ ኪዳን ታቦቱ የልብ ማስቀመጫ የአማኝ ሰው አካል"Body" ነው፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥16 ኢተአምሩኑ ከመ ታቦቱ ለእግዚአብሔር አንትሙ፤ ወመንፈሰ እግዚአብሔር ኅዱር ላዕሌክሙ? "ከመ ታቦቱ ለእግዚአብሔር አንትሙ" የሚለው ይሰመርበት! ትርጉም፦ "የእግዚአብሔር ታቦት እንደ ሆናችሁ" ማለት ነው፥ ዐማርኛው ላይ "ቤተ መቅደስ" ቢለውም ግዕዙ ላይ "ታቦት" ይለዋል፦ 2ኛ ቆሮንቶስ 6፥16 ወመኑ ዘይዴምር "ታቦተ እግዚአብሔር" ውስተ ቤተ ጣዖት? "ታቦት" ማለት የጽላት ማስቀመጫ ሲሆን "ቤተ መቅደስ" ነው፥ "ቤተ መቅደስ" ማለት "የመቅደስ ቤት" ማለት ነው። የተቀደሰው ልብ ቤቱ አካል ነውና "የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ" ተብሏል፦ 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19 ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን?። በአዲስ ኪዳን ላይ "ጠረጴዛ" "መሠዊያ" የሚል ቃል አለ፥ ነገር ግን አንድም ቦታ ላይ ጠረጴዛውን ሆነ መሠዊያን "ታቦት" ወይም "ጽላት" ብሎት አያውቅም። "የአዲስ ኪዳን ታቦት ጠረጴዛ ወይም መሠዊያ ነው" ብሎ ማጭበርበር ምናባዊ ሰጊዎት እንጂ ነባራዊ ፈቲዎት አይደለም፥ ብሉይ ኪዳን ላይ ያለው ታቦት ሳጥኑ መሆኑን በጥቅስ ስናንቆራጥጣቸው፣ ስናራውጣቸው እና ስናሯርጣቸው "የአዲስ ኪዳን ታቦት ወይም ጽላት ሥጋው ወደሙ የሚፈተትበት እና የሚቆረስበት "መሠዊያ" "ጠረጴዛ" ነው" ብለው ከድጥጡ ወደ ማጡ ገቡ። ይህ የማያዋጣ ሙግት ሲሆን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነው፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን በአዲሱ ኪዳን አምላክ የሰው እጅ በሠራው መቅደስ ውስጥ አይኖርም፦ የሐዋርያት ሥራ 7፥50 ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም። የሐዋርያት ሥራ 17፥24 ዓለሙን እና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይ እና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም። በእያንዳንዱ ደብር በንግሥ ቀን እያወጡ የሚያስገቡት ጣውላ ታቦት ስለመሆኑ ምንም ዓይነት የአዲስ ኪዳን ጥቅስ የለም። ሐዋርያት የሚያስገቡት እና የሚያስወጡት ታቦት እንዴት የላቸውም? "ታቦት በውስቴታ ኦሪት በውስቴታ ውቱረ ይከድንዋ በወርቅ" ወይም "ውስቴታ ታቦት በውስቴታ ኦሪት በውስቴታ ይኬልልዋ በወርቅ ይኬልልዋ" እየተባለ የንግሥ ቀን የሚከበረው "የብሉይ ኪዳን ታቦት ነው" በሚል ዕይታ ነው። "መሠዊያ" እና "ጠረጴዛ" ከታቦት እና ከጽላት እጅጉን የተለየ ነገር እንደሆነ "የብሉይ ኪዳን ታቦት" በሚል አይተን ነበር፥ አዲስ ኪዳን ላይ "መሠዊያ" "ጠረጴዛ" የሚላቸው ምን እንደሆኑ ኢንሻ አሏህ! በክፍል ሁለት እንመለከታለን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም

ትግራይ መቀመጫ ያደረገው የኦርቶዶክስ ሲኖዶስ "አክሱም ቅድስት ከተማ ናት" ካለ ቅድሚያ ጽዮን ማርያም አጠገብ የተተከለውን የወንድ ኃፍረተ ሥጋ ቅርፅ የያዘውን ሐውልት ማፍረስ ይገባቸዋል። ፈጣሪ "የ
ትግራይ መቀመጫ ያደረገው የኦርቶዶክስ ሲኖዶስ "አክሱም ቅድስት ከተማ ናት" ካለ ቅድሚያ ጽዮን ማርያም አጠገብ የተተከለውን የወንድ ኃፍረተ ሥጋ ቅርፅ የያዘውን ሐውልት ማፍረስ ይገባቸዋል። ፈጣሪ "የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ" ብሎአል፦ ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።

የብሉይ ኪዳን ታቦት ክፍል ሁለት በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 7፥145 ለእርሱም በሰሌዳዎቹ ላይ ከነገሩ ሁሉ ግሳጼን እና ለነገሩም ሁሉ ማብራራትን ጻፍንለት፡፡ وَكَتَبْنَا لَهُ فِي الْأَلْوَاحِ مِن كُلِّ شَيْءٍ مَّوْعِظَةً وَتَفْصِيلًا لِّكُلِّ شَيْءٍ በዐረቢኛ “ለውሕ” لَوْح ማለት "ሰሌዳ" ማለት ሲሆን አምላካችን አሏህ ለሙሣ ቃላትን በሰሌዳዎች ላይ ጽፎ እንደሰጠው በተከበረ ቃሉ ይናገራል፦ 7፥145 ለእርሱም በሰሌዳዎቹ ላይ ከነገሩ ሁሉ ግሳጼን እና ለነገሩም ሁሉ ማብራራትን ጻፍንለት፡፡ وَكَتَبْنَا لَهُ فِي الْأَلْوَاحِ مِن كُلِّ شَيْءٍ እዚህ አንቀጽ ላይ "አልዋሕ" أَلْوَاح ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ለውሕ” لَوْح ለሚለው የብዙ ቁጥር ሲሆን "ሰሌዳዎች" ማለት ነው። በዐረቢኛ "ታቡት" تَّابُوت ማለት "ሳጥን" ማለት ነው፦ 20፥39 ሕፃኑን በሳጥኑ ውስጥ ጣይው፡፡ أَنِ اقْذِفِيهِ فِي التَّابُوتِ እዚህ አንቀጽ ላይ "ሳጥኑ" ለሚለው የገባው ቃል "አት ታቡት" التَّابُوت ነው። የጽላት ማስቀመጫ ሳጥኑ "ታቡት" تَّابُوت ተብሎአል፦ 2፥248 ነቢያቸውም ለእነርሱ፡- «የንግሥናው ምልክት ከጌታችሁ የኾነ እርጋታ የሙሣ ቤተሰብ እና የሃሩን ቤተሰብ ከተውትም ቅርስ በውስጡ ያለበት መላእክት የሚሸከሙት ኾኖ "ሳጥኑ" ሊመጣላችሁ ነው፡፡ አማኞች ብትኾኑ በዚህ ለእናንተ እርግጠኛ ምልክት አለ» አላቸው፡፡ وَقَالَ لَهُمْ نَبِيُّهُمْ إِنَّ آيَةَ مُلْكِهِ أَن يَأْتِيَكُمُ التَّابُوتُ فِيهِ سَكِينَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَبَقِيَّةٌ مِّمَّا تَرَكَ آلُ مُوسَىٰ وَآلُ هَارُونَ تَحْمِلُهُ الْمَلَائِكَةُ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لَّكُمْ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ እዚህ አንቀጽ ላይ "ሳጥኑ" ለሚለው የገባው ቃል "አት ታቡት" التَّابُوت ሲሆን ሙፈሢሮች እንዳስቀመጡት በታቦቱ ውስጥ የሙሣ ቤተሰብ እና የሃሩን ቤተሰብ የተዉት "ቅርስ" ተብሎ የተቀመጠው ጽላት፣ የሃሩን በትር፣ መና ነው፥ ታቦቱን ከዳጎን ቤት ወደ አሚናዳብ ቤት ተሸክመው የወሰዱት መላእክት ናቸው። እንደ ኢትዮጵያ ጽብሓውያን ኦርቶዶክስ አቆጣጠር በ 1225 ድኅረ ልደት ላይ በንቡረ ዕድ ይስሐቅ የተቀነባበረ ክብረ ነገሥት የተባለው የታሪክ መጽሐፍ ይህ በሙሴ ዘመን የነበረው ታቦት በንጉሥ ሰሎሞን ዘመን አክሱም ገብቶ እንደተቀመጠ ይናገራል፥ የአገራችን ሰዎች ይህንን ትርክት ተከትለው ዛሬ ላይ "አክሱም ጽዮን ማርያም ቅጥር ግቢ ውስጥ የሙሴ ታቦት አለ" ብለው ያምናሉ። ማሩን አምርሮ ወተቱን አጥቁሮ መሞገት ከሐሰት ባለቤት የሚጠበቅ ቢሆንም ይህ ትርክት እልም ያለ ቅጥፈት መሆኑን የምትረዱት ከሰሎሞን ህልፈት 400 ዓመት በኃላ በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን ታቦቱ የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በሠራው ቤት ውስጥ ነበረ፦ 2ኛ ዜና መዋዕል 35፥3 እስራኤልንም ሁሉ ያስተምሩ ለነበሩት ለያህዌህ ለተቀደሱት ሌዋውያን እንዲህ አለ፦ "ቅዱሱን ታቦት የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በሠራው ቤት ውስጥ አኑሩት! ከዚህም በኋላ በትከሻችሁ ላይ ሸክም አይሆንባችሁም"። የብሉይ ኪዳን ታቦት አራት ሰዎች በትከሻቸው የሚሸከሙት ግዙፍ ሳጥን እንጂ ዛሬ ላይ በየአድባሩ ያሉት ጣውላዎች ንድፍ የሆኑለት በአክሱም ጽዮን የተቀመጠው ባለ ሁለት ቅጥ አይደለም፥ ይህ የሙሴ ታቦት የሚሉት ከአክሱም ማርያም ለንግሥ የማያወጡበት ምክንያት ከብሉይ ኪዳን ታቦት ጋር የማይመሳሰል ስለሆነ ነው። ቅሉ እና ጥቅሉ የቃል ኪዳኑን ታቦት የባቢሎን ንጉሥ ናቡነደፆርን እና ሰራዊቱን በ 606 ቅድመ ልደት ማርከው ወስደውታል፦ ዕዝራ ሱቱኤል 9፥22 "የቃል ኪዳናችን ታቦት" እንደ ተማረከች፥ ንዋየ ቅድሳታችን እንዳደፈ፥ ስማችን እንደ ረከሰ፥ ጌቶቻችን እንደ ተዋረዱ፥ ካህኖቻችን እንደ ተቃጠሉ፥ ሌዋውያኖቻችን እንደ ተማረኩ፥ ደናግሎቻችን እንደ ተገደሉ፥ ሚስቶቻችንን እንደ ቀሙን፥ ጻድቃኖቻችን እንደ ተጐተቱ፥ ጐልማሶቻችን እንደ ተገዙ፥ ወንዶች ልጆቻችን እንደ ተቀሙ፥ አርበኞቻችን እንደ ደከሙ አታዪምን? Second Esdras 10፥22 The ark of our covenant has been plundered, our holy things have been polluted, and the name by which we are called has been almost profaned; our children[c] have suffered abuse, our priests have been burned to death, our Levites have gone into exile, our virgins have been defiled, and our wives have been ravished; our righteous men[d] have been carried off, our little ones have been cast out, our young men have been enslaved and our strong men made powerless. "የቃል ኪዳናችን ታቦት እንደ ተማረከች"The ark of our covenant has been plundered" የሚለው ይሰመርበት! በዐማርኛው ዕዝራ ሱቱኤል እና በእንግሊዝኛው ዕዝራ ሱቱኤል የምዕራፍ ልዩነት እንዳለ ሆኖ ግዕዙ "ወተበርበረት ታቦተ ሕግነ" በማለት እንቅጩን ፍርጥ አርጎ ይናገራል፥ ይህ ዘገባ የክብረ ነገሥት ትርክት አፈር ከድሜ የሚያስገባ ነው። በባቢሎን ምርኮ ዘመን ይህ የብሉይ ኪዳን ታቦት ተማርኮ ከዚያ በኃላ ጠፋ፦ ዕዝራ ሱቱኤል 9፥23 ከዚህ ሁሉ የሚበልጥ ታቦተ ጽዮን እንደጠፋች ቀረች፥ ከእሷም ንዋየ ቅድሳቱ ተማርኮ ሄደ በጠላቶቻችን በባቢሎን እጅ ወደቅን። ይህ ዘገባ የክብረ ነገሥት ትርክት ዶግ አመድ የሚያደርግ ነው። ከባቢሎን ምርኮ በኃላ እስራኤላውያን "የያህዌህ የቃል ኪዳኑ ታቦት" ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም፣ ልብ አያደርጉትም፣ አያስቡትም፣ አይሹትም፣ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም፦ ኤርምያስ 3፥16 በዚያ ዘመን፦ "የያህዌህ የቃል ኪዳኑ ታቦት" ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም፣ ልብ አያደርጉትም፣ አያስቡትም፣ አይሹትም፣ ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም። ቃልቻ እና ጉልቻ የተቀላቀለበት ይህ የብሉይ ኪዳን ታቦት ትርክት በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ውዝግብ በማስነሳት የሚያራኩት ነው፥ ትግራይ መቀመጫ ያደረገው የኦርቶዶክስ ሲኖዶስ "አክሱም ቅድስት ከተማ ናት" ካለ ቅድሚያ ጽዮን ማርያም አጠገብ የተተከለውን የወንድ ኃፍረተ ሥጋ ቅርፅ የያዘውን ሐውልት ማፍረስ ይገባቸዋል። ፈጣሪ "የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ" ብሎአል፦ ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ። ስለ ብሉይ ኪዳን ታቦት ይህንን ካልን ዘንዳ ኢንሻ አሏህ በቀጣይ ጊዜ ስለ አዲስ ኪዳን ታቦት እንመለከታለን። አምላካችን አሏህ ከውዝግብ ይጠብቀን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም

ትክክል ያልሆነ ግን ታቦት የሚሉት በጨርቅ የሚሸፍኑት ጣውላ ይህ ነው።
ትክክል ያልሆነ ግን ታቦት የሚሉት በጨርቅ የሚሸፍኑት ጣውላ ይህ ነው።

የመጀመሪያው መጋረጃ የመገናኛውን ድንኳን ከቅድስት የሚለይ ሲሆን ሁለተኛው መጋረጃ ቅድስትን ከቅድስተ ቅዱሳን የሚለይ ነው። ስለዚህ በቫርኒሽ የተቀባውን ጣውላ "ታቦት ነው" እያላችሁ ምስኪኑን ሕዝብ አታታሉት! የመቅደስ ሁለተኛው ክፍል "ቅድስት" ሲባል በቅድስት ውስጥ መቅረዙ እና ጠረጴዛው፣ የመስዋዕቱ ኅብስት ይቀመጣሉ፦ ዕብራውያን 9፥2 በእርስዋም ቅድስት በምትባለው ውስጥ መቅረዙ እና ጠረጴዛው፣ የመስዋዕቱ ኅብስት ነበረባት። σκηνὴ γὰρ κατεσκευάσθη ἡ πρώτη, ἐν ᾗ ἥ τε λυχνία καὶ ἡ τράπεζα καὶ ἡ πρόθεσις τῶν ἄρτων, ἥτις λέγεται Ἅγια· "ጠረጴዛ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛ" τράπεζα ሲሆን "ገበታ"Table" ማለት ነው፥ ብሉይ ኪዳን ላይ "ጠረጴዛ" የተባለው ከታቦት እና ጽላት የተለየ ነገር ነው፦ ዘኍልቍ 3፥31 ታቦቱን፣ ገበታውን፣ መቅረዙን፣ መሠዊያዎቹን፣ የሚያገለግሉበትን የመቅደሱን ዕቃ፣ መጋረጃውንም፣ ማገልገያውንም ሁሉ ይጠብቃሉ። ማሶሬት፦ ומשמרתם הארן והשלחן והמנרה והמזבחת וכלי הקדש אשר ישרתו בהם והמסך וכל עבדתו ሰፕቱአጀንት፦ καὶ ἡ φυλακὴ αὐτῶν, ἡ κιβωτὸς καὶ ἡ τράπεζα καὶ ἡ λυχνία καὶ τὰ θυσιαστήρια καὶ τὰ σκεύη τοῦ ἁγίου, ὅσα λειτουργοῦσιν ἐν αὐτοῖς καὶ τὸ κατακάλυμμα καὶ πάντα τὰ ἔργα αὐτῶν." "ገበታ" ለሚለው የገባው ቃል "ሹልሀን" שֻׁלְחָן ሲሆን "ታቦት" ከተባለው ነገር "ቨ" וְ ማለትም "እና" በሚል መስተጻምር ተለያይተዋል፥ በግሪክ ሰፕቱአጀንት"LXX" ላይም ደግሞ "ገበታ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛ" τράπεζα ሲሆን "ታቦት" ከተባለው ነገር "ካይ" καὶ በሚል መስተጻምር ተለያይተዋል። እዚሁ አንቀጽ ላይ "መሠዊያ" ለሚለው የገባው ቃል በማሶሬት "ሚዝቤያህ" מִזְבֵּחַ ሲሆን በግሪክ ኮይኔ "ቱሲአስተሪኦን" θυσιαστήριον ነው፥ "መሠዊያ" ከታቦቱ እና ከጠረጴዛው ቨ" וְ እና "ካይ" καὶ በሚል መስተጻምር ተለይቷል። የመቅደስ ውጨኛው እና የመጀመሪያው ክፍል "የመገናኛው ድንኳን" ሲባል ይህ የመጀመሪያይቱ ድንኳን ናት፦ ዕብራውያን 9፥2 የመጀመሪያይቱ ድንኳን ተዘጋጅታ ነበርና። ዕብራውያን 9፥7 በሁለተኛይቱ ግን ሊቀ ካህናት ብቻውን በዓመት አንድ ጊዜ ይገባባታል፥ ዕብራውያን 13፥11 ሊቀ ካህናት ስለ ኃጢአት ወደ ቅድስት የእንስሶችን ደም ያቀርባልና። ሁለተኛይቱ ድንኳን ቅድስት ከሆነች የመጀመሪያይቱ ድንኳን የመገናኛው ድንኳን ናት፥ በመገናኛው ድንኳን አደባባይ፣ የመታጠቢያ ሰን እና የመሥዋዕት መሠዊያ አሉ። በዚህ በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ይህ የመሥዋዕት መሠዊያ የናስ መሠዊያ ሲሆን ከታቦት እና ከጠረጴዛ የተለየ ነው። ጠረጴዛ እና መሠዊያ ሁለት የተለያዩ ነገሮች ሆነው ሳለ ለምን ይሆን የአገራችን የኦርቶዶክስ መምህራን ጣውላውን "ሥጋው ወደሙ የሚፈተትበት እና የሚቆረስበት "መሠዊያ" "ጠረጴዛ" ነው" እያሉ ሕዝቡን የሚጫወቱበት እና የሚቀልዱበት? ደም የሚሉትስ ወይኑ የሚቆረስ ነገር ሳይሆን የሚፈስ ነገር ሆነ ሳለ "ደሙ ሚፈተትነት" ማለታቸውችየጤና ነውን? ኢንሻ አሏህ ክፍል ሁለት ይቀጥላል... ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም

የብሉይ ኪዳን ታቦት ክፍል አንድ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 2፥248 የንግሥናው ምልክት ከጌታችሁ የኾነ እርጋታ የሙሣ ቤተሰብ እና የሃሩን ቤተሰብ ከተውትም ቅርስ በውስጡ ያለበት መላእክት የሚሸከሙት ኾኖ “ሳጥኑ” ሊመጣላችሁ ነው፡፡ إِنَّ آيَةَ مُلْكِهِ أَن يَأْتِيَكُمُ التَّابُوتُ فِيهِ سَكِينَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَبَقِيَّةٌ مِّمَّا تَرَكَ آلُ مُوسَىٰ وَآلُ هَارُونَ تَحْمِلُهُ الْمَلَائِكَةُ ጭሮ አዳሪ ከመሆን ይልቅ ጸብ አጫሪ መሆንን ምርጫቸው ያረጉ ደሴታውያን "ጸብ በደላላ ካልሆነልን" ብለው ለገላይ በማያመች "ያዙኝ ልቀቁኝ ደግፉኝ ጣሉኝ" በማለት መፎለሉን፣ ማቅራራቱን፣ መሸለሉን፣ መፎከሩን ተያይዘውታል። ትግራይ መቀመጫ ያደረገው የኦርቶዶክስ ሲኖዶስ "የብሉይ ኪዳን ታቦት ጽዮን ማርያም ውስጥ ስላለ አክሱም ቅድስት ከተማ ናት" የሚል መግለጫ ሰጥቶአል፥ ይህ ትርክት የተሳሳተ ትርክት ነው። ምሁራን "ውኃን ከጥሩ ነገርን ከሥሩ" እንደሚሉ ስለ ብሉይ ኪዳን ታቦት ከሥር መሠረቱ ኢንሻላህ እንመልከት! በግዕዝ "ብሉይ" ማለት "ጥንት" "ፊተኛ" "አሮጌ" ማለት ሲሆን "ሐዲስ" ማለት "አዲስ" ማለት ነው፦ 2ኛ ቆሮንቶስ 3፥14 "ብሉይ" ኪዳን ሲነበብ ያ መጋረጃ ሳይወሰድ እስከ ዛሬ ድረስ ይኖራልና። "ጽሌ" የሚለው የግዕዝ ቃል "ፊደል" "ሰሌዳ"Tablet" ማለት ነው፥ የጽሌ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ጽላት” ሲሆን “ሰሌዳዎች” "ፊደሎች" ማለት ነው፦ ዘዳግም 9፥11 ከአርባ ቀን እና ከአርባ ሌሊት በኋላ ያህዌህ ሁለቱን የድንጋይ ጽላት የቃል ኪዳኑን "ጽላት" ሰጠኝ። וַיְהִ֗י מִקֵּץ֙ אַרְבָּעִ֣ים יֹ֔ום וְאַרְבָּעִ֖ים לָ֑יְלָה נָתַ֨ן יְהוָ֜ה אֵלַ֗י אֶת־שְׁנֵ֛י לֻחֹ֥ת הָאֲבָנִ֖ים לֻחֹ֥ות הַבְּרִֽית ዘጸአት 34፥28 በዚያም አርባ ቀን እና አርባ ሌሊት ከያህዌህ ጋር ነበረ፥ እንጀራም አልበላም፥ ውኃም አልጠጣም። በጽላቱ አሥሩን የቃል ኪዳን ቃሎች ጻፈ። וַֽיְהִי־שָׁ֣ם עִם־יְהוָ֗ה אַרְבָּעִ֥ים יֹום֙ וְאַרְבָּעִ֣ים לַ֔יְלָה לֶ֚חֶם לֹ֣א אָכַ֔ל וּמַ֖יִם לֹ֣א שָׁתָ֑ה וַיִּכְתֹּ֣ב עַל־הַלֻּחֹ֗ת אֵ֚ת דִּבְרֵ֣י הַבְּרִ֔ית עֲשֶׂ֖רֶת הַדְּבָרִֽים ሁለቱም አናቅጽ ላይ "ጽላት" ለሚለው የገባው ቃል "ሉዋህ" לוּח ሲሆን ያ ሰሌዳ የድንጋይ ሰሌዳ ነው፥ አሥሩ ቃላት በአንዱ ሰሌዳ ላይ አምስት በሌላው ሰሌዳ ላይ አምስት ሆኖ ተጽፏል። ይህም ሰሌዳ የሚቀመጠው በታቦት ውስጥ ነው፥ "ታቦት" ማለት "ማህደር" "ሰገባ” “ሳጥን” “ማደሪያ”Ark" ማለት ነው፦ ዘዳግም 10፥5 ተመልሼም ከተራራው ወረድሁ። ጽላቱን በሠራሁት ታቦት ውስጥ አደረግኋቸው፥ ያህዌህ እንዳዘዘኝ በዚያ ኖሩ። ואפן וארד מן־ההר ואשם את־הלחת בארון אשר עשיתי ויהיו שם כאשר צוני יהוה እዚህ አንቀጽ ላይ "ታቦት" ለሚለው የገባው ቃል "አሮን" אָרוֹן ሲሆን ያ ሳጥን የጽላት ማስቀመጫ ነው፥ ስለዚህ ጽላት እና ታቦት ሁለት የለተያዩ ነገሮች ናቸው። የብሉይ ኪዳን ታቦት ባለ ሦስት ቅጥ"Three Dimension" ነው፦ ዘጸአት 25፥10 ከግራር እንጨትም "ታቦትን" ይሥሩ፤ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን። ሦስት ቅጥ ማለት ርዝመት፣ ወርድ(ስፋት)፣ ቁመት ያለው ይዘት"Volume" ነው፥ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ነው። አገራችን ውስጥ በየአድባራቱ እየነገሠ ያለው ታቦት ሳይሆን በቫርኒሽ የተቀባ ጣውላ ነው፥ ጣውላ ደግሞ ባለ ሁለት ቅጥ ማለትም ርዝመት እና ወርድ ያለው ገጽታ"Area" ስለሆነ ከብሉይ ኪዳን ታቦት ጋር በጭራሽ አይመሳሰልም። ታቦት ግን ሳጥን ከመሆንም አልፎ በወርቅ የተለበጠ የጽላት ማስቀመጫ ማህደር ነው፦ ዕብራውያን 9፥4 በዚያም ውስጥ የወርቅ ማዕጠንት ነበረ፥ ሁለንተናዋም በወርቅ የተለበጠች የኪዳን ታቦት፣ በእርስዋም ውስጥ መና ያለባት የወርቅ መሶብ፣ የበቀለች የአሮን በትር እና የኪዳኑ ጽላት ነበሩ። "ፕላክ" πλάξ ማለት "ጽላት" ማለት ሲሆን "ኪቦቶስ" κιβωτός ማለት "ታቦት" ማለት ነው፥ በታቦቱ ውስጥ ሦስት ነገር ማለትም መና ያለባት የወርቅ መሶብ፣ የበቀለች የአሮን በትር፣ የኪዳኑ ጽላት ይቀመጡ ነበር። በባይብል ታቦት እና ጽላት እጅግ ሰፊ የተለያዩ ነገሮች ሲሆኑ በመቅደስ ሦስተኛው ክፍል በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ የሚቀመጡ ናቸው፦ ዕብራውያን 9፥3 ከሁለተኛውም መጋረጃ ወዲያ "ቅድስተ ቅዱሳን" የምትባለው ድንኳን ነበረች።

መጅሊሥ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 42፥38 ለእነዚያም የጌታቸውን ጥሪ ለተቀበሉት፣ ሶላትንም ላዘወተሩት፣ ነገራቸውም በመካከላቸው መመካከር ለኾነው፣ ከሰጠናቸውም ሲሳይ ለሚለግሱት፡፡ وَالَّذِينَ اسْتَجَابُوا لِرَبِّهِمْ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَأَمْرُهُمْ شُورَىٰ بَيْنَهُمْ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ "መጅሊሥ" مَجْلِس ማለት "ጉባኤ"Congregation" ማለት ሲሆን በግሪክ ኮይኔ "ሲኖዶስ" σύνοδος ማለት "ጉባኤ" ማለት ነው፥ የሕዝበ ሙሥሊሙ ድምፅ በምርጫ የሚመሠረተው ጉባኤ በምክክር ነው። አሏህ ዘንድ ያለውም ምንዳ ነገራቸውም በመካከላቸው መመካከር ለኾነው በላጭና ሁል ጊዜ ነዋሪ ነው፦ 42፥38 ለእነዚያም የጌታቸውን ጥሪ ለተቀበሉት፣ ሶላትንም ላዘወተሩት፣ "ነገራቸውም በመካከላቸው መመካከር" ለኾነው፣ ከሰጠናቸውም ሲሳይ ለሚለግሱት፡፡ وَالَّذِينَ اسْتَجَابُوا لِرَبِّهِمْ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَأَمْرُهُمْ شُورَىٰ بَيْنَهُمْ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ "ነገራቸውም በመካከላቸው መመካከር ለኾነው" የሚለው ይሰመርበት! የአርባ ዘጠነኛው ስም የተወሰደው ከዚህ አንቀጽ ሲሆን "ሹራእ" شُورَىٰ ማለት "ምክክር"Consultation" ማለት ነው፥ መጅሊሡ ከሕዝበ ሙሥሊሙ የሚሰጠውን አስተያየት መቀበል አለበት! ይህንን ተቋም ለማፈረስ ከማኅበረ ቅዱሳን እስከ ፋኖ፣ ከጴጥሮሳውያን እስከ ሞዐ ተዋሕዶ፣ ከባልደራስ እስከ ኢትዮ 360 ያሉት ደሴታውያን በውስጥም በውጪም እየታገሉ እንደሆነ እየሰማን ነው፥ ኢንሻ አሏህ አይሳካላቸውም። መጅሊሡ በሁለት እግሩ ያልቆመ እና ብዙ ክፍተት ያለበት ቢሆንም ከቀድሞ ጊዜ በተሻለ ሁኔታ ዘርፈ ብዙ እና መጠነ ሰፊ ሥራ ሠርቶአልና ልናበረታታው ይገባል፥ በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ኢንሻ አሏህ ሁላችንም አሻራችንን እናስቀምጣለን። መጅሊሡ በዲን ስም የሚነግዱትን ሌቦችን፣ አጭበርባሪዎች፣ ጭልፊቶችን የማጣራት፣ የመከታተል እና የመቆጣጠር ግዴታውን መወጣት አለበት! ዲን ፓለቲካ እና መልክ መሥሪያ ወይም ገጽታ መገንቢያ አሊያም የግለሰቦች ኪስ ማደለቢያ አለመሆኑን ተገንዝቦ ወንበዴዎችን፣ ወሮበላዎችን፣ ወስላታዎችን በእንጭጩ መቅጨት አለበት! በታሪክ እና አሏህ ዘንድ እንዳንጠየቅ እና ለመጪው ትውልድ ዋጋ እንዳያስከፍለን በቅጡ እና በአግባብ መሥራት የሁላችንም ግዴታ ነው። አምላካችን አሏህ በእርሱ መንገድ ለእርሱ ብለን የምንሠራ ያርገን! ዲንን እና ኡማውን ከሚበክሉ ሙፍሢዶች ይጠብቀን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም

ወንድም ዒምራንን 1 ሚልዮን የማስገባት ተግዳሮት ተቀላቀሉ፦ https://www.tiktok.com/@emranapologetics_?_r=1&_t=ZS-96JGNgw4nLw 1M
ወንድም ዒምራንን 1 ሚልዮን የማስገባት ተግዳሮት ተቀላቀሉ፦ https://www.tiktok.com/@emranapologetics_?_r=1&_t=ZS-96JGNgw4nLw 1M

አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ሙሥሊም ወንድሞቼ እና እኅቶቼ! ባለፈው እነ ዒምራን የውይይት ጥሩ አቅርበው "የውይይት ጥሪ ከሙሥሊሞች ቀርቧል፥ እኔ ፍላጎቱ"Eager" አለኝ" በማለት ተሳዳቢው እፎይ ቪድዮ ሠራ። ያንን ተከትሎ ወንድም ዒምራን በሁለት የጋራሜዳ"Cohost" ሐሙስ ማታ ውይይት ማድረግ እንደሚችል ተናገረ። አጅሬው ተሳዳቢ በተናገረው መሠረት "እወያያለው" ወይም "አልወያይም" አሊያም "ጊዜው ይቀየርልኝ" ሳይል ዝም ብሎ ቀረ። ለአንድ ሰዓት ያክል ተጠብቆ ሲጠየቅ "አሁን ላይ የውይይት ፍላጎት የለኝም" ብሎ አረፈው። ይህንን የሰሙት ተከታዮቹ ተስፋ በመቁረጥ "አዋረድከን" በማለት በድምፅ እና በኮሜንት ሲያንቆራጥጡት አንዲት እሥልምናን የምትሳደብ "ጆኒ ራጋ" የምትባል ሴት ቤት ውስጥ ሰኞ ነገ ውይይት እንደሚደረግ ተናገረች እንጂ ቅድሚያ የኡሥታዝ ሑሱ ፈቃድ፣ ጊዜ እና የርዕስ መረጣ አልተጠየቀም፥ "ልጂቱ ሙሥሊም ናት" የሚለው ቅጥፈት ለፓለቲካ ማመቻቻ እና ማምታቻ ሲሆን ልጂቱ የቲክ ቶክ ትኩረት ፈላጊ"Attention seeker" እንጂ ሙሥሊም አይደለችም። ይህ እልም ያለ የእልህ መርፌ መዋጥ እና የፓለቲካ ጨዋታ እንጂ የውይይት ቅድመ ሁኔታ ጊዜ፣ ቦታ እና ርዕስ ያልተካተተ "ቀረ" ተብሎ ፓለቲካ እና መልክ ለማሠራት ሆን ተብሎ የታቀደ ደባ፣ ሴራ እና ተንኮል መሆኑን ከወዲህ እንድታውቁ ለቲክ ቶክ እና ለተቀረው ማኅበራዊ ሚድያ እናሳውቃለን። አልህን እና ቁጭትን ተገን ያረገ እንጂ ዕውቀትን እና ሥነ ምግባርን ዋቢ ያላደረገ መሆኑን ከወዲሁ ተረድታችሁ "ሰኞ ውይይት" እያሉ የሚያዘዋውሩት በአንድ እጅ ለማጨብጨብ መሆኑን ተረድታችሁ ለሌሎች አስረዱ! ሼር ማድረጋችሁ አትርሱ! ጀዛኩሙ ሏህ ኸይራ ። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም