HOP Ministry
Kanalga Telegram’da o‘tish
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
445
Obunachilar
+224 soatlar
+237 kunlar
+6630 kunlar
Postlar arxiv
446
https://vt.tiktok.com/ZSxvs1R6b/
Dear everyone on TikTok,
Please share and repost this gospel message so that together we can spread the Good News and invite others to come to Christ and receive eternal life.
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice.
Thank you for helping share the gospel with others. ✝️🙏
446
#ይህን_ያውቁ_ኖሯል?
እግዚአብሔር እውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትን ከእኛ ቢጠብቅም ከእኛ በሆነ አቅርቦት እንድንኖረው ግን አይጠብቅም፤ እንዲሁም አያስገድደንም። እርሱ ካልዘራበት ለማጨድ የሚሻ ጌታም አይደለም። #ከእርሱ_በእርሱ_ለእርሱ የሆነ ሕይወትን ከእኛ ይጠብቃል። እውነተኛ መንፈሳዊነት በእኛ እንዲገለጥ ከሚያስፈልገው ነገር እግዚአብሔር ያጎደለብን አንዳች ነገር የለም። የሀብቱን መጠን፣ የተሰጠውን ያላወቀ ሰው ባለጠጋ ሆኖ ሳለ በድህነት፣ በእጦት መኖሩ የማይቀር ነው።
የእስከዛሬው ጉድለታችን፣ ለእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት ባዳ መሆናችን እግዚአብሔር ይህን ሕይወት ለመኖር ከሚያስፈልገን ነገር ያጎደለብን ነገር ስላለ ነው ወይስ የተሰጠንን ባለማወቃችን? እርሱ የሚያስፈልገንን ነገር ሁሉ ሰጥቶናልና እርሱ የሚፈልገውን ሕይወት መኖርን ከእኛ ይጠብቃል።
ጸጋ ይብዛልን!!
“በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን እርሱን በማወቅ ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገንን ሁሉ የመለኮቱ ኀይል ሰጥቶናል።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 April 22, 2025
446
#Malnutrition
አንዳንድ ነገሮች ውጪ ላይ ተጀምረው ውጪ ላይ የሚያልቁ አይደሉም። ይልቁንም ከሆነው፣ ከተገለጠው ነገር ጀርባ ያለውን መንስኤ ማጤን ይፈልጋል። በውጪው ሰውነት የሚገለጠው ሁሉ የውስጡ ፍሬ አልያም የውስጡ ሰውነት ነጸብራቅ ነው።
ራሴንና ሁኔታዬን ደግሞም የአብዛኞቻችንን ሁኔታ እያሰላሰልኹ በዚህ ሕይወታችን ብዙ የማንወደው እንዲሁም ሊቀየር የተገባው ብዙ ነገር እንዳለ፤ መሆን የተገባው ትክክለኛው ነገርም ይሄ እንዳልሆነ አስተውላለሁ።
ይሄ ሁሉ ለምን ሆነ ብዬ ስጠይቅ ግን ትናንትም፣ ዛሬም ደጋግሞ ወደ ልቤ እየመጣ ያለ ነገር ቢኖር የጎደለን፣ ያጣነው፣ ያልበላነው፣ ማግኘት ሲገባን ያላገኘነው ነገር መኖሩ ነው። ቀጥሎም ይሄ ጥያቄ በአሳቤ መመላለስ ጀመረ፦ ለድርቀት፣ ለክሳት፣ ለመጠውለግ፣ ላለማፍራት የበቃነው ቤቱ ውስጥ ምግብ ጠፍቶ ነው? ወይንስ እኛ እንዲያው የተሰጠንን፣ የቀረበልንን ወስዶ መብላት አቅቶን?
የያዘን በሽታ ጉዳይ እጅግ አሳስቦኛልና ቀጥዬ ስራዬ አልኩና ስለ #Malnutrition (የአስፈላጊ ንጥረ ነገሮች፣ ምግቦች እጥረት) ምልክቱ ምንድነው? የሚያስከትለው ጉዳትስ ብዬ ማንበቤን ቀጠልኩ። ይሄ እንግዲህ ለዚህ ለሟች ስጋችን ነው፦ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ የማያቋርጥ ድካም፣ ትኩረት ማጣት፣ በተደጋጋሚ በተለያየ በሽታ መጠቃት፣ ከበሽታው ፈጥኖ ማገገም አለመቻል፣ አለማደግ፣ የከሳና የተጎሳቆለ ተክለ-ሰውነት......እነዚህ እና የመሳሰሉት ሁሉ አንድ ሰው ሊያገኝ የተገባውን ንጥረ ነገር ባላገኘ ጊዜ የሚከሰቱ ነገሮች ናቸው።
ይሄ ሁሉ ለሥጋችን፣ ለሰውነታችን ተገቢውን እንክብካቤ ከማድረግ አንጻር አስፈላጊ መረጃ መሆኑ እንዳለ ሆኖ የእኔ ዋናው ነጥብ ግን ይሄ አይደለም። ልናበላው ሲገባ ያላበላነው፣ ልንመግበው ሲገባ ስለተራበው #የውስጥ_ሰውነታችን እንጂ።
የሚያስፈልገውን ነገር ከማጣቱ የተነሳ የውጪው ሰውነታችን የሚሆነውን ነገር ሁሉ የውስጥ ሰውነታችንም ይሆነዋል። ለመንፈሳዊው ነገር ፍላጎትና ረሃብ ማጣትም ሆነ ድካም፣ ትኩረት ማጣትም ሆነ መንፈሳዊ በሽታና ውድቀት፣ በበሽታው መማቀቅም ሆነ አለማደግ፣ ክሳትና ጉስቁልናም ሁሉ ባልበላን፣ የሚያስፈልገንን መንፈሳዊ መብል ባላገኘን መጠን የእኛ ሆነዋል።
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን ደግሞ የእኛ ሕይወት እድገት የአንድ ቀን ሳይሆን የሂደት፣ የመሰራት፣ የመገንባት፣ የመታነጽ ጉዳይ ነው። ለማደግም መንፈሳዊው መብል፣ የእግዚአብሔር ጸጋና እውቀት ብቸኛው አማራጭ ነው።
ችግሩ ግን ምን እንደሚያሳድገን አለማወቃችን ጋር ሳይሆን እያወቅን ወደሚያሳድገን ነገር አለመጠጋታችን፣ የሚያሳድገንን ነገር አብዝተን አለመፈለጋችን፣ የሚያሳድገን ነገር ላይ አለመጣበቃችን፣ ለሚያሳድገን ነገር ጊዜና ትኩረት አለመስጠታችን፣ የሚበላው ሳይጠፋ መብላት አለመፈለጋችን፣ በሕይወት ከሚያሰነብተን፣ ሕይወት ከሚገኝበት ነገር ይልቅ ተራና የማይጠቅመንን መውደዳችን ላይ ነው።
ታዲያ በዚህ ሁኔታ ብንደርቅ፣ ብንጠወልግ፣ ፍሬ ባይገኝብን ምን ይገርማል? ሰጪው ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት ከሚያስፈልገን ነገር አንዳች ሳያጎድልብን ከእኛ ስንፍና የተነሳ ግን አለማደግ መለያችን ቢሆን ምን ይገርማል?!
“በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን እርሱን በማወቅ ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገንን ሁሉ የመለኮቱ ኀይል ሰጥቶናል።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)
“ነገር ግን በጌታችንና በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ዕውቀት እደጉ፤ ለእርሱ አሁንም፣ ለዘላለምም ክብር ይሁን፤ አሜን።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 3፥18 (አዲሱ መ.ት)
“በድነታችሁ እንድታድጉ፣ አዲስ እንደ ተወለዱ ሕፃናት ንጹሑን መንፈሳዊ ወተት ተመኙ፤”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥2 (አዲሱ መ.ት)
✍️ መክሊት አየለ
📆 March 10, 2025
446
Repost from Amharic Spritual Books
Yosef_Alamrew_አሸንፌ_ኖራለሁ_Endale_Woldegiorgis_Ethiopian_Protestant.m4a7.80 MB
446
#ድኻው_ማንነው?
እኛ እና የእኛ ላይ ተደግፈን ሕይወቱን እንድንጀምር፣ እግዚአብሔርንም እንድንመስል አልተጠራንም። ይልቁንም ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል፤ ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገንን ሁሉ ሰጥቶን ሜዳውም ፈረሱም ያው! አለን እንጂ።
በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን ባናውቅ፣ ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገን ነገር ሁሉ እንደተሰጠን ባንረዳ፣ እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚያስፈልገውን ኃይል፣ ግብአትና አቅርቦት ፍለጋ ስንኳትን ብንውል፤ ድኻው ማነው? ሰጪውን፣ ደግሞም የተሰጠንን ያላወቅን እኛ ወይስ ሁሉ በሁሉ የሆነው፣ የማይነጥፈው፣ ሳይነቅፍ በልግሥና የሚሰጠው የመለኮቱ ኃይል?!
ዛሬ ወደ ቅዱሱ ቃል ጠጋ ብዬ ሁለተኛይቱን የሐዋርያው የጴጥሮስ መልዕክት ሳጠና፤ የምወደውን፣ ደጋግሜ ያነበብኹትን፣ ያሰላሰልኹትን፣ ለእግዚአብሔር ለመኖር ኃይልና ብርታት የሚሆነኝን የከበረ ቃል እንደ አዲስ ተመለከትኹ። እርሱም፦
“በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን እርሱን በማወቅ ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገንን ሁሉ የመለኮቱ ኀይል ሰጥቶናል።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)
የሚል ነው።
ይሄ ቃል ደስታዬ፣ ተድላዬም ነው፤ ደጋግሜም አሰላስዬዋለሁ። ከዚህ በታች በአንድ ወቅት በነበረኝ ቃሉን የማሰላሰል ጊዜ የከተብዃትን፣ ደግሞም ለእኔ እንደሆነችው ሁሉ ለሌሎችም በረከት ትሆን ዘንድ
በ October 6, 2024 ያጋራኋትን ጽሁፍ ዳግም ላጋራችሁ።
#ሜዳውም_ፈረሱም_ያውላችሁ!
እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በርህራሄው ወደ ራሱ ሳበን፤ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን፤ ጠራን። ታዲያ ከጠራን በኋላ ዋናው መምጣታቸው ነው፤ እንዴት እንደሚኖሩ እነርሱ ያስቡበት ብሎ ለራሳችን አልተወንም፤ ይሄን ሕይወት እንዴት ነው የምኖረው? እውነተኛ መንፈሳዊነትስ እንዴት ነው በእኔ የሚገለጠው? ብለን ግራ እንዳንጋባ #ለሕይወትና_ለእውነተኛ_መንፈሳዊነት_የሚያስፈልገንን_ሁሉ_በመለኮቱ_ኀይል_ሰጥቶን ሜዳውም ፈረሱም ያውላችሁ አለን። የተሰጠውን የማያውቅ፣ አውቆም የማይጠቀምበትና የማይኖርበት ሰው፦ ሳያጣ ያጣ፣ በድህነት የሚኖር ባለጠጋ ነው። ከእግዚአብሔር የተሰጠንን በማወቅ፣ በእርሱም በመኖር ማረፍ ይሁንልን!!
“በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን እርሱን በማወቅ ለሕይወትና ለእውነተኛ መንፈሳዊነት የሚያስፈልገንን ሁሉ የመለኮቱ ኀይል ሰጥቶናል።”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥3 (አዲሱ መ.ት)
ዛሬም ሜዳውም ፈረሱም በመለኮቱ ኃይል ተሰጥቶናልና፦ ሳያጡ ያጡ፣ በጉስቁልና የሚኖሩ ድኾች አንሁን! እላለሁ። የተሰጠንን በማወቅ፣ በሰጪው ታምነንና ተደግፈን፣ በሙላት እንኑር!!
✍️ መክሊት አየለ
446
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እደሚታወቀው በዚህ ቻናል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል የተለያዩ መንፈሳዊ፣ የጥሞና ጽሁፎች አንዱ እንደሆኑ ይታወቃል።
ጽሁፉን የምናቀርብበት ዋና ዓላማ በግል የተማርነውን እና የተጠቀምንበትን ነገር ሌሎች እንዲጠቀሙበት እና እንዲታነጹ ለማድረግ ነው። በዚህም ብዙዎች እየተጠቀማችሁ እንዳለ እምነታችን ነው።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በዚህ ቻናል ላይ የሚቀርቡ ጽሁፎች በቀጥታ #Copy ተደርገው በተለያየ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ እየተሰራጩ እንደሆነ አስተውለናል። መልዕክቱ ብዙ ሰዎች ጋር እየደረሰ በመሆኑና ብዙዎች እየታነጹበት ስላለ እጅግ ደስተኞች ነን። ነገር ግን የራስን ገጽታ ለመገንባት በማሰብ ደግሞ ልክ እንደግል ጽሁፋችሁ አድርጋችሁ፣ ስማችሁን ጠቅሳችሁ #Post በምታደርጉ ሰዎች ደግሞ ተግባራችሁ እንደ ክርስቲያን አግባብ አይደለምና አዝነናል።
ስለዚህ መጽሐፍትን ጨምሮ የተለያዩ የሰው ስራዎችን ከተለያዩ የሚድያ አማራጮች ላይ፦
ከፌስቡክ ገጽ፣ ከቴሌግራም ቻናል.... ላይ የሌላን ሰው ጽሁፎችን፣ ስራዎችን ስትወስዱ እና በግል ገጻችሁ ላይ ስታጋሩ የጸሀፊውን ስም፣ የቴሌግራም ቻነል ወይም የፌስቡክ ገጽ ስም፣ ያገኛችሁበትን ምንጭ ብትጠቅሱ፣ አልያም ትምህርተ ጥቅስ (" ") ብትጠቀሙ፤ ካልሆነም #Share ብታደርጉ መልካም ነው።
✍️ መክሊት አየለ
446
📢 Dear Subscribers,
We are pleased to inform you that direct messaging is now open on our channel. You are welcome to share your feedback, suggestions, questions, and encouragement with us through this platform.
Your input is valuable and helps us improve our ministry and future Bible study programs.
We also encourage you to stay connected with us as we continue to grow together in God's Word and seek to draw closer to Him.
Thank you for being part of our community.
Blessings,
HOP Ministry
Hear. Obey. Practice.
Join us and invite others to grow together in God’s Word.
📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10
446
#ራሴን_ችዬ_ከቤት_እወጣለሁ!
ህጻናት በልጅነታቸው ወራት ከወላጅ፣ አሳዳጊዎቻቸው ጋር ሲኖሩ በማን ላይ ሸክም ይሁኑ አይሁኑ፣ ስለ እነርሱ ማን ይጨነቅ አይጨነቅ፣ ወጪያቸው በማን ይሸፈን አይሸፈን ልብ አይሉም፤ ይሄ ሁሉ ግድ አይላቸውም።
በሰል እያሉ ሲሄዱ ግን ይሄን አድርጉልኝ፣ ያንን ግዙልኝ ከሚለው ጥያቄያቸው ይነሱና በቤተሰባቸው የሚደረግላቸውን ነገር፣ የሚያገኙትን ጥቅም መቁጠር ይጀምራሉ። ለፍላጎታቸው ሁሉ መልስ ማግኘት ሲያቅታቸው፣ ቤተሰባቸውንም ያስቸገሩና ሸክም የሆኑ ሲመስላቸው፣ ደግሞ የቤተሰባቸው ስለ እነርሱ መድከም ግድ ሲላቸው፦ በተለምዶው እንደሚባለው #አስራ_ስምንት (18) ዓመት ይሙላኝና፣ ትምህርቴን ልጨርስና፣ ሥራ ልያዝና፣ ትንሽም ብትሆን የራሴ ገቢ ትኑረኝና #ራሴን_ችዬ_እወጣለሁ! ይላሉ። በዚህ ውስጥ በቅንነትም ሆነ ባለማወቅ የተጠነሰሰ ከጥገኝነት የመላቀቅ ጥማት፣ ጩኸት ይስተዋላል።
እኛም እንዲሁ ገና ደካሞች ሳለን ከወደደን ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ሕብረት ገና በኃጢአትና በድካም ተጥለን ስንኖር ሳለን የተጠነሰሰው ፍቅር አድጎ በቤቱ ኖረን፣ ኖረን፣ ኖረን.....መጎልመስ ስንጀምር፣ በራሳችን ለመቆም አቅም ያገኘን ሲመስለን፤ ጥንት በስብራታችን ዘመን የጠገነንን፣ ደግፎም ያቆመንን እግዚአብሔርን ዝንግት እናደርግና፦ ሕይወቱ፣ አገልግሎቱ፣ ሥራው፣ የያዝነውና የጨበጥነው ነገር ሁሉ ስክትክት ብሎ ሲቃናልን፤ ያለ እኔ ማን ብርቱ ይኖራል? ሁሉ በእጄ እንደሆነ ሁኔታዬ አይናገርም? ለማለት እየዳዳው ልባችን በትዕቢት ውጥር ይልና የእግዚአብሔርን ፊት፣ ጥገኝነታችንን ችላ ብለን ራሴን ችዬ ከቤት እወጣለሁ እንላለን። ቃል በቃል ለእግዜር እንዲህ ባንለው እንኳ በልብና በተግባራችን ከፊቱ በመኮብለል፣ እርሱን ባለመደገፍና ባለመታመን እራሳችንን እንደቻልን እናሳየዋለን። ሆኖም ከአጉል ስብራት፣ ባልተገባ መንገድ ሲሮጡ ከመውደቅና ከመጋጋጥ ውጪ አንዳች አናተርፍም።
አስጠግቶ ድካምን ያስጣለኝን፣ የማይነጥፍ ብርታት የሆነኝን እግዚአብሔርን ገፋ አድርጌ፤ ሁሉን ለማድረግ ብቁ የሆንኹ፣ የበሰልኹ፣ አስተዋይ ነኝ ባልሁና ራሴን የቻልኹ በመሰለኝ ጊዜ እንክት ብዬ ስሰበር፣ ብርታቴ ነጥፎ ባዶ ስሆን በደንብ አይቻለሁ።
ታድያ ከስብራት፣ ከግል ጉዳትና ቁስል በላይ የሚያነቃ ጥሩ መምህር የለምና አሁን ለነፍሴ ደጋግሜ የምነግራት፣ #ለመጠጊያ_ዓምባዬ_ለእግዚአብሔርም የምነግረው ነገር ቢኖር፦
#ራሴን_ሳልችል_በቤትህ_እኖራለሁ፤ #ጥገኛህ_እንደሆንኹ_ከአንተ_ጋር_እኖራለሁ። የሚል ነው።
ምክንያቱም ራሴን ችዬ ከቤትህ እወጣለሁ የሚለው ትዕቢቴ ሲሰብረኝ እንጂ አንዳች ብርታትና ትርፍ ሲሰጠኝ አላየሁም። ይልቁንም የእርሱ ጥገኛ መሆኔ፣ በቤቱ መኖሬ፣ ራሴን አለመቻሌ እጅጉን ሲጠቅመኝ አይቻለሁ።
ከቤቱ የማልወጣበት፣ ራሴን የማልችልበት፣ ዘወትር የእርሱ ጥገኛ የምሆንበት ምክንያቴም ያለ እርሱ ምንም ማድረግ አለመቻሌ ነው። ስለዚህ ግብዝነትና ትዕቢቴን ዋጥ አድርጌ፤ በድፍረትና በልበ መሉነት፣ በደስታም እግዚአብሔርን፦ #እኔ_የዘላለም_ጥገኛህ_ነኝ፤ #አንተም_የዘላለም_ዓምባዬ_ነህ፤ #እኔም_ያለ_አንተ_ምንም_ማድረግ_አልችልም።
እለዋለሁ!!
446
+4
በየዋህነት እግዚአብሔር ልብ ሰፈር መሰንበት፣ ብልጣብልጥ ሆኖ ከእግዚአብሔር በላይ ለራሴ አውቃለሁ አለማለት የእግዚአብሔርን ይዞ ለመውጣት ይጠቅማል።
በራሴ ምንም ማድረግ አቅቶኛል ብሎ፣ እስርስር እንዳለ ገብቶት፣ ታስፈልገኛለህ እያለ እግዚአብሔር እግር ስር የተደፋ ሰው ሩቅ የመሄጃ ምስጢሩ ገብቶታል።
ሌሊት ከእቅልፋችን ስንነቃ፣ ማልደንም ስንነሳ ማንኛውንም ነገር በራሳችን ማድረግ አለመቻላችን ገዝፎ ከታየን፣ ያለ እግዚአብሔር ንቅንቅ ማለት ካቃተን የእርሱ ጥገኛ መሆናችን በርትቷልና ድል መንሳታችንም በዛው ልክ ይጨምራል።
እርሱን የሙጥኝ ማለቱን ከተያያዝነው እኛነታችንም ሆነ ነገራችን በእርሱ መሰራቱ አይቀሬ ነው!!
446
አለመውደዳችን በዝቶ የገለጥነው ኃጢአት በዛ።
ብዙ ብንወድድ ብዙ ኃጢአት መሸፈን በቻልን ነበር። ትግላችን ኃጢአቱን ካለመሸፈናችን ጋር ሳይሆን ካለመውደዳችን ጋር ይሁን። ብዙ ፍቅር ሲኖረን፣ እርስ በእርሳችን ከልብ ስንዋደድ ብዙ ኃጢአትን እንሸፍናለን።
እግዚአብሔር በሰጠን በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር እንደገና በልባችን ይፍሰስ። በተወደድንበት መውደድ ሌሎችን መውደድ እንድንችል፣ ይቅር እንደ ተባለ ሰው ይቅር ማለት እንድንችል ጸጋ ይብዛልን!!
“ፍቅር ብዙ ኀጢአትን ይሸፍናልና ከሁሉ በላይ እርስ በርሳችሁ ከልብ ተዋደዱ፤”
— 1ኛ ጴጥሮስ 4፥8 (አዲሱ መ.ት)
446
https://vt.tiktok.com/ZSx4WmNK1/
🌿 Stay rooted in God’s presence.
Daily devotionals • Christian encouragement • Faith-building content
Follow hopministry and grow with us. ✨
446
በወንዙ ዳር የተተከሉት ዛፎችና ከወንዙ ርቀው የሚገኙት መልካቸው ለየቅል ነው፤ በፍሬያቸውም በቀላሉ ተለይተው ይታወቃሉ።
በወንዙ ዳር የተተከሉት ዛፎች ሊያለማቸው ወድዶ ያለማቋረጥ የሚያጠጣቸው ምንጭ አለና ፍሬያቸውም አያቋርጥም። ከወንዙ መገኛ የራቁት ግን የሚያጠጣቸውን ምንጭ ተለይተዋልና ለሀሩርና ለድርቅ የቀረቡ፣ የተጋለጡ ናቸው።
ከሞት ጋር እየተጋፈጥን በምንውልበት በዚህ ዓለም ከሕይወት ውሃ ወንዝ ጋር መጣበቅን ማስቀደም አለብን። የዚህን ጊዜ ድርቁን መቅደም፣ ሀሩሩን ማሸነፍ፣ ልምላሜን ገንዘባችን ማድረግ እንችላለን።
በውጭ ካለ ሀሩር፣ ድርቅ በውስጥ ሰውነት ባለ ብርታት የሚያስመልጥ እግዚአብሔር ይባረክ!! ሀሩሩ ምን በርትቶ ቢያቃጥል ከተተከልንበት፣ ዘወትር በሕይወት ለመኖር ከምንጠጋጋው የሕይወት ውሃ ምንጭ በልጦ አያደርቀንምና ከሀሩሩ ግለት በላይ በምንጩ ሕያውነት ላይ እናተኩር።
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እንድጸልይ፣ ቃልህን እንዳነብና እንዳሰላስል፣ የሕይወት ውሃ ምንጭ ከሆንኸው ከአንተ ጋር ተጣብቄ እንድቆይ፣ ዘወትር የሕይወትን ቃል እንድበላ እርዳኝ!! ከወንዙ ርቄ እንዳልቆም፤ ይልቁንም ከወንዙ ዳር እንድተከል ጸጋህን አብዛልኝ።
መዝሙር 1 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² ነገር ግን ደስ የሚሰኘው በእግዚአብሔር ሕግ ነው፤ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያሰላስለዋል።
³ እርሱም በወራጅ ውሃ ዳር እንደ ተተከለች፣ ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣ ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ነው፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።
