Usmanic Islamic psychology/ ስለ ሰው ልቡና
Kanalga Telegram’da o‘tish
- እውነተኛ የህይወት ታሪኮች - ኢስላማዊ የስነልቦና ምክሮች ፣ ጥያቄዎች እና አገልግሎቶችን ያገኛሉ። - ስለ ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ ይማራሉ። - ሳምንታዊ ሽልማቶች ለሁሉም በማጋራት የሙስሊሙ ኡማ የአይምሮ ጤና የሚጠበቅበትን ይህን ቻናል እናሳድግ ጥያቄ ለማቅረብ እና አገልግሎት ለማግኘት @usmanoman ላይ ያናግሩን።
Ko'proq ko'rsatishMamlakat belgilanmaganToif belgilanmagan
911
Obunachilar
+9924 soatlar
+2937 kun
+51330 kun
Postlar arxiv
የዚህ ሳምንት ተሸላሚ 📦
-ሬድዋን ሰይድ ከ ወሎ ዩኒቨርስቲ
ሆኗል።-
ምድር ላይ የሰው ልጅ ስለሚያጋጥመው ፈተና እና ተስፋ ከ 9 - 15 መስመር ባልበለጠ ሀሳብን የመግለፅ ውድድር ባለቀ የስነፅሁፍ ውበት እና የዳኛ ድምፅ እና የሰዎች ምርጫ አሸናፊ በመሆን የ'ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ' መፅሐፍ እና የሳምንታዊ ኢንተርኔት ፓኬጅ ተሸላሚ ሆኗል።
ለሁላችሁም ተወዳዳሪዎች እና ተሳታፊዎች በአላህ ስም ከልብ እናመሠግናለን።አብሮነታችሁ አይለየን!!
ያሸነፈው ፅሁፉ ከታች ተያይዟል።
👇👇
"የሰው ልጅ በምድር ጉዞው በፈተና እሳት ውስጥ አልፎ የሚበቅል ብርቅዬ ፍጥረት ነው፤ እሾህ በበዛበት መንገድ ላይ እያለቀሰ እንኳን ወደ ፊት የሚራመደው በልቡ የጫራት ጥቂት የተስፋ ጭላንጭል ጨለማውን የመስበር አቅም ስላላት ነው። መከራ የጠንካራ ማንነት መፅሐፍ ገፅ እንጂ የመጨረሻው ምዕራፍ አለመሆኑን የተረዳ ሰው፣ ፈተናን ማለፊያ ድልድይ እንጂ መቆሚያ ግድግዳ አድርጎ አይቆጥረውም። ሁልጊዜም ከፅኑ ጨለማ በኋላ የሚፈካው የጠዋት ብርሃን እንዳለ ሁሉ፣ በፈጣሪ ቸርነትና በርህራሔው ላይ የተጣለ እውነተኛ ተስፋ የትኛውንም እሳት ወደ ለምለም ገነት የመቀየር ተአምር አለው!!!"
ሬድዋን ሰይድ ✍️
አሸናፊ የሆነው ተሸላሚው የሚለይበት ሰአታት እየተቃረቡ ነው።
መራጮች ምርጡ ተመራጮች አስመርጣችሁ አጠናቅቁ።
ሁላችንም እየጠበቅንህ ነው ጌታዬ 🙏። ሀጃችን ብዙ ነው ወደ አንተ የሚያመላልሰን 🔄።
በቅፅበት ሁሉንም ልታሳካልን ሳይሳንህ ግን ፍቅርህ ነው ❤️ እና ከደጅህ የምንመላለስበትን ጉዳይ እልፍ አደረከው ✨
ምኞቶቻችን ወደ አንተ የሚያቀርቡን ፀሎት ናቸው 📿። ህልማችን ዘውትር አንተን በትህትና እንደንጠይቅህ የሚያስችሉን ተስፋዎቻችን ናቸው 🌟።
በራህመትህ ጎብኘን አዛኙ ጌታ ሆይ! 🙏
'አላህ የወሰነው' እና 'አላህ የፈቀደው'
-ነፃ - ፍቃድ/ free will -
ሁሉም ነገር የሚሆነው በአላህ ፍቃድ ሲሆን በተሰጠን ነፃ ፍቃድ ውስጥ ሁሉንም ነገር የምንወስነው/የምንመርጠው ግን እኛ ነን።
አላህ እንዲሆን የፈቀደው ማለት አላህ የወሰነው (predestined) ማለት አይደለም።
እኛ ነን ምንናገረውን የምንወስነው ፣ እኛ ነን ጓደኞቻችን እነማን መሆን እንዳለባቸው የወሰነው። እኛ ነን ተግባሮቻችንን ስራዎቻችንን....የምንመርጠው የምነወስነውም።
ሰዎች በራሳቸው ስህተት እና አላህ የሰጣቸውን አቅል/የማገናዘብ አቅም በቅጡ ሳይጠቀሙ ህይወታቸው ላይ ለሰሩት ስህተት አላህ ወስኖብኝ/ሽቶብኝ ነው ይላሉ። አዎ ያለ አላህ ፍቃድ ያን ነገር መፈፀም አይችሉም ነበር ግን ነፃ ፍቃዳቸውን ተጠቅመው የተሻለ ነገር ላይ የመድረስንም ሰበብ ማድረስ ይችሉ ነበር።
አላህን ሰበብ እያደረጉ መቆዘም የቀደር ግንዛቤ ድክመት ነው።
ሁሉም ነገር (አተነፋፈሳችን ፣ ጠብ የምትለው ውሀ ፣ አይምራችን ሊረዳቸው የማይቻሉ ደቂቅ ነገሮች ሁሉ አስቀድመው የተፃፉ ናቸው)
ምድር እና ሰማይ ከመፈጠራቸው 50ሺ አመታት በፊት ነገራት በሙሉ ለህወል መህፉዝ ላይ ሁሉን አዋቂ በሆነው ጌታ የተከተቡ ናቸው።
የምናደርገው ነገር ይታወቃል ማለት የማድረግ ነፃ ፍቃዳችን ተፅእኖ ስር ነው ማለት አይደለም ከጊዜ እና ከቦታ ገደብ ውጪ የሆነው ጌታ አላህ ግን ምን እንደምንወስን እና እንደምናደርግ ከእኛ የማሰብ አቅም ውጪ በሆነ መንገድ ቀድሞ ያውቃል።
ይህ ደግሞ ሀኪም/ጥበበኛ እና አዚም/ታለቅ የመሆኑ ሚስጥር ነው።
#ስለ_ቀደር
#usman_mus ✍️
ኡስማኒክ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ
#2 ሽልማት የሚያስገኝ ሀሳብን በፅሁፍ የመግለፅ ውድድር 5 የመጨረሻ ዙር ተፋላሚዎች ተለይተዋል።
ከታች በሰማያዊ የተፃፉትን የተወዳዳሪዎች ቅደም ተከተል በመንካት እና በመግባት ኮሜንት ውስጥ ከ የወደዳችሁት ተቀ ፅሁፍ ላይ ሪአክት በማድረግ እንዲያሸንፉ አግዟቸው። ብዙ ሪአክሽን ያገኘ የማሸነፍ እድሉ ከፍ ይላል።
የህዝብ ድምፅ 40% የዳኛ 60% ድርሻ ይይዛል።
ፀሀፊዎችም ሊንኩን በመላክ ሪአክት ማስደረግ ይችላሉ።
መልካም እድል
አንደኛ ተወዳዳሪ
ሁለተኛ ተወዳዳሪ
ሶስተኛ ተወዳዳሪ
አራተኛ ተወዳዳሪ
አምስተኛ ተወዳዳሪ
5,ተስፋ መቁረጥ ሲሰማን ይህን ዱአ በማለት የአላህ ምራቻ እንጠይቅ
اللهم إني أسألك رحمةً من عندك وعملًا صالحًا تقربني إليك.
አላህ ሆይ ምህረትህን እንዲሁም ወደ አንተ የምታቀርበኝን መልካም ስራ ትለግሰኝ ዘንድ እጠይቅሃለሁ።
የዚህ ዱአ ስነልቦናዊ ጠቀሜታዎች
- በጎ የማድረግ ሞራላችን ያነቃቃል
- በአላህ በመመራት እና በመመካት ውስጥ መስከን ውስጥ እንገባለን።
ፅሁፉን የማስገቢያ ጊዜ የመግሪብ አዛን ላይ ይጠናቀቃል። መሳተፍ የምትፈልጉ የቀሩትን ሰአታት ተጠቀሙበት።
ኢስላሚክ ሳይኮሎጂ/ኢልመ- ነፍስ
ክፍል 4. አቅል
-ፊጥራ
-ነፍስ
-ሩህ
-አቅል/አይምሮ
-ቀልብ/ልብ
-ተዝኪየቱ ነፍስ/ራስን ከወንጀል ማፅዳት
ለዛሬ አቅልን በጣም በአጭሩ እናያለን ኢንሸአላህ!
አቅል ምንድነው?
የአቅል (عقل) (mind) ስርወ - ቃል መሠረተ ትርጉም መገንዘብ ፣ መረዳት ፣ ማወቅ የሚል ትርጉም አለው።
ይህ የሰው ልጅ በምክንያት/አምክንዮ የሚያስብበት ክፍል ሲሆን ፥ እውነትን ከውሸት የሚለይበት ፍጥረተ አለሙ የሚረዳበት እና የሚገነዘብበት የማስተዋያ ክፍሉ ነው።
አቅል እስካሁን ካየናቸው የሰው ልጅ መሰረታዊ የማንነት ክፍሎች አንዱ ሲሆን ስለራሱ ስለሰዎች እና ስለፈጣሪው በትክክል እና በጥራት እንዲያስብ የሚያደረገው መሣሪያ ነዉ
አቅል በኢስላሚክ ሳይኮሎጂ ጥናት ውስጥ
በኢስላሚክ/በኡስማኒክ ሳይኮሎጂ ውስጥ አቅል መስታወት ሆኖ ሰው አለምን የሚያይበት የመመልከቻ መነፅሩ ነወ።
በተለያዩ ምክንያቶች የእውነት እና የፍትህ ሚዛኑ የተዛባ አይምሮን እና በሀቅ ላይ ቆሞ በጥራት ህይወትን መገንዘብ ያቃተውን አይምሮ በማገዝ የሰዎችን የማመዛዘን ተፈጥሯዊ ማንነት የማስመለስ ህክምናዊ እና ስነዘዴያዊ መንገዶችን ይከተላል።
ኢስላማዊ ሳይኮሎጂ መፅሀፍ
አዘጋጅ እና ፀሀፊ ኢስላሚክ ሳይኮሎጂስት ኡስማን ሙስጠፋ)
ኢንሻአላህ ይቀጥላል...
#2 ሽልማት የሚያስገኝ ሀሳብን በፅሁፍ የመግለፅ ውድድር
ርእስ እና የመወዳደሪያ መንገድ :- ምድር ላይ የሰው ልጅ ስለሚያጋጥመው ፈተና እና ተስፋ ከ 4-7 መስመር ባልበለጠ በጥሩ አገላለጽ እና ሳቢ የአፃፃፍ ስልት ኮሜንት መስጫው ላይ በማስቀመጥ ተወዳደሩ!
አሪፉ ፅሁፍ ታይቶ አሸናፊው ሽልማቱን ይወስዳል።ኢንሻአላህ!
ሽልማቱ:- የ ፍፁም ሰው ፍፁም ነብይ መፅሀፍ እና የሳምንታዊ 780 ሜ.ባ የኢንተርኔት ፖኬጅ
#ከኡስማኒክ_ኢስላሚክ_ሳይኮሎጂ
መልካም እድል!
ጥያቄ 3
ልማር ወይስ ላቁም?
እኔ የ18 ወጣት ስሆን ቀጣይ አመት የ 12ተኛ ክፍል ተፈታች ነኝ። ትምህርት የሚሆንልት አይነት ሰው ብሆንም ታላላቆቼ ተምረው ያሰቡትን ማሳካት አለመቻላቸውን ሳይ እና 'ትምህርት አያሳልፍልህም አርፈህ ተፍ ተፍ በል' የሚሉ መሰል ተደጋጋሚ ምክሮችን ስሰማ ተስፋ ስለቆረጥኩኝ።
የ ቀጣይ አመት የ12ተኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ወስጄ የትምህርት አለምን ልሰናበት ወይ? በሚል ጥያቄ ራሴን እያፋጠጥኩኝ አለው። እባክህን ለኔ እና ለመሰል ጓደኞቼ በትምህርት ጉዳይ ያለህን አቋም ብታሳውቀን። አመሠግናለሁ።
(መልስ እሰኪሰጥ ድረስ አስተያየታችሁን ታች አሰፍሩ)
