196
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+47 kun
-430 kun
Postlar arxiv
አንድ ጊዜ አንድ ድሀ ልጅ ነበር። ስሙ ኤልያስ ይባል ነበር። በቀን ይሠራ ነበር፣ በማታም ያጠና ነበር። አንዳንድ ጊዜ በጣም ይደክመው ነበር፣ ጓደኞቹም “አትችልም” ይሉት ነበር።
ነገር ግን ኤልያስ አንድ ነገር ያምን ነበር፦
“ዝግ በር ማለት መንገድ የለም ማለት አይደለም።”
አንድ ሌሊት በጣም አዝኖ ተቀምጦ እያጠና ነበር። መብራቱም ጠፋ። እሱ ግን በትንሽ ሻማ ብርሃን ማንበቡን ቀጠለ።
ዓመታት አለፉ። ኤልያስ በትምህርቱ ጎበዝ ሆነ፣ ታላቅ ሰውም ሆነ። አንድ ቀን ሰዎች የስኬቱን ምስጢር ሲጠይቁት፣ እንዲህ አለ፦
“ጨለማ በመጣ ጊዜ መቆም አልመረጥኩም፤ ትንሽ ብርሃን ፈልጌ መሄድ ቀጠልኩ።”
ተስፋ ትንሽ ብትሆንም ሕይወትን ማብራት ትችላለች። 🕯️✨
ከጨለመ አይደል...
ኩራዝ ትዝ ሚልህ
መሸት ሲል አይደል...
የብርሃን ጥቅሙ የሚገለጥልህ
ሲበርድህም አይደል...
ፀሀይ ምትናፍቀው
[እንግዲህ እሷንም]
ያጣሃት እለት ነው...
ፍቅሯን እምታውቀው @luna2117
