ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Відкрити в Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Показати більше2 936
Підписники
+1424 години
+3877 днів
+38530 днів
Архів дописів
ስቦ ማስከዳቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
#_የሻለቃ_ዘመቻ_መሪው_50አለቃ_ከፍያለው_አምሳሉ_እና_5የሚሊሻ_አባላት ከግንደወይን እና ከዋበር ከተማ በመውጣት ፋኖን ተቀላቅለዋል።
==========================
.....ነሐሴ 04/12/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት ከግንደወይን እና ከዋበር ከተማ ወጥተው 201ኛ ኮር 74ኛ እና 54ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን፦
1.50 አለቃ ከፍያለው አምሳሉ ..የሻለቃ ዘመቻው ክላሽ 3ካዝና ሙሉ ተተኳሽ እና 1መገናኛ ሬዲዮ በመያዝ ወደ 54ክ/ጦር
2.ይበልጣል የስጋት...ሚሊሻ74ኛክ/ጦር
3.ውጣባቸው ጌታውአንተ....ሚሊሻ
4.ሙጨው ፀጋ............ሚሊሻ
5.ብርሀኑ አበረ............ሚሊሻ
6.ሙሉቀን ጌታው.......ሚሊሻ ሲሆኑ ለሌላ እልቂት ትሄዳላቹህ በማለት እያስጨነቁት ሲሆን ሁሉም የብልፅግና ሰራዊት አባላት የመዋጋት ስነ ልቦና የሌለው መሆኑን እና ለመውጣት ሁኔታወችን እየተጠባበቁ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን አሁንም ቢሆን አልረፈደም ወደ ወንድሞቻቹህ ተመለሱ ኑ በክብር እንቀበላቹሀለን በማለት ጥሪያችን እናስተላልፋለን።
የአፋብን ጎጃም ጠቅላይ ግዛት ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የብልፅግና መከላከያ ሠራዊት ከገዳ ኮማንዶ ጋር በመቀናጀት በጉሙዝ ሕዝብ ላይ ጭፍጨፋ ከፈተ!
ከብልፅግና መከላከያ ሠራዊት፣ ከገዳ ኮማንዶና ከሚኒሻ የተወጣጣ ጥምር ወታደራዊ ኃይል፡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን ሚዚጋ ወረዳ(በቀድሞው በለውጅጋንፎይ ወረዳ) ሜጢ ቀበሌ ላይ ከቀናት በፊት ጀምሮ በከባድ መሣሪያ የታገዘ ጥቃት ከፍቶ በርካታ ንፁኋን የጉሙዝ ብሔረሰብ አባላትን መግደሉን የመረብ ሚዲያ ምንጮች ገልፀዋል።
በጥቃቱ ከተገደሉት በተጨማሪ በርካታ ንፁኋኖች የቆሰሉ ሲሆን፡ ሃብት ንብረታቸው ወድሟል፣ ቀሪዎቹ ሕይወታቸውን ለማትረፍ በሽሽት ላይ ናቸው።
አከባቢውን ወደ ኦሮሚያ ክልል ለማካለል ያለመ ነው በተባለው በዚህ ጥቃት በመከላከያ ሠራዊቱ ፈቃድ ከጥምር ጦሩ ጋር ተሰልፎ ሀብት ንብረት እየዘረፈ በተሽከርካሪ ጭኖ የሚወስድ ቡድን መኖሩንና ከቀንድ ከብት ጀምሮ የቤት ጣራና ግርግዳ ጭምር እየነቀለ ዘርፎ የሊሙ ወረዳ ዋና ማዕከል ወደሆነችው ገሊላ ከተማ እየወሰደ መሆኑን ነው የመረብ ሚዲያ ምንጮች የገለፁት።
የብልፅግናው መከላከያ ሠራዊት ከኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች ጋር በመቀናጀት ምንም አይነት መሣሪያ ባልታጠቁ ንፁኋኖች ላይ ነው በሞርታርና በዙ23 ጭምር የታገዘ ጥቃት የከፈተው ያሉት ምንጮቻችን፡ ጥቃቱ ተባብሶ መቀጠሉንና የሟቾችን አስከሬን መቅበር አለመቻሉን ገልፀዋል።
የጄኔራሎችን ዘመቻ ድባቅ የመታው የሉማሜ ከተማ ጀብድ!
ነሐሴ 4/ 2018 ዓ.ም
=================================== ጅባራው ብርሃኑ ጥላሁን የ6ኛ ዕዝ አዛዥ፣ ጄኔራል ሶፊያ በክሪ የ602ኛ ኮር አዛዥ፣ ኮሎኔል አለምሰገድ ተስፋየ የ32ኛ ክ/ጦር አዛዥ በአለፍቱ ቀናት የጎጃምን ታጋይ ወደ ተራ ሽፍትነት ቀይረነዋል የሚል ትልቅ ዘመቻ በጮቄ ተራራ አድርገናል እያሉ ሲያቅራሩ የተመለከተው 34ኛ ክ/ጦር ሉማሜ ከተማን በመቆጣጠር ጀብድ ሰርቷል።
ሉማሜ ከተማን ካርታ ላይ በማስፈር የተጠና እቅድ በማቀድ የተጀመረው ልዩ ኦፕሬሽ የጦር አመራሩ ሰራዊቱን የግዳጅ አፈፃፀሙን በሚገባ እንዲረዳ አድርገዋል። ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በጀግኖች የተመራው 34ኛ ክ/ጦር ሉማሜን በመቆጣጠር የጠላትን ሰራዊት ድባቅ መምታት ጀምረዋል።
የጠላት የሰራዊት አቀማመጥ ቤተ ክርስቲያንን ከለላ ያደረገ ቢሆንም የወገን ኃይል በተጠና መልኩ ሰራዊቱን በማናጠል ደምስሰዋል። የሉማሜ ከተማ ሰላምና ደህንነት ኃላፊ ተመስገን ምስክር በብልፅግና ቢሮ በር ላይ በ34ኛ ክ/ጦር ተደምስሷል።
አቶ ናቃቸው ጫኔ በሉማሜ ከተማ የገቢዮች ጽ/ቤት ግብር ሰብሳቢ ቡድን መሪ የነበረው ህዝብን በከፍተኛ ግብር በማሰቃየት እንዲሰደዱ ያደረገ ዋና የብልፅግና ጨካኝ ሰው በማህበረሰቡ ጥቆማ ተማርኳል።
በሉማሜ ከተማ የመሸገውን የጠላት ኃይል በመደምሰስ የጄኔራሎች ጩኸት ባዶ ያስቀረው 34ኛ ክ/ጦር ከፍተኛ ወታደራዊ ድል አስመዝግቧል ።
በነበረው ውጊያ 4 ፓትሮል፣3 አምቡላንስ የጠላት ኃይል ቁስለኛ ሁኗል ከ25 በላይ ተደምስሷል፤ ክላሾች ተማርከዋል።
ከቀናት በፊት አስደማሚ የኮማንዶ ሰራዊት ያስመረቀው 34ኛ ክ/ጦር በተከታታይ አቅዶ በተዋጋባቸው ውጊያዎች ድል ማስመዝገቡ ቀጥሏል።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
ከወታደራዊ ግዳጆች ጎን ለጎን ህዝባዊ ውይይቶች ቀጥለዋል!!
ነሐሴ 04/2010ዓ.ም
የአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ከቅርብ ጊዜው የአንድነት ምስረታ ማግስት ጀምሮ በስምሪት ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ ከወቅታዊ ወታደራዊ ግዳጆቹ ጎን ለጎን በሁሉም ቀጠናዎች ከሕዝብ ጋር የሚደረጉ ውይይቶችን አጠናክሮ ቀጥሏል።
የዕዙ ሥራ አስፈጻሚ በሁሉም ቀጠናዎች ውይይቶችን እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን፣ለጎንደር አንድነት የተከፈለውን ውድ ዋጋ ለህዝባችንና ለሰራዊታችን ግልጽ ስለማድረግ፣ የሕዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ለማስፋት ያለመ እና በፖለቲካ መር ትጥቅ ትግል ውስጥ የህዝባችንን ሚና ምን መምሰል አለበት በሚሉ አንኳር ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።
በእብናት ወረዳ ወርጋጃ ላይ በተካሄደው መድረክ የዕዙ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ጀኔራል ተሾመ አበባው እና ሌሎች የዕዝና የክፍለ ጦር አመራሮች በተገኙበት ዕዙ አንድነቱን ለማምጣት የደረሰበትን ውጤት ፣ የሰራዊቱንና የህዝባችን ሁለተናዊ ትስስር ፣ ለማይቀረው የአሸናፊነት ጉዞ የአንድነታችን ብስራት የውዴታ ግዴታ መሆኑንና ህዝባችን ባለፉት 3 ዓመታት ላደረገው አይተኬ ድጋፍን በተመለከተ ለተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥቶበታል ።
በተጨማሪም በመድረኩ የወደፊት ወታደራዊና ሕዝባዊ የጋራ አቅጣጫዎች ላይ ጥልቅ ውይይት የተደረገ ሲሆን ፣ በተለይም የአንድነትንና የመተባበርን አስፈላጊነት፣ የተቀናጀ ሕዝባዊ ድጋፍን ማጠናከር እንደሚገባ እንዲሁም ጠንካራ ሕዝባዊ ወገንተኝነት ያለው ጦር በመገንባት ሂደት ዙሪያ ባሉ ዋና ዋና ነጥቦች ላይ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
ፋኖ በአማራ ሕዝብ ታሪክ፣ ባህልና ማኅበራዊ መዋቅር ውስጥ ጥልቅ ቦታ ያለውና ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የኖረ የነጻነትና የራስን የመከላከል ምልክት ነው።
የአማራ ልጅ ሲወለድ አንድ ዲግሪ አለው» የሚባለው በአማራ ማኅበረሰብ ዘንድ ገና ከሕፃንነቱ ጀምሮ የሚኮተኮተውን የመታገል፣ የአገር ፍቅር፣ የጀግንነት እና የራስን ክብር የማስጠበቅ እሴት ያመለክታል። ትምህርት ቤት ሳይገባ ወይም ዘመናዊ ሳይንስ ሳይማር፣ በባህሉና በታሪኩ ውስጥ የነጻነትንና የጀግንነትን ትምህርት አብሮት ይዞ የሚያድግ መሆኑ ው።
ሁሉን አቀፍ ተሳትፎ (ከሌቅ እስከ ደቂቅ) የፋኖነት እሴት የወሰነ የዕድሜ፣ የጾታ ወይም የማኅበራዊ ደረጃ ገደብ የለውም። «ከሌቅ እስከ ደቂቅ» እንደሚለው፣ ሽማግሌው፣ ወጣቱ፣ አባወራው፣ እናቱም ሆነ ሕፃኑ በየፊናቸውና በየአቅማቸው ለማኅበረሰቡ ደህንነትና ለነጻነቱ ጥበቃ የየራሳቸውን አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት ባህላዊ መዋቅር አለው።
ትውልድ ተሻጋሪነት ፋኖነት ለአንድ ወቅት ወይም ለአንድ ዘመን ብቻ ተከስቶ የሚያልፍ ሳይሆን፣ ትውልድ ከአባቶቹ ተቀብሎ ለቀጣዩ የሚያስተላልፈው ዘላቂ የማንነትና የባህል አካል ነው። ታሪክን፣ ባህልን፣ ተረትንና ጀግንነትን የማስታወስ ሂደት እንደመሆኑ መጠን ከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፋል።
የመደጋገፍና የማኅበራዊ ቁርኝት ምሳሌ ፋኖ በጦርነትና በችግር ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ በማኅበራዊ ህይወት ውስጥም ለፍትሕ፣ ለእውነት እና ለመደጋገፍ የሚቆም ማኅበረሰባዊ ምሰሶ እንደሆነ ይቆጠራል። #Dave #Amhara
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት የ«ኮሉ ብርጌድ» ደጀን አርበኞች ጦር እየተደራጀ ይገኛል!!
ነሐሴ 04/2018 ዓ.ም
በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ ምህዳር ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚይዘው የሸዋ ምድር፣ የትግሉን ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሚዛን መልክ የሚቀይር አዲስ የሃይል አደረጃጀት እየተደራጀ ይገኛል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በሚዳና ሬማ ክላስተር፣ በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ በአፄ ዓምደ ጽዮን ኮር አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በሚቀሳቀስበት ቀጠና «ኮሉ ብርጌድ» የተሰኘ ግዙፍ የአርበኞች ጦር ሰራዊት በይፋ መመስረቱ ታውቋል።
ከውስጣዊ ፈተና ወደ ወታደራዊ የበላይነት የተሸጋገረው ማሕበረሰብ በፖለቲካ ውስብስብ ጉዳዮች እየተፈተነ የህልውና አደጋ ይታይበት የነበረና ለጠላት ሃይሎች መፈንጫ ሆኖ የቆየ ስትራቴጂካዊ ቀጠና እንደሆነ ይታወቃል። ሆኖም የትግሉን ሚዛን ማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን የተረዱት የቀጠናው ቁርጠኛ ታጋዮች፣ በጥቂት ቀናት ውስጥ የተካሄደውን የተናበበ የመልሶ ማደራጀት ስራ ተከትሎ ከመደበኛው የፋኖ ሰራዊት ውጭ ሁለት ግዙፍ የአርበኞች ጦር ብርጌድ «ካራምሽግ» እና «ኮሉ» ብርጌዶችን ማደራጀት ተችሏል።
ከፍተኛ የአሳምነው ዕዝ እና የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አመራሮች፣ የየቀበሌ አስተዳደሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በተካሄደው የዚሁ ምስረታ ስነ-ስርዓት ላይ፣ ለሰራዊቱ ሰፊ የፖለቲካና የወታደራዊ ስትራቴጂ/ግንባታ ትምህርቶች ተሰጥተዋል።
የብርጌዱን አወቃቀር በተጠናከረ መልኩ ከመደራጀቱም በላይ፣ አመራሮችና አባላት ህዝባቸውንና ቀጠናቸውን በፍፁም ታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝብ ፊት ቃለ-መሃላ ፈጽመዋል። አደረጃጀቱም የወታደራዊ ደጀንነቱን በቁርጠኝነት በማገዝ በአገዛዙ ሃይሎች ላይ ለሚሰነዘረው የማጥቃት ስምሪት ይበልጥ የተቀናጀ እንደሚያደርገው በመድረኩ የተገኙት የዕዝ አመራሮቹ ገልፀዋል ሲል ኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በዚገም ወረዳ ሰፍሮ ማሕበረሰቡን ሲዘርፍና ሲያሳድድ በነበረው የሚኒሻ ኃይል ላይ በተወሰደ ከባድ የቆረጣ እርምጃ ከ20 በላይ የሚኒሻ አባላት ሲገደሉ 12 ክላሽንኮፍ መሣሪያ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውሏል።
የፋኖ የቆረጣ ታክቲክ ከማጥቃት ፍጥነት ጋር ተዳምሮ የጠላትን ጦር ባሽመደመደበት በዚህ ተጋድሎ፡ በዚገም ወረዳ ዚገም ፊለም፣ ጉሀ፣ አሀቲ፣ ኮሸይ፣ ዳዳን ቲትም የተባሉ አከባቢዎች ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
በሰሜን ወሎ ዞን ዳዉንት ወረዳ ታልቅ ህዝባዊ መድረክ ተካሂደ!!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ በስሩ ከሚያስተዳድራቸዉ ወረዳዎች መካከል አንዱ የሆነዉ በሰሜን ወሎ ዞን ዉስጥ ዳዉንት ወረዳ አንዱ ሲሆን በዚህም በዛሬዉ ዕለት ማለትም በቀን 03/12/2018
ዓ.ም የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ታላቅ ህዝባዊ መድረክ ተካሂዷል።
በዚህ ህዝባዊ መድረክም የአማራ ህዝብ የህልዉና ትግል መነሻ፣ አሁናዊ ትግሉ ያለበትን ደረጃ፣ ሰለ አጋርነት እና ትብብር እና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ በሚኒልክ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ተሰጥቷል።
በዚህ ህዝባዊ ዉይይት በማህበረሰቡ የተለያዩ ጥያቄዎችን እና ሃሳቦችን የተነሱ ሲሆን ለተነሱት ጥያቄወች እና ሃሳቦች የሚመለከታቸዉ አካላት በዘርፉ መልስ ሰጥተዋል:: ማህበረሰቡም ለጠየቋቸዉ ጥያቄወች ፈጣንና ግልጽ ምላሽ በመሰጠታቸዉ እንደተደሰቱ ገልፀዉ "ካሁን በኋላ ከፋኖ ጋር በጋራ ሁነን ይህን የብልፅግና ስርዓት ለመጣል" ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በዚህ ህዝባዊ መድረክ የምኒልክ ዕዝ ም/ትል ሰብሳቢ አርበኛ ረዳ ዉበቱ(ቀኝ አዝማች)፣ የምኒልክ ዕዝ ፖለቲካ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ሞገስ አባራዉ፣ የምኒልክ ዕዝ ዘመቻ መምሪያ አርበኛ በለጠ ሸጋዉ(ድሮን)፣ የምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ አርበኛ ብርሃን አርጋ እና የምኒልክ ዕዝ 16ኛ ኮር አመራር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ተገኝተዋል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!
ነሀሴ :- 03/ 2018 ዓ/ም
አቶ ናቃቸው ጫኔ የሉማሜ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት የግብር ሰብሳቢ ቡድን መሪ በሉማሜ ከተማ በተደረገው ኦፕሬሽን በ34ኛ ክ/ጦር ተማርኳል። ናቃቸው ጫኔ የሉማሜ ከተማ ነዋሪዎችን በግብር ጫና ያሰደደ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ በማህበረሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል።
እኔ የሚገርመኝ እኔን ለማሸማቀቅ የሚትሮጡበት መንገድ ያስገርመኛል አርፋችሁ ተቀመጡ እኔ የአማራ ልጅ ፋኖ ነኝ ዋ ዝምታ መልስ እንደሆነ ይግባችሁ ምድር ድኩማን ተውኝ እንደ አማራ በሆዳም አማራዎችና በብልፅግና የተገፋሁ ልጅ ነኝ ተውኝ ተውኝ ተውኝ
+5
የአማራ_ጭፍጨፋ_በጉራጌ_ዞን‼️
በምስል የሚታዩት የአማራ ተወላጅ
1. ተመስገን ጌታቸው
2. ይታገሱ አሰግደው
3. ግዛው ግርማዬ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ላይ ፋኖ ናቹህ በማለት ከተሳፈሩበት መኪና ላይ በማስወረድ ልዩ ስሙ #አገና ከተማ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቀን 24/11/2018 ዓ.ም በግፍ እጃቸውን በገመድ ወደኋላ አስረው ከረሸኗቸው በኋላ ወደ ትውልድ ቀያቸው #ናቻ ቀሊት ቀበሌ አስከሬናቸውን በመጣል ማንም ሰው አንስቶ እንዳይቀብር በማለት 3 ቀን ሙሉ ቆይቶ አስከሬናቸው በጅብ,በአሞራ እና በውሻ እንዲበላ ተደርጓል ፣ይህ አፀያፊ ተግባር የተፈፀመው የአብይ አህመድ ስልጣን አስጠባቂ በሆነ የመከላከያ ሰራዊትና በቀጠናው ባለው ፅንፈኛ አካሎች ነው እባካቹህ ድምፅ ሁኑን በደላችንን አለም ሁሉ ይስማው ሲሉ የአይን እማኞች ገልፀዋል።
በአሁኑ ሰዓት የቢዛሞ ወለጋ አማራን በየከተማው እና በየሰፈሩ ህፃን ፣ ነፍሰ ጡር ፣ አዛውንት ፣ ወጣት ሳይቀራቸው ህዝቡን በሙሉ እየጨፈጨፉ ያሉ የኦህዴድ ኃይሎች እነዚህ ናቸው።
⚡️ የኦህዴድ መሩ የብልግና ወንበር አስጠባቂ መከላከያ ተብዬ
⚡️ የኦሮሚያ ፖሊስ ተብየ–
⚡️ የክልል 4( ኦሮሚያ) የፀረ ሽምቅ ተዋጊ ተብዬ (Oromia Anti-Guerrilla Police )
⚡️ የሰፈር ሚሊሻ (Local militia )
⚡️ ለኦህዴድ እጁን የሰጠው እና በጃል ሰኚ የሚመራው የOLF-Shene ክፋይ እና
⚡️ ገዳ ኮማንዶ ተብዬ ናቸው ። .....እነዚህ በሙሉ ተሰብሰሰበው የአማራ ንፁሃንን መንገድ በመዝጋት እየጨፈጨፉ ይገኛሉ።
የቢዛሞ አማራ ሆይ ይሄንን ሁሉ ኃይል በማሰማራት ከምድረ ገፅ እያጠፋህ የሚገኘውን አረመኔውን የኦህዴድ ኃይል በብላሽ ከመሞት ጥሎ መሞት ክብር አለው እና ለነፃነትህ ታገል።
ይሄ ኃይል ጀኖሳይድ ፈፃሚ አረመኔ ስብስብ ነውና ጥርስህን ነክሰህ ታገለው።
ሰርተህ እንዳትበላ ፣ በላብህ እንዳትኖር ሀብትህን እያወደሙት ፣ ህይወትህን እየነጠቁህ ነውና በእልህ ታገላቸው‼️
