uk
Feedback
Minber News - ሚንበር ኸበር

Minber News - ሚንበር ኸበር

Відкрити в Telegram
8 441
Підписники
+424 години
+377 днів
+6530 день
Архів дописів
በኢትዮጵያ የወሊድ ምጣኔ መቀነሱን የሚያሳይ አዲስ ሪፖርት ይፋ ተደረገ - በአዲስ አበባ ከመላው ኢትዮጵያ ዝቅተኛ የተባለው 2.3 ልጅ አማካይ የወሊድ ምጣኔ ተመዝግቧል ዕለተ ማክሰኞ ሐምሌ 7 – 2018 ሙሐረም 29 – 1448 የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከነሐሴ 2016 እስከ ሚያዝያ 2017 ባለው ጊዜ ውስጥ የሰበሰበውን መረጃ መሠረት በማድረግ 5ኛውን የኢትዮጵያ የሕዝብ እና ጤና ቅኝት ማጠቃለያ ሪፖርት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ በኢትዮጵያ የወሊድ ምጣኔ መቀነሱን ያሳያል፡፡ በጥናቱ ላይ ከ21 ሺሕ በላይ ሴቶች የተሳተፉ ሲሆን፣ የሀገሪቱ ወቅታዊ የሕዝብ ስብጥር፣ የጤና እና የኑሮ ሁኔታ የሚያሳይ ሰፊ መረጃ ተካቶበታል። የአገልግሎቱ ሪፖርት እንደሚያመለክተው፣ በኢትዮጵያ የአንዲት ሴት አማካይ የወሊድ ምጣኔ በ1992 ከነበረበት 5.5 ልጆች በአሁኑ ወቅት ወደ 4 ልጆች ዝቅ ብሏል። በክልሎች መካከል የወሊድ ምጣኔው ልዩነት የተመመዘገበበት ሲሆን፣ ከፍተኛው የወሊድ ምጣኔ በሱማሌ ክልል (6.5 ልጆች) ተመዝግቧል፡፡ ዝቅተኛው ደግሞ በአዲስ አበባ (2.3 ልጆች) ሆኖ ተመዝግቧል። በሪፖርቱ መሠረት ይህ የወሊድ ምጣኔ ከፍተኛ ትምህርት ደረጃ ያላቸው ሴቶች ዝቅተኛ የትምህርት ደረጃ ካላቸው ሴቶች ጋር ሲነፃፀሩ የመውለድ እድላቸው በአጠቃላይ ይቀንሳል። እንዲሁም የቤተሰብ ሀብት እየጨመረ ሲሄድ የወሊድ ምጣኔው ሲቀንስ፣ በተቃራኒው በድኻ ቤተሰቦች ውስጥ ያሉ ሴቶች ብዙ ልጆችን ይወልዳሉ፡፡ ከሕፃናት ሞት ጋር በተገናኘም ከ1992 ጀምሮ ከ1 ሺህ በሕይወት የተወለዱ ሕፃናት ከ97 ሞት ወደ 39 ቀንሷል፡፡ ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት ሞት በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ከ166 ወደ 51 ሞት ቀንሷል። በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ቤተሰቦች በአማካይ 4.4 አባላት ሲኖራቸው፣ 28 በመቶ የሚሆኑትን የኢትዮጵያ ቤተሰቦችን ሴቶች ያስተዳድራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የቤተሰብ አባላት 42 በመቶ የሚሆኑት ከ15 ዓመት በታች ናቸው። ሌላው ሪፖርቱ ያካተተው ጉዳይ የመሠረተ ልማት እና የቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ነው፡፡ በዚህ ረገድ 57 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ መሠረታዊ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ያገኛል። ይሁን እንጂ 71 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ በመኖሪያ ግቢው ውስጥ የውሃ መስመር የለውም። መሠረታዊ የሽንት ቤት አገልግሎት የሚያገኘው ሕዝብ 31 በመቶ ብቻ እንደሆነ ያሳየው ሪፖርቱ፤ 27 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ አሁንም በሜዳ ላይ የመጸዳዳት ልማድ አለው ብሏል። የኃይል አቅርቦትን በተመለከተ 64 በመቶ የሚሆነው የሀገሪቱ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የሚያገኝ ቢሆንም ለምግብ ማብሰያነት ዘመናዊና ንፁህ የኃይል አማራጮችን ወይም የኤሌክትሪክ ምድጃ፣ ጋዝ የመሰሉትን የሚጠቀመው 5 በመቶ ብቻ ነው። በከተማ የኤሌክትሪክ ምጣድ አጠቃቀም 31 በመቶ ሲሆን በገጠር 2 በመቶ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ መኪና፣ የጭነት መኪና ወይም ሞተር ሳይክል/ስኩተር ያላቸው አራት በመቶ የሚሆኑ ቤተሰቦች እንደሆኑም ሪፖርቱ አሳይቷል። በሌላ በኩል የዓለም የሕዝብ ብዛት 8.2 ቢሊዮን በላይ መሻገሩን የዓለም ባንክ ባወጣው አዲስ ሪፖርት አስታውቋል። የዩናይትድ ኔሽን ፖፑሌሽን ፈንድ ሪፖርት እንደሚያሳየው ደግሞ፣ የኢትዮጵያ የሕዝብ ብዛት 135 ሚሊዮን በማለፍ ከዓለም 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡ በሕዝብ ብዛት ከዓለም ቀዳሚውን ሥፍራ የያዘችው ሕንድ ስትሆን፤ ከ1. 41 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ብዛት ያላትን ቻይና አስከትላለች። (ሚንበር ቲቪ)

በኢትዮጵያ የወሊድ ምጣኔ መቀነሱን የሚያሳይ አዲስ ሪፖርት ይፋ ተደረገ በድረ ገጽ ተጨማሪ ያግኙ፦ https://minbertv.com/?p=11656
በኢትዮጵያ የወሊድ ምጣኔ መቀነሱን የሚያሳይ አዲስ ሪፖርት ይፋ ተደረገ በድረ ገጽ ተጨማሪ ያግኙ፦ https://minbertv.com/?p=11656

ለደራሲ ሙሐመድ ዓሊ ቡርሃን የዕውቅናና የምሥጋና ፕሮግራም ተካሄደ የኢስላምን ታሪክ ጨምሮ ከ35 በላይ የፍልስፍና ማኅበራዊ ይዘት ያላቸውን መጻሕፍት ለአንባቢያን በማቅረብ ለሚታወቀው ደራሲ ሙሐመድ ዓ
+9
ለደራሲ ሙሐመድ ዓሊ ቡርሃን የዕውቅናና የምሥጋና ፕሮግራም ተካሄደ የኢስላምን ታሪክ ጨምሮ ከ35 በላይ የፍልስፍና ማኅበራዊ ይዘት ያላቸውን መጻሕፍት ለአንባቢያን በማቅረብ ለሚታወቀው ደራሲ ሙሐመድ ዓሊ (ቡርሃን አዲስ) የምሥጋናና ዕውቅና ሥነ ሥርዐት የተካሄደው በአዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው ማርዮት ሆቴል ነው። በሥነ ሥሬዐቱ ላይ የደራሲው ወዳጆችና የሥራው አድናቂዎች ታዳሚ ሆነዋል። ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በኬሚካል ኢንጂነሪንግ ዘርፍ የተመረቀው ደራሲ ሙሐመድ ዓሊ ቡርሃን፤ ከልጅነት አንስቶ ዝንባሌው ወደነበረው ሥነ ጽሑፍ በመሳብ ለአንባቢያን ካደረሳቸው መጻሕፍት መካከል  እስልምና በ20ኛው ክፍለ ዘመን፣ እስልምና አጭር መግቢያ እና ያልታዩ እውነቶች፣ የፍልስፍና ጥበባትና እስልምና፣ ኢማም ገዛሊ፣ ዑመር አል ፋሩቅ፣ ሸይኽ ዓብዱልቃድር ጂላኒ ተጠቃሽ ናቸው። "የማንነት ክንፎች"፣ "የመሲኆች እድር"፣ "የዘር ካርድ"፣ ነቢይ እና ፈላስፋ እና "መሆንን መድረስ" የተሰኙት መጻሕፍትም ይጠቀሳሉ። ከዚህም ባሻገር በእስልምና ዙሪያ ሰፋ ያሉ ታሪካዊ ጉዳዮችን በቴሌቭዥን አሰናድቶ በማቅረብ ይታወቃል። በዛሬው ዕለት በተካሄደው ፕሮግራም ላይ የተገኙ ዕድምተኞች እና የቅርብ ወዳጆቹ ለደራሲው ያላቸውን አክብሮት ሥጦታ በማበርከት ገልጸውለታል። በመርሐ ግብሩ ላይ የሙሐመድ ዓሊ ሥራዎች ቀርበው በጨረታ ተሸጠዋል። (ሚንበር ቲቪ)

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብን አነሳ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብን ማንሳቱን አስታውቋል። ብሔራዊ ባንኩ ይህን ያስታወቀው ዛሬ ሐምሌ 6/2018 ያካሄደውን ሰባተኛ ስብሰባ ተከትሎ አምስት ምክረ ሃሳቦችን የያዘ መግለጫ ባወጣበት ወቅት ነው። ማዕከላዊ ባንኩ ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብን (credit cap) ቀጥተኛ ያልሆኑ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎችን በመጠቀም በወለድ ምጣኔ ላይ ተመስርቶ ወደሚሰራ የገንዘብ ፖሊሲ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ እስኪሸጋገር ድረስ በጊዜያዊነት ሲጠቀምበት መቆየቱን ገልጿል። ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት የብድር ገደቡ የታቀደለትን ዓላማ ማሳካቱን በመግለጽ ኮሚቴው ገደቡ ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ ተወስኗል ብሏል። ሆኖም የብድር ገደቡ መነሳት የብሔራዊ ባንኩ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ አቋም ለውጥ ሳይሆን የወለድ ተመንን መሠረት ያደረገው የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ወደ ተሳካ ሽግግር በመድረሱና ቀጥተኛ ያልሆኑ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎች ውጤታማ እየሆኑ በመምጣታቸው እንደሆነ አመልክቷል። አክሎም  የብድር ገደብ በመነሳቱ ተመጣጣኝ  ጥብቅ የፖሊሲ መውሰድ እንደሚያስፈልግ በማስገንዘብ የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔን በ10 መቶኛ ነጥብ (ከ15 በመቶ ወደ 16 በመቶ) ለማሳደግ እና የ +3 የመቶኛ ነጥብ ክልል (band) ሳይለወጥ እንዲቆይ መወሰኑን አስታውቋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የብድር ዕድገት መስፋፋት በዋጋ ግሽበት ላይ አሉታዊ ጫና የሚያሳድር ከሆነ ብሄራዊ ባንኩ ግምገማ በማካሄድ የእያንዳንዱ ባንክ የብድርና የተቀማጭ ሂሳብ ጥመርታ ላይ በመመርኮዝ የተለየ የመጠባበቂያ ተቀማጭ እንዲተገብር እንደሚያደርግ ገልጿል። ሌላኛው የወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን ለማሻሻል፣ የገበያ ላይ መተማመን ለመገንባት እና የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማሳለጥ፣ ላኪዎች ከሚያገኙት የውጭ ምንዛሪ ግኝት ላይ ለባንኮች እንዲሸጡ የሚጠየቀው 50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ መደረጉ ነው። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ አቋሙን ለማስቀጠል በፖሊሲ ማዕቀፉ ውስጥ ያሉትን ሁሉንም ቀጥተኛ ያልሆኑ የገንዘብ ፖሊሲ መሣሪያዎችን መጠቀሙን እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብን አነሳ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የብድር ዕድገት ገደብን አነሳ

በሳዑዲ የሕግ ሒደትና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው ከ1 ሺህ 970 በላይ ኢትዮጵያውያን የምህረት ተጠቃሚ ሆነዋል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት፤ በ
በሳዑዲ የሕግ ሒደትና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው ከ1 ሺህ 970 በላይ ኢትዮጵያውያን የምህረት ተጠቃሚ ሆነዋል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽሕፈት ቤት፤ በሳዑዲ ዐረቢያ የሕግ ሒደትና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው 1 ሺህ 971 ኢትዮጵያውያን የምህረት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቋል። ጽሕፈት ቤቱ ይህን ያስታወቀው ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 6/2018 ባወጣው መግለጫ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት በተለይም ደግሞ የሕግ ሒደትና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸውን ዜጎች በተመለከተ ከሳዑዲ ዓረቢያ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሠራ እንደሚገኝም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሳዑዲ ዐረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር ተከታታይ ውይይቶች ማድረጉን አስታውሷል። አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች ሰብዓዊ ምሕረት እንዲደረግላቸው እና ተገቢው መፍትሔ እንዲፈለግላቸው ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር ያለውን ውይይት አጠናክሮ መቀጠሉንም አስታውቋል። ይህን ተከትሎም እስከ አሁን ድረስ የንጉሣዊ ምሕረት ተጠቃሚ መሆን የቻሉትን ኢትዮጵያውያን ዜጎችንም ወደ ሀገራቸው የማጓጓዝ ስራ መጀመሩንም አስታውቋል፡፡ ከሳዑዲ ዐረቢያ ከዚህ ቀደም የመጀመርያዎቹ 320 ተመላሾች ኢትዮጵያ መግባታቸው ይታወቃል። (ሚንበር ቲቪ)

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በኳታር አሚር ሸይኽ ሐማድ ቢን ኸሊፋ ኅልፈት ተከታዩን የሐዘን መግለጫ ሰጥተዋል 👇 ​በእኔ፣ በኢትዮጵያ እስልምና
+1
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በኳታር አሚር ሸይኽ ሐማድ ቢን ኸሊፋ ኅልፈት ተከታዩን የሐዘን መግለጫ ሰጥተዋል 👇 ​በእኔ፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በመላው የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም ሥም፣ ለተከበሩት የሀገረ ኳታር አሚር ሸይኽ ታሚም ቢን ሐማድ አል ሳኒ፣ ለኳታር መንግሥት እና ለኳታር ሕዝብ፣ በክቡር አሚር ሸይኽ ሐማድ ቢን ኸሊፋ አል ሳኒ ኅልፈተ ሕይወት የተሰማኝን ልባዊ እና ጥልቅ ሐዘን እገልጻለሁ። ​ክቡር አሚር ሸይኽ ሐማድ ቢን ኸሊፋ አስሳኒ ለኳታር ብቻ ሳይሆን ለሀገራት ሁሉ ሰላም በተለይም በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚነሱ ግጭቶችን ለመፍታት ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ አርዓያ መሪ ነበሩ። ​የኢትዮጵያ ሙስሊሞችና መላው ሕዝብ ለሟቹ አሚር ታላቅ ክብርና መልካም ትውስታ ያለው ሲሆን ክቡር አሚር የኢትዮጵያ እና የኳታር ታሪካዊ ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከማድረግ አንጻር ከፍተኛ ሚና ነበራቸው። በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ያለው ሃይማኖታዊና ሰብዓዊ ትስስር ሁለንተናዊ በሆነ መንገድ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ደማቅ አሻራ አሳርፈዋል። ​ለክቡር አሚር ሸይኽ ሀማድ ቢን ኸሊፋ አል ሳኒ ምሕረቱንና እዝነቱን እንዲለግሣቸውና ማረፊያቸውን በጀነት እንዲያደርግላቸው አላህን እንማጸነዋለን። ለተከበረው የሀገረ ኳታር መንግስትና ህዝብ እንዲሁም ለወዳጆቻቸው ሁሉ አላህ መጽናናትንና ሰላምን እንዲሰጥ ዱዓችን ነው።

ኸበር፡ የዘመናዊቷ ኳታር መሐንዲስ በመባል የሚታወቁት አሚር ሸይኽ ሐማድ ቢን ኸሊፋ አስሳኒ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሸይኽ ሐማድ ከሌሎች ጉዳዮች በተጓዳኝ የኳታር ንጉሣዊ ቤተ መንግሥት አዲስ
ኸበር፡ የዘመናዊቷ ኳታር መሐንዲስ በመባል የሚታወቁት አሚር ሸይኽ ሐማድ ቢን  ኸሊፋ አስሳኒ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ሸይኽ ሐማድ ከሌሎች ጉዳዮች በተጓዳኝ የኳታር ንጉሣዊ ቤተ መንግሥት አዲስ ጎሕ ሲል የጠራውንና በዓረቡም ሆነ በዓለም አቀፍ ሚዲያ አዲስ ምዕራፍ የከፈተውን አልጀዚ ኔትወርክን በመመሥረት ይታወሳሉ። (ሚንበር ቲቪ)

ለዑምራ ቁጠባ አገልግሎት ይሰጣል የተባለው ኒያ ዕቁብ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ተደረገ ኒያ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ ከአይቤክስ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ኒያ ዕቁብ የተሰኘ አዲስ የሞባይል መተግበሪያ በ
+9
ለዑምራ ቁጠባ አገልግሎት ይሰጣል የተባለው ኒያ ዕቁብ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ተደረገ ኒያ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ ከአይቤክስ ቴክኖሎጂ ጋር በመተባበር ኒያ ዕቁብ የተሰኘ አዲስ የሞባይል መተግበሪያ በዛሬው እለት ይፋ አድርገዋል። መተግበሪያ ዑምራ የማድረግ ሕልም ላላቸው ውጥን ለማሳካት በዲጂታል አማራጭ የቀረበ መሆኑ ተገልጿል። የገንዘብ ቁጠባ አሠራሩ የተዘረጋው ከአዲስ ባንክ ጋር የዲጂታል ባንኪንግ ትስስር በመፍጠር ነው። በአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ የተባሉት አነስተኛ ንግድ ላይ የተሠማሩ፣ ቋሚ ደመወዝተኞችና ሌሎችም ምዕመናን ናቸው። በመድረኩ ላይ የተናገሩት የኒያ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂስ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተውፊቅ ራሕመቶ፤ መተግበሪያ የቀረበው ባህላዊ የዕቁብ አሰባሰብ ሥርዓትን ከዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ጋር በማስተሳሰር የዑምራ ኒያ ያላቸው ሰዎች ከሕልማቸው ጋር እንዲገናኙ በማሰብ ነው። ሸሪዓዊ መርሆዎችን በመከተል መተግበሪያው ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የፋይናንስ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑንም አክለዋል። መተግበሪያን ያበለፀገው የአይቤክስ ቴክኖሎጂስ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢዘዲን ካሚል፤ መተግበሪያው በአስተማማኝ መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን በመግለጽ የደኅንነት ማረጋገጫ ሰጥተዋል። የአዲስ ባንክ ሷሂብ ከወለድ ነፃ አገልግሎት ዳይሬክተር አጂቦ ፈኽሩ በበኩላቸው፤ ከባንኩ ጋር በቀርደል ሐሰን አሠራር በኒያ ዕቁብ አማካኝነት የሚሰበሰበው የዑምራ ኒያ ገንዘብ የሚቀመጠው በዝግ አካውንት መሆኑን ጠቁመዋል። (ሚንበር ቲቪ)

#ሚንበር_ቲቪ_ከሥፍራው፦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሐላል ቢዝነስ ፎረም እየተካሄደ ነው በኢትዮጵያ በርካታ ቁጥር ያላቸው አምራቾች፣ የጅምላና የችርቻሮ ነጋዴዎች፣ አስመጪዎች እንዲሁም ላኪዎች እንዲሁም
+9
#ሚንበር_ቲቪ_ከሥፍራው፦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሐላል ቢዝነስ ፎረም እየተካሄደ ነው በኢትዮጵያ በርካታ ቁጥር ያላቸው አምራቾች፣ የጅምላና የችርቻሮ ነጋዴዎች፣ አስመጪዎች እንዲሁም ላኪዎች እንዲሁም የፖሊሲ ተዋናዮች የተሳተፉበት የሐላል ቢዝነስ ፎረም ዛሬ ቅዳሜ 4/2018 በይፋ ተጀምሯል። ሚንበር ቲቪ የፎረሙ የሚዲያ አጋር ሆኖ እየሠራ ይገኛል። በፎረሙ መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ፣ የፋይናንስና የኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚመሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ጥላሁን እስማኤል፣ የኤፍ ኤስ ዲ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሒክመት ዓብደላ፣ በኬሚካልና በኮንስትራክሽን ግብአቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ዋና ስራ አስፈፃሚና ተመራማሪ አቶ ሀብታሙ አራጌ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የፖርትፎሊዮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አስማ ረዲ ይገኙበታል። በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሐላል ቢዝነስ ፎረም የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሙሂዲን ያሲን፤ ፎረሙ ለንግዱ ማህበረሰብ የስልጠናና የማማከር አገልግሎቶችን በመስጠት አቅምን ማሳደግ ላይ በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል። ይህ መድረክ በኢትዮጵያ እያደገ የመጣውን የሀላል ቢዝነስና ኢንቨስትመንት ሥነ-ምህዳር ይበልጥ ለማጠናከርና በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትን ትስስር ለማጎልበት ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ይጠበቃል። እስከ አመሻሽ የሚቆየው ፎረም የሚዲያ አጋር ሚንበር ቲቪ ነው። (ሚንበር ቲቪ)

በታላቁ አንዋር መስጂድ ውስጥ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ገደማ በአገልግሎት የቆዩት ጋሽ ዓብዶሽ ፈቂህ ወደ አኺራ ተሻገሩ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ታላቁ አንዋር መስጂድ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ገደማ በአ
በታላቁ አንዋር መስጂድ ውስጥ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ገደማ በአገልግሎት የቆዩት ጋሽ ዓብዶሽ ፈቂህ ወደ አኺራ ተሻገሩ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ታላቁ አንዋር መስጂድ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ገደማ በአገለግሎት የቆዩት ጋሽ ዓብዶሽ ፈቂህ ዛሬ ጁምዓ ሐምሌ 3/2018 ወደ አኺራ መሻገራቸው ታውቋል፡፡ ጋሽ ዓብዶሽ ከ1970 ጀምሮ ኅልፈታቸው እስከተሰማበት ቀን ድረስ፣ ለ48 ዓመታት ያህል ሙሉ ሙሉ እድሜያቸውን በአንዋር መስጂድ ውስጥ በማገልገል አሳልፈዋል። እኒህ አባት በየትኛውም ሰዓት መስጅዱ ግቢ ውስጥ የማይታጡ እንደነበሩ የሚያውቋቸው ይናገራሉ፡፡ በመስጂዱ ውስጥ ከበርካታ ሥራዎች ባለፈ በተለይም ሴቶችን በመድረሳ ውስጥ በቅርበት በመከታተልና ቁጥጥር በማድረግ ረገድ ትልቅ አደራ ተወጥተዋል፡፡ በአንዋር መስጂድ ቅጽር ውስጥ ገንዘብ በማሰባሰብ ለአቅመ ደካማ ሴቶችና እሕቶች በመስጠት የብዙዎችን እንባ በማበስ ችግራቸው እንዲቃለል በማድረግም ይታወሳሉ፡፡ ሚንበር ቲቪ ጋበሽ ዓብዶሽ ፈቂህ ኅልፈት የተሰማውን ሐዘን እየገለጸ ለመስጂዱ ማኅበረሰብ አላህ (ሱ.ወ) መጽናናትን እንዲለግሥ ይመኛል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

ኸበር ደርሷል! https://youtu.be/90WIO7577ug?si=CI

ካንሠር በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀን 26 ሺሕ ሰዎችን ይገድላል - የዓለም ጤና ድርጅት በድረ ገጽ ያንብቡ፡ https://minbertv.com/?p=11654
ካንሠር በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀን 26 ሺሕ ሰዎችን ይገድላል - የዓለም ጤና ድርጅት በድረ ገጽ ያንብቡ፡ https://minbertv.com/?p=11654

ለአሸናፊዎች ሦስት ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ሽልማት የተመደበለት 29ኛው ዓለም አቀፍ የቅዱስ ቁርኣን ሽልማት ውድድር በይፋ ተከፈተ ዕለተ ሐሙስ ሐምሌ 2 – 2018 ሙሐረም 24 – 1448 የተባበሩት ዓረብ ኢሜሬትስ ምክትል ፕሬዝዳንት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የዱባይ ገዥ ሸይኽ ሙሐመድ ቢን ረሺድ አል መኽቱም፤ የ29ኛውን የዱባይ ዓለም አቀፍ የቅዱስ ቁርኣን ሽልማት ውድድር በይፋ አስጀምረዋል፡፡ ሸይኽ ሙሐመድ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ “በዓለም ላይ ያሉ እጅግ ማራኪ የቁርኣን ድምጾችን በምናደርገው ሐሰሳ ለማክበር፣ ከበስተጀርባቸው ለመስገድ እና በሚቀጥለው ረመዳን እውቅና ለመስጠት ዝግጅት ላይ ነን” ብለዋል። የዘንድሮው ውድድር፡ “በዓለም ላይ እጅግ ውቡን የቁርኣን ቲላዋ ሐሰሳ” በሚል የተዘጋጀ ነው፡፡ ገልፍ ኒውስ እንደዘገበው፤ ሰኔ 30 የተጀመረው ውድድር በሦስት ዙር የሚካሄድ ነው። የውድድሩ መዝጊያ ሥነ ሥርዓት በረመዳን ወር የሚካሄድ ሲሆን፤ ለአሸናፊዎች ከሦስት ሚሊዮን ዶላር በላይ የገንዘብ ሽልማት ተመድቧል፡፡ ከተወዳዳሪዎች ወደ ሁለተኛው ዙር የሚያልፉ ብቁ የሆኑና የተመረጡ ቡድኖች በኢምሬትስ በሚገኙ ዋና ዋና መስጂዶች የተራዊህ ሰላት እንዲመሩ ወደ ዱባይ ይጋበዛሉ። የዘንድሮው 29ኛው ዓለም አቀፍ ውድድር በሶስት ዘርፍ የተዘጋጀ ሲሆን የመጀመርያው ምድብ ውስጥ የተካተቱት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በላይ የሆኑ ወንዶች ናቸው። ሁለተኛው የውድድር ዘርፍ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ወንዶችና ሴቶች ምድብ ሲሆን፤ ሦስተኛው የዓለም አቀፍ ቁርኣናዊ ስብዕና ተብሎ የተሠየመ ነው፡፡ በሦስቱም ዘርፍ አንደኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች ለእያንዳንዳቸው የ1 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ተዘጋጅቷል ተብሏል። ዘንድሮ ለ29ኛ ጊዜ የሚካሄደው ይህ የቁርኣን ሒፍዝ እና ንባብ ውድድር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ከ126 ሀገሮች ከ7 ሺሕ 820 በላይ ተሳታፊዎችን አስተናግዷል። (ሚንበር ቲቪ)

ለአሸናፊዎች ሦስት ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ሽልማት የተመደበለት 29ኛው ዓለም አቀፍ የቅዱስ ቁርኣን ሽልማት ውድድር በይፋ ተከፈተ
ለአሸናፊዎች ሦስት ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ሽልማት የተመደበለት 29ኛው ዓለም አቀፍ የቅዱስ ቁርኣን ሽልማት ውድድር በይፋ ተከፈተ

ኸበር ደርሷል! 🔗 https://youtu.be/8jRZL8sm4Jo 🔗

ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ የ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ትርፍ ማስመዝገቡን አስታወቀ ዕለተ ሰኞ ሐምሌ 1 – 2018 ሙሐረም 23 – 1448 ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ሂጅራ ባንክ፤ በተጠናቀቀው የ2025/2026 በጀት ዓመት በሁሉም የሥራ መስኮች የላቀ ዕድገት ማስመዝገቡን የባንኩ ኃላፊዎች ባቀረቡት ሪፖርት ገልጸዋል፡፡ የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳዊት ቀኖ ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 1/2018 በአዲስ አበባ በተዘጋጀ ሥነ ሥርዐት ላይ እንደተናገሩት፤ ባንኩ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበው የ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ትርፍ ካለፉት አራት ዓመታት ድምር አንጻር የ132 በመቶ ዕድገት ያሳየ ነው። ፕሬዝዳንቱ ይፋ ባደረጉት ሪፖርት መሠረት፣ የባንኩ ዓመታዊ ገቢ የ97 በመቶ ዕድገት በማሳየት 3 ነጥብ 55 ቢሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ አጠቃላይ የሐብት መጠኑ ደግሞ በ115 በመቶ በማደግ 31.45 ቢሊዮን ብር ደርሷል። በተመሳሳይ የደንበኞች ተቀማጭ ገንዘብ በ101 በመቶ አድጎ 24 ቢሊዮን ብር ደርሷል፡፡ ጠቅላላ ካፒታሉም ከሁለት እጥፍ በላይ 202 በመቶ በሆነ ዕድገት 7 ነጥብ 45 ቢሊዮን ብር መድረሱን አቶ ዳዊት ገልጸዋል። በበጀት ዓመቱ 158 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት መቻሉም በበጀት ዓመቱ ከተመዘገቡት ስኬቶች መካከል ጠቅሰዋል፡፡ በተጨማሪም ባንኩ ለደንበኞቹ ያቀረበውን የፋይናንስ መጠን በ133 በመቶ በማሳደግ 16.78 ቢሊዮን ብር በላይ ሲደርስ፤ በበጀት ዓመቱ 41 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አጠቃላይ የቅርንጫፎቹን ቁጥር 170 አድርሷል። ዲጂታል ባንኪንግን በማዘመን ረገድም የደንበኞቹን ቁጥር 2.24 ሚሊዮን ደርሷል፡፡ 3,871 ለሚሆኑ አነስተኛና መካከለኛ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ወገኖች፣ ሴቶችና ወጣቶች ያለ ማስያዣ 1.5 ቢሊየን ብር የኢሙራበሃ ፋይናንሲንግ አቅርቧል። ሂጅራ ባንክ የሸሪዓ መርሆዎችን መሠረት በማድረግ ከአጠቃላይ ትርፉ ላይ ተቋማዊ ዘካ 8 ሚሊየን ብር እና ለወቅፍ 2 ሚሊየን ብር ማውጣቱን ፕሬዝዳንቱ አስታውሰዋል። እንዲሁም ያለምንም ትርፍ በቀርድ አል ሐሰን 341.72 ሚሊየን ብር የፋይናንስ አገልግሎት የሰጠ ሲሆን፣ የገንዘብ እጥረት ለነበረባቸው 35 ምዕመናን የ50 በመቶ ወጪን በብድር በመሸፈን የሐጅ ጉዞ ህልማቸውን እውን ማድረጉን አቶ ዳዊት ቀኖ በማብራሪያቸው ላይ አንስተውታል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ የ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ትርፍ ማስመዝገቡን አስታወቀ
+8
ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ የ1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ትርፍ ማስመዝገቡን አስታወቀ

የመዲናዋ ዓመታዊ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን ተወሰነ በአዲስ አበባ የ2019 የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን ተወስኗል ሲል የአዲስ አበባ የ
የመዲናዋ ዓመታዊ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን ተወሰነ በአዲስ አበባ የ2019 የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11 ነጥብ 5 በመቶ እንዲሆን ተወስኗል ሲል የአዲስ አበባ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል። ይህን ተከትሎም በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት በይፋ መተግበር ይጀምራል ብሏል። ቢሮው ባወጣው መረጃ መሠረት፣ የዋጋ ማስተካከያ ውሳኔው በዘፈቀደ የተወሰነ ሳይሆን በከተማዋ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ከተካሄደ በኋላ የነዋሪውን እውነተኛ የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ የተዘጋጀ ነው። በተጠናቀቀው ሰኔ ወር የመዲናዋ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን ሳይንሳዊና ምክንያታዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የመተመኛ ጥናት ቀርቦ የፓናል ውይይት መካሄዱ ይታወሳል። የከተማ አስተዳደሩ የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት ርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝም አስታውሷል። አሠራሩ አከራዮች ወቅቱንና የኢኮኖሚ ሁኔታውን ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ የሚያረጋግጥ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን፣ ተከራዮችም እንዲሁ ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ በመክፈል ከተደጋጋሚ መፈናቀልና ሥነ ልቡና ስጋት በመዳን የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያደርጋል ሲል ቢሮው አብራርቷል። (ሚንበር ቲቪ)