1 068
Підписники
+224 години
Немає даних7 днів
+230 день
Архів дописів
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል - ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተመዘገበው ስኬት ለሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት ያለፉት 9 ወራት አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአፈፃፀም ሪፖርትን ያቀረቡት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል÷ባለፉት 9 ወራት እንደ ሀገር በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፤ በሚኒስቴሩም ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡
በእያንዳንዱ ዘርፍ እድገት ሲመዘገብ በቀጥታ ከሥራ እድል ፈጠራ ጋር እንደሚገናኝ ገልፀው÷እንደ ሀገር የተከናወነው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለዘርፉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማድረጉን አንስተዋል፡፡
ባለፉት 9 ወራት ለ3 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ዜጎች የሥራ እድል መፈጠሩን የጠቀሱት ሚኒስትሯ÷የግብርና፣ የኢንዱስትሪ እና የአገልግሎት ዘርፎች ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ አስረድተዋል፡፡
የዲጂታል ሥራን በማጠናከር 344 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የውጭ ሀገር ሥራ እድል መፍጠሩን ጠቁመው÷ በኮደርስ ኢንሼቲቭ 45 ሺህ ዜጎችን የዲጅታል ሥራዎች ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አመላክተዋል፡፡
በተጨማሪም ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎችን የሥራ እድል ፈጠራ ስልጠናዎችን በመስጠት በአካባቢያቸው ያለውን ፀጋ እንዲመለከቱ ማድረግ መቻሉን አስገንዝበዋል፡፡
በልምድ ሲሰሩ ለነበሩ ሙያ ፈጣሪዎች ሚኒስቴሩ እውቅና መስጠት መጀመሩን እና በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 80 ሺህ የልምድ ባለሙያዎችን እውቅና ለመስጠት መታቀዱን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የሥራ ፍላጎት ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሯ÷የሥራ እድልን በመፈጠር ረገድ ከመንግስት በተጨማሪ ባለሃብቶችና ባለድሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
ሚያዝያ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
ለጥንቃቄ!
ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማሰራጫት ህብረተሰቡን ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየዳረጉ በመሆኑ መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የሌለ መሆኑን እየገለጽን ዜጎቻችን በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣ እንግልትና ሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
የሁለትየሽ ስምምነት በተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት የሥራ ዕድል ማግኘት ከፈለጉ የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ (lmis.gov.et) በመጠቀም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
ሚያዝያ 5፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/m
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ለአዳዲስ እጩ መዛኞች ስልጠና አዘጋጀ፤
ይህም ስልጠና በቀጣይ ሳምንት ለሚጀመረው አጠቃላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና አሰልጣኝ መምህራንን በምዘና ለማሳለፍ ከፌደራል የተሰጠውን አቅጣጫ ወደ ተግባር ለማስገባት በድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ የሚገኙ ከሁለተኛ ዲግሪ እና ከዚያ በላይ ያላቸውን መምህራን የእጩ መዛኝነት ስልጠና እንዲወስዱ ተደርጓል።
ከዚሁ ጎን ለጎን ማዕከሉ አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ ለማድረግ እንዲያስችለው ቀጣይነት ያለውና የማይቋረጥ የሪፎርም ስራዎችን በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን በዋናነት ከዩኒቨርሲቲው የተመረጡ መዛኞችን በማፍራት ምዘና እና መዛኝነትን በሚገባ ተረድተው ተመዛኙን በፍጹም ስነምግባር እንዲመዝኑ የሚያስችላቸው እንደሚሆን የማዕከሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ አሚን አብዱላሂ ገልጸዋል፡፡
ዳይሬክተሩ አክለውም ምዘና ያለ ብቁ መዛኝ የማይታሰብ መሆኑንና ከዚህም በላይ በብዛትም ሆነ በጥራት እንዲፈሩ የማድረጉ ስራ በተመሳሳይ ከተቋማት ጋር በትብብር እየተሰራ የሚገኝ መሆኑንና ከምዘና ጋር ተያይዞ ከተገልጋይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ከሚመልሱ ተግባራት አንዱና ዋነኛው አዳዲስ መዛኞችን ማፍራትና ማብቃት እንደመሆኑ ቀጣይነት እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 4/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የEASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣይ ሩብ አመት እቅድ ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት የተከናወኑ ያለፉት 3ወራት የትግበራ አፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣዩን 3ወራት እቅድ ለኮሌጁ ኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ በዛሬው እለት አቅርቦ በመድረኩ ውይይት ተደርጎበታል::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደገልፁት ፕሮጀክቱ በየሩብ አመቱ ሪፖርቱን ሲያቀርብ በዋነኛነት የደረሰበትን አፈፃፀም ደረጃ ለባለድርሻ አካላት ግልፅ ከማድረግም በተጨማሪ ለቀጣይ ትግበራዎች ግብዓት የሚሆኑ ምክረ-ሃሳቦችን ከመድረኩ ለማግኘት በማሰብ ጭምር መሆኑንም ገልፀዋል::
የፕሮጀክቱን ያለፈው ሩብ አመት አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት ዋና ኮርድኔተር ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን
በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርትም በሩብ አመቱ ሊሰሩ የታቀዱ በርካታ ተግባራት መከናወናቸው ተገልፇል::
በዚህም.... የፕሮጀክቱን አዲስ ቢሮ ከማደራጀት አንስቶ
-የGender & Inclucsive guidline ማዘጋጀት
-የአሰልጣኞችን የውጭ ስልጠና የማመቻቸት
-የDigitalization ስራዎች የማስፋፋት
-ከተለያዩ የፌደራል ተቋማት እና ከ14 አጎራባች ቴክኒክና ሙያዎች ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ውል የመፈራረም
-የተልያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች
-የHigh school ተማሪዎች ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በሩብ አመቱ ከተከናወኑት ተግባራቶች ውስጥ እንደሚጠቀሱም ተገልፇል::
መድረኩ ቀጥሎም በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 3ወራት በኮሌጁ የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የፕሮጀክቱ አፈፃፀምና የቀጣይ ትግበራ እቅድን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት የሚረዱ ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት ተደርጎበታል::
በመጨረሻም በEASE ፕሮጀክት የትኩረት ዘርፎች ተብለው በተለዩት ዲፓርትመንትቶች ላይ ጊዜው የደረሰበትን የስልጠና ማቴሪያሎች ለማሟላት በዲፓርትመንቶቹ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንን በማቀናጀት እየተዘጋጀ ሚገኘው የማቴሪያል ልይታ(Specification) ለኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርዱ የቀረበ ሲሆን የቦርዱ አባላትም ካላቸው ልምድ አኳያ በማቴሪያል ዝርዝሩ ላይ ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን እንዲሁም ማስተካከያ ሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች ምክረ-ሀሳብ እንዲሰጡበት የተደረገ ሲሆን የማቴሪያል ዝርዝሩን ሚያዘጋጁት መምህራንም ከመመድረኩ የተሰጠውን ግብረ-መልስ በማካተት በቀጣይ በሚኖረው መድረክ የሚያቀርቡም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሚያዚያ 4/2017 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ድሬ ፖሊስ lll ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓም
የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ እና የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ ።
በመርህ ግብሩ ላይ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክና ኮሌጅ አማካኝነት በሁለት ዙር መሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና የወሰዱ የድሬዳዋ ፖሊስ አባላት እና አመራሮች የተመረቁ ሲሆን የአስተዳደሩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የአስተዳደሩ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ክቡር ኮሚሽነር አለሙ መግራ እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰላዲን አብዱል ሀሚድና ሌሎች አስተዳደሩ እና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል ።
በመድረኩ ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር እንደተናገሩት ድሬዳዋን ስማርት ሲት የማደረግ ጥረት በአስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ገልፀው ይህንንም ለማሳካት በቴክኖሎጂ የታገዘ የፖሊስ ሃይል ወሳኝ በመሆኑ ይህንን ባገናዘበ መልኩ ሁሉም የፖሊስ አባላት መሰረታዊ የኮምፒውተር እውቀት እንዲኖር ለማስቻል ሁለቱ ተቋማት የጀመሩት ቅንጅታዊ ስራ የሚበረታታ እና የአስተዳደሩም አቅጣጫ ነው ብለዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ባስተላለፉት መልዕክት ቢሮአቸው ከዚህ ቀደምም ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጋር በቅርበት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸው በቀጣይም በተፈራረሙት ስነድ መሠረት የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት የአባላቱን የቴክኖሎጂ አቅም ከማሳደግ ባለፈ ተቋሙን በተለያዩ የቴክኖሎጂ ግብአቶች ለመደገፍ በትኩረት ሰጥቶ ከሚሰራቸው ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑን ተናግረዋል ።
ድሬዳዋ ፖሊስ ያስቀመጠው ራዕይ ጋር ለማደረስ በፍጥነት እየተጓዘ ነው ያሉት ክቡር ኮሚሽነር አለሙ መግራ ይህንን ዕውን ለማድረግ ከተለያዩ የትምህርት ተቋማት ጋር ለመስራት የሚያስችል ስነድ በመፈራረም ስራዎችን እየሰራ መሆኑን የገለፁት ሲሆን ከድሬዳዋ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ጋርም የተጀመረው የሁለቱ ተቋማት ጠንካራ ግንኙነት ይበልጥ ለማስቀጠል ስነድ መፈራረማቸውን ተናግረዋል ።
በተለይ የፖሊስ አባላቱን የቴክኖሎጂ አቅም ይበልጥ ለማሳደግ ከድሬዳዋ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ ጋር የሚሰሩ ሰፊ ስራዎች መኖራቸውንም ክቡር ኮሚሽነር አለሙ መግራ ጨምሮ ተናግረዋል ።
በመርሃ ግብሩ ላይ በሁለት ዙር የተሰጠው ስልጠና ላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ የፖሊስ አባለት እና አሰልጣኞች እንድሁም ለተቋሙ እውቅና እና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል።
ድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የብልፅግና ህብረት የ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ሩብ አመት ኮንፈረንስ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ።
በተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንዳሉት የብልጽግና ህብረቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በርካታ የፖለቲካ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀው በተለይ ደግሞ ከመንግስት ሥራ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የተገኘው ውጤታማ አፈጻጸም በጥምረት መቅረቡ ፖለቲካው ህብረተሰቡን የሚጠቅም ተጨባጭ ስራ ለመስራት ወሳኝ ሚና እንዲጫወት አድርጎታል ብለዋል።
የብልጽግና ህብረቱ ም/ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ አክለው በአስተዳደሩ ትኩረት የተሰጠውንና የቢሮው ዋነኛና ተቀዳሚ ተልዕኮ የሆነውን ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ አባላት ውጤት ሊያስገኝ የሚችልን ስራ በመስራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በግንባር ቀደምነት ልንሰለፍ ይገባል ብለዋል።
በኮንፈረንሱ ፕሮግራም ላይ የብልጽግና ህብረቱ የዘጠኝ ወር የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እና የቀጣይ 3 ወር ዕቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበት በአባላቱ በሙሉ ድምፅ የፀደቀ ሲሆን በመጨረሻም በቀጣይ ህብረቱን እና የኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን አደረጃጀትን የሚመሩ አመራር ምርጫን በዴሞክራሲያዊ መንገድ በማከናወን ኮንፈረንሱ ተጠናቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 4/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከተማዋን ጽዱና ውብ የማድረግ ዕቅድ አካል የሆነ የጽዳት ዘመቻ ተካሄደ።
በቢሮው ቅጥር ጊቢ እና አካባቢ ላይ በተካሄደው ጽዳት ዘመቻ የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል ።
በዘመቻው ላይ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደገለጹት ድሬዳዋን ጽዱ የምናደርገው እኛው እንጂ ሌላ አካል አለመሆኑን በመገንዘብ ሁሉም የቢሮው ማህበረሰብ ቀጣይነት ያለው የአካባቢውን ንጽሕና የመጠበቅ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም አሳስበዋል።
የፅዳት ዘመቻው በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተገልጿል ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 4/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ አገራዊ ጉባዔ ላይ የተሰጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ላይ የተዘጋጀ የሦስት ወራት ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ የሚከናወኑ ስራዎችን በመለየት ዝርዝር የድርጊት መርሃግብር በማዘጋጀት በስሩ ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ዕቅዱን በማውረድ በዕቅድ ጊዜያቶች ውስጥ በአጠቃለይ የሚፈጠሩ የስራ እድሎችን በአስተዳደሩ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡
የአስተዳደሩን ሥራ እድል ፈጠራን ከማጠናከር አንጻር ዋናዋና በዕቅዱ የተመላከቱ
ለስራ እድል ፈጠራው በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችን የመለየት ስራ በትኩረት ይከናወናል፡፡
በልምድ ተገኙ ክህሎቶችን የመለየት ስራ ይከናወናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በልምድ የተገኙ ክህሎቶች በምዘና የብቃት ማረጋገጥ ስራ ይከናወናል፡፡
ኢ-መደበኛ የሆኑ አንቀሳቃሾችን የመለየትና መረጃዎቻቸውን የማደራጀት ስራ ይከናወናል፡፡
በገጠርና በከተማ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራው ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን ይሆናል፣
ዜጎች በውጪ አገር የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት ይሰራሉ፡፡
የወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል የስራ ባህል ሊቀይሩና ከፍተኛ ተነሳሽነትን የሚፈጥሩ የማይንድ ሴት ስልጠናዎች የሚሰጡ ይሆናል፡፡
በተጨማሪ የማህበራዊ ልማቶችን የሚደግፉ ስራዎችን ለመስራት ታቅዷል
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
