1 068
Підписники
+224 години
Немає даних7 днів
+230 день
Архів дописів
በሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ አገራዊ ጉባዔ ላይ የተሰጡ አቅጣጫዎችን መነሻ በማድረግ በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ላይ የተዘጋጀ የሦስት ወራት ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ የሚከናወኑ ስራዎችን በመለየት ዝርዝር የድርጊት መርሃግብር በማዘጋጀት በስሩ ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ዕቅዱን በማውረድ በዕቅድ ጊዜያቶች ውስጥ በአጠቃለይ የሚፈጠሩ የስራ እድሎችን በአስተዳደሩ የሚገኙ ዜጎችን ተጠቃሚ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡
የአስተዳደሩን ሥራ እድል ፈጠራን ከማጠናከር አንጻር ዋናዋና በዕቅዱ የተመላከቱ
ለስራ እድል ፈጠራው በየአካባቢው የሚገኙ ፀጋዎችን የመለየት ስራ በትኩረት ይከናወናል፡፡
በልምድ ተገኙ ክህሎቶችን የመለየት ስራ ይከናወናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በልምድ የተገኙ ክህሎቶች በምዘና የብቃት ማረጋገጥ ስራ ይከናወናል፡፡
ኢ-መደበኛ የሆኑ አንቀሳቃሾችን የመለየትና መረጃዎቻቸውን የማደራጀት ስራ ይከናወናል፡፡
በገጠርና በከተማ የስራ ዕድል ፈጠራ ስራው ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን ይሆናል፣
ዜጎች በውጪ አገር የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት በትኩረት ይሰራሉ፡፡
የወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል የስራ ባህል ሊቀይሩና ከፍተኛ ተነሳሽነትን የሚፈጥሩ የማይንድ ሴት ስልጠናዎች የሚሰጡ ይሆናል፡፡
በተጨማሪ የማህበራዊ ልማቶችን የሚደግፉ ስራዎችን ለመስራት ታቅዷል
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት የስርዓተ-ፆታ ትግበራ መመሪያን ለማዘጋጀት የተሰራው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ ላለፉት ወራት ለዚህ ተግባር በተዋቀሩ ባለሙያዎች ሲዘጋጅ የቆየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዛሬው እለትም ለኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል::
የEASE ፕሮጀክት በቀጣይ አመታት በሚኖረው ትግበራ በHard Skills ላይ የሴት ሰልጣኞችን ቁጥር በተቻለ መጠን ለማሳደግ ትኩረት እድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ይህንን የዳሰሳ ጥናት በከፍተኛ ተነሳሽነት ያዘጋጁ ባለሙያዎችን አመስግነው በቀጣይም የስርዓተ-ፆታ መመሪያው ተዘጋጅቶ በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ እንዲገባ ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል::
ፕሮጀክቱ በዚህ የትግበራ ማእቀፍ በዋነኛነት የሴት ሰልጣኝ ተማሪዎችን እንዲሁም የኮሌጁ ሴት ሰራተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የምንሰራበት ነው ያሉት ደግሞ የEASE ፕሮጀክት ዋና ኮርድኔተር ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ ይህ ትግበራ በትክክል ግብ እንዲመታ ከማድረግ አኳያም የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱን የጉዳዩ ባለቤት በሆኑት ሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ሴት አመራሮች እንዲዘጋጅ እድርገናልም ብለዋል::
በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5አመት ውስጥ በስርዓተ-ፆታ ላይ ለሚከናወኑ ተግባራት መነሻ የሚሆን መመሪያ ለማዘጋጀት የተሰራው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በወ/ሮ ራሄል እሸቱ እንዲሁም በኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በHard Skills ላይ የሴት ሰልጣኞችን ውስነት መነሻ በማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ጥናትም በዋነኛነት የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት ሴት ሰልጣኞች የተሳተፉበት ሲሆን በተጨማሪም ዲፓርትመንት ተጠሪዎች፣ ሴት አሰልጣኝ መምህራን፣ የኮሌጁ ዲኖች እንዲሁም እንዱስትሪዎችንም በጥናቱ ተሳታፊ እንደነበሩ የተገለፀ ሲሆን በዘርፉ ለሚስተዋለው ችግር መንስኤ ናቸው ያሏቸው ጉዳዩችም ለጥናቱ በግብአትነት ተካተውበታል::
በመድረኩ በቀረቡት የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቶች መነሻነት ከተሳታፊዎች በርከት ያሉ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተካሄደ ሲሆን ጥናቱንም ለማዳበር ተጨማሪ ግብአቶች የተገኘበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሚያዚያ 3/2017 ዓ.ም
በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ከአስተዳደሩ የገጠር ወረዳዎች ምክትል ስራ አስፈፃሚዎች ጋር ውይይት አካሄዱ።
በዚህም በአጠቃላይ የሥራና ክህሎት ስራዎች ተደራሽነት ጋር በተያያዘ ተቀናጅቶ እና ተናብቦ የገጠሩን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች በሚሰሩበት አግባብ ላይ ውይይት አድርገዋል።
በተለይም በገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ትኩረት በመስጠት የገጠር ስራ ዕድልን ስርዓትን ከዚህ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን ማረምና መለወጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።
በተጨማሪም አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻል ፕሮጀክት (LLRP) ወጣቶችን ፣ ሴቶችን ብሎም ሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎችን በማህበር በማደራጀት አዋጭ በሆኑ የስራ መስኮች ተሰማርተው የገቢ ምንጫውንም በማስፋት ኑሯቸውን የሚያሻሽሉበትን መንገድ ለማመቻቸት እየተሰራ ያለውን ስራ ትርጉም ባለው መልኩ የገጠሩን ነዋሪ ህይወት ቀያሪ ሆኖ ማሳየት ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በሥራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገነቡት የኮንስትራክሽን ስራዎች ላይ ለሚሰሩ የቀን ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ ለ2ኛ ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ።
መድረኩን በመክፈት ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ኤች አይ ቪ ኤድስ ሴክሬተሪያት ባለሞያና የፅ/ቤቱ ተወካይ የሆኑት አቶ የኋላሸት ውብሸት ሲሆኑ በኮንስትራክሽን ዘርፍ ስራዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙ እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነታቸው ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም ይህ ሀይል ወጣቶችንና ሴቶችን በከፍተኛ ቁጥር ያካተተ በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት የዛሬው መድረክ እንደተዘጋጀ ገልፀው መድረኩን አስጀምረዋል።
በመቀጠል የዕለቱን ስልጠና የሰጡት አቶ ፈቲ መሀመድ ሲሆኑ የስልጠናውን ሰነድ ካቀረቡ በኋላ መድረኩን ለውይይት ክፍት በማድረግ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦችና ጥያቄዎችን ተቀብለው ምላሾችንም ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የሥራና ክህሎት ቢሮ የሴቶች ወጣቶችና ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ ማርታ በዛብህ ይህ አይነቱ መድረክ በተከታታይነት እንደሚዘጋጅና ተጨማሪ ስራዎችም ቢሮው እንደሚሰራ ገልፀው መድረኩ ተጠናቋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 3/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የትምህርትና ስልጠና ስርዓቱን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ወቅቱን ያማከለ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በICT ዲፓርትመንት የተጀመረውን የትምህርትና ስልጠና ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝድ የማድረግ ስራ በስፋት እንዲከናወን ለማድረግ ያለመ የውይይት መድረክ ተካሄደ::
በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ አንደኛው በትኩረት ከተያዙ ጉዳዮች ውስጥ የትምህርትና ስልጠና አሰጣጡን ዲጂታላይዝድ ማድረግ ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም እሁን ላይ የትኛው ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ሲደረግ የአይ.ሲ.ቲ መሰረት ልማትና የግሪን ኢነርጂ ላይ ትኩረት እዲደረግ ይጠይቃልም ብለዋል::
ICT ላይ ቀድሞ የተጀመረና የዲጂታል ኮንቴንት (E-learning System) ላይ የተሰራ ስራ መኖሩን ያስትትወሱት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ የተጀመሩትን ስራዎች ኮሌጁ የልህቀት ማዕከል በሆነባቸው ዘርፎች ላይ እያሰፋን እስከ ፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ድረስ በኮሌጁ ያሉትን እንቅስቂሴዎች ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ለመቀየር እሰራለንም ብለዋል::
በኮሌጁ የICT ዲፖርትመንት አማካኝነት የትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን እየተሰራ ያለው ስራ ይበልጥ ለማስፋት የተዘጋጀውን ሰነድ በዲፓርትመንቱ ተጠሪ አሰልጣኝ መ/ር አቤል ፋንታሁን አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይም በICT አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም በኮሌጁ ሀላፊዎች ውይይት የተካሄደበት ሲሆን በተቀመጠው Action plan መሰረትም ወደ ትግበራ እንደሚገባ ከመድረኩ ማወቅ ተችሏል::
የE-Learning system/ የትምህርትና ስልጠናውን ከማዘመኑም በተጨማሪ ሰልጣኝ ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ቆይታቸው ስልጠናቸውን እንኪያጠናቅቁ ድረስ ሙሉ የትምህርትና ስልጠና መረጃቸውን ሲሰተሙ የሚይዝ በመሆኑ የስልጠናቸውን ሁኔታና አፈጻጸም እንዲሁም የትምህርትና ስልጠናውን ጥራት በማስጠበቅ ረገድ የራሱን እስተዋፅኦ እንደሚያደርግም ይታመናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ሚያዚያ 2/2017 ዓ.ም
በድሬደዋ አስተዳደር ከተለያዩ ቢሮዎችና ከሚመለከታቸው አካላት የተወጣጣ የሱፐርቪዥን ቡድን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦም ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ የቀረበው ሪፖርት አቀራረቡንና የተከናወኑ ስራዎችን አድንቀው በቀጣይ ሊተኮርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገባቸውን ጉዳዮች ሀሳብና አስተያየቶች አክለው ለቢሮው ግብረመልስ የሚሰጡም ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ከሚያስተባብሩ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የፕሮግራም አስተባባሪዎች ጋር በሥራ ፈጠራና ክህሎት ልማት የጋራ ዕቅድ ላይ ያተኮረ ውይይትና ስምምነት አካሄደ፤
በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞች ሲኖሩ በዛሬው ዕለት ከቢሮው ጋር ስራዎቻቸውን በዕቅድ አናብበው ለመስራት የተስማሙት የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም፣ ጥላ ፕሮግራም፣ ሳፊ ፕሮግራም፣ መስመር ፕሮግራም እና ሲድ ፕሮግራም ናቸው፡፡
የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም : 5 ዓመት የሚቆይ ፕሮግራም ሲሆን፣ 100 ጊግ ሞዴል ያላቸውን ቢዝነሶችን መርጦ ሁለገብ ድጋፍ ይሰጣል።
ጥላ ፕሮግራም ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ የገጠር ወጣት ሴቶች ቀጣይነት ያለው የኑሮ መሻሻል እንዲፈጠር መነሻ ካፒታል የሚሆን የሶስት አመት ከዋስትና ነጻ የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ እና ቢዝነሶቹን በቅርበት ውጤታማነታቸውን በመከታተል መደገፍ ላይ የሚሰራ ነው።
ሳፊ ፕሮግራም ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራ ሲሆን መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን ያቀርባሉ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ ይሰራል።
መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የብድር አገልገሎት ይሰጣል አገልገሎቱ በአስተዳደራችን የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ሲድ ፕሮግራም እንደ ኢትዮጵያ ለአንድ ሚሊዮን ወጣቶች እና ሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ይፈልጋል፡፡ አንድ መቶ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን በማጎልበት ለውጥ አምጭ የንግድ ሞዴሎችን በማስተዋወቅ፣ የንግድ መፈልፈያ ማዕከላትን በማቋቋምና ወደ ስራ በማስገባት እንዲሁም ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ልማቶችን በማጎልበት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን ለመደገፍ በማለም የሚተገበር ነው፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ አበይት ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ላይ የአጋር አካላት ሚና ቀላል የማይባል መሆኑንና በቀጣይም ተቀራርቦ እና በየጊዜው ስራዎችን አቅዶ እየገመገሙ መሄድ አስፈላጊ በመሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለፁት የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እየተተገበሩ የሚገኙ ፕሮግራሞችን ከዘርፉ እሳቤ ጋር የተቀናጀ እንዲሆኑ ለማስቻል ብሎም ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር በጋራ አቅዶ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ከሚያስተባብሩ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የፕሮግራም አስተባባሪዎች ጋር በሥራ ፈጠራና ክህሎት ልማት የጋራ ዕቅድ ላይ ያተኮረ ውይይትና ስምምነት አካሄደ፤
በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞች ሲኖሩ በዛሬው ዕለት ከቢሮው ጋር ስራዎቻቸውን በዕቅድ አናብበው ለመስራት የተስማሙት የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም፣ ሳፊ ፕሮግራም፣ መስመር ፕሮግራም እና ሲድ ፕሮግራም ናቸው፡፡
የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም : 5 ዓመት የሚቆይ ፕሮግራም ሲሆን፣ 100 ጊግ ሞዴል ያላቸውን ቢዝነሶችን መርጦ ሁለ ገብ ድጋፍ ይሰጣል፤
ሳፊ ፕሮግራም ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራ ሲሆን መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን ያቀርባሉ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ ይሰራል፤
መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የብድር አገልገሎት ይሰጣል አገልገሎቱ በአስተዳደራችን የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ሲድ ፕሮግራም እንደ ኢትዮጵያ ለአንድ ሚሊዮን ወጣቶች እና ሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ይፈልጋል፡፡ አንድ መቶ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን በማጎልበት ለውጥ አምጭ የንግድ ሞዴሎችን በማስተዋወቅ፣ የንግድ መፈልፈያ ማዕከላትን በማቋቋምና ወደ ስራ በማስገባት እንዲሁም ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ልማቶችን በማጎልበት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን ለመደገፍ በማለም የሚተገበር ነው፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ አበይት ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ላይ የአጋር አካላት ሚና ቀላል የማይባል መሆኑንና በቀጣይም ተቀራርቦ እና በየጊዜው ስራዎችን አቅዶ እየገመገሙ መሄድ አስፈላጊ በመሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለፁት የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እየተተገበሩ የሚገኙ ፕሮግራሞችን ከዘርፉ እሳቤ ጋር የተቀናጀ እንዲሆኑ ለማስቻል ብሎም ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር በጋራ አቅዶ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዝያ 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞችን ከሚያስተባብሩ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የፕሮግራም አስተባባሪዎች ጋር በሥራ ፈጠራና ክህሎት ልማት የጋራ ዕቅድ ላይ ያተኮረ ውይይትና ስምምነት አካሄደ፤
በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ስር የሚገኙ የተለያዩ ፕሮግራሞች ሲኖሩ በዛሬው ዕለት ከቢሮው ጋር ስራዎቻቸውን በዕቅድ አናብበው ለመስራት የተስማሙት የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም፣ ሳፊ ፕሮግራም፣ መስመር ፕሮግራም እና ሲድ ፕሮግራም ናቸው፡፡
የመስራት ስራ ፈጣሪዎች ፕሮግራም : 5 ዓመት የሚቆይ ፕሮግራም ሲሆን፣ 100 ጊግ ሞዴል ያላቸውን ቢዝነሶችን መርጦ ሁለ ገብ ድጋፍ ይሰጣል፤
ሳፊ ፕሮግራም ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰራ ሲሆን መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ብድሮችን ያቀርባሉ በተለይ ለኢ-መደበኛ ተበዳሪዎች በመታወቂያ ብቻ ብድሮችን ከእጅ ንክኪ ነጻ የሆነ በAI ታግዘው ብድሮችን ያመቻቻሉ፤በዚህም በዋናነት 80% ሴቶች፣ 10% ለአካል ጉዳተኞች እና 10% ለተፈናቃዮች ትኩረት አድርጎ ይሰራል፤
መስመር ፕሮግራም የብድር አገልገሎት ሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን ለማበረታታትና ሥራቸውን ለማስፋፋት የብድር አገልገሎት ይሰጣል አገልገሎቱ በአስተዳደራችን የሚገኙ በተለይም በወጣት ሴቶች የሚመሩ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በመጠነኛ ዋስትናና በአነስተኛ የወለድ መጠን እንዲሁም የሸሪአ መርህን የተከተለ ከወለድ ነጻ የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
ሲድ ፕሮግራም እንደ ኢትዮጵያ ለአንድ ሚሊዮን ወጣቶች እና ሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ይፈልጋል፡፡ አንድ መቶ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጆችን በማጎልበት ለውጥ አምጭ የንግድ ሞዴሎችን በማስተዋወቅ፣ የንግድ መፈልፈያ ማዕከላትን በማቋቋምና ወደ ስራ በማስገባት እንዲሁም ፍላጎትን መሰረት ያደረጉ ልማቶችን በማጎልበት የወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን ለመደገፍ በማለም የሚተገበር ነው፡፡
በመድረኩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ አበይት ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ላይ የአጋር አካላት ሚና ቀላል የማይባል መሆኑንና በቀጣይም ተቀራርቦ እና በየጊዜው ስራዎችን አቅዶ እየገመገሙ መሄድ አስፈላጊ በመሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአስተዳደሩ ከተማና ገጠር ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የአጋር አካላት ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን የገለፁት የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን እየተተገበሩ የሚገኙ ፕሮግራሞችን ከዘርፉ እሳቤ ጋር የተቀናጀ እንዲሆኑ ለማስቻል ብሎም ጠንካራ ትብብር ለመፍጠር በጋራ አቅዶ በትኩረት ይሰራል ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ ሥራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሮክቶሬት በ2017 ዓ.ም የተዘጋጁ ከ75 በላይ በስራ ገበያ ተፈላጊ የሆኑ ፤የስራ እድል የሚፈጠርባቸው የተለዩ አዳዲስ ገበያ ላይ ሊውሉ የሚችሉ ገበያ ተኮር አጫጭር ስልጠና የሚሰጥባቸው ስርዓተ ትምህርቶች እና የማሰልጠኛ መሳሪያዎችን ለመንግስት ኮሌጆች ዲፓርትመንት ተጠሪዎች ፤ለግል ማሰልጠኛ ተቋማት እና ለድሬዳዋ ፌደራል ማረሚያ ቤቶች ማስተዋወቅና ማሰራጨት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ፡፡
በዚህም የአዲሱ የTVET ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ላይ ተመስርተው የተዘጋጁና የተከለሱ በቀጥታ የስራ እድል የሚፈጠርባቸው የተለዩ አዳዲስ የአጫጭር ስልጠና የሚሰጥባቸው በገበያ ላይ ሊውሉ የሚችሉ ከክህሎት ስልጠና እና ከስራ ጋር የተቆራኙ በኢንዱስትሪው መስክ ፤በቴክኖሎጂ እድገት ምክኒያት በየጊዜው እየተለወጠ የመጣውን ተፈላጊ የሆኑ ችሎታዎች እንዲኖሯቸው የሚያስችሉ የሚፈለገውን ክህሎት የሚያጎሉ ሙያዎች እና በቴክኒክና ሙያ ስልጠና አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመክፈት እና ማስፋፋት ፍላጎትን ለማሟላት የሚስችሉ በጣም አስፈላጊ የማሰልጠኛ መሳሪያዎች ተዘጋጅተው ሲሰራጩ መቆየታቸውን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን የገለጹ ሲሆን የስርዓተ-ስልጠና እና የማሰልጠኛ መሳሪያዎች ስርጭትን አስመልክቶ በነባራዊ ሁኔታ የሚታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ላይ ውይይት በማድረግ መድረኩ ተጠናቋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 1/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ለትራንስፖርት ማህበራትና በኢንዱስትሪዎች ለሚገኙ ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
የስልጠና መድረኩ የሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር በአዋጅ ቁጥር 1156/2011 በሕብረት ድርድር ዙሪያ ሲሆን በይበልጥ ትኩረቱን በሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር ያደረገና በአሰሪና ሠራተኛ መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን ለማስቀርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሥራ ቦታ ማሕበራዊ ምክክር የሚጫወተውን ሚና ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
አዋጁን በመረዳትም የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ሚያዚያ 1/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
