1 091
Підписники
+324 години
+257 днів
+1730 день
Архів дописів
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከመንግስትና ከግል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሳይንስ ትምህርቶች ላይ ዝንባሌ ላላቸውና የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች በSTEM Power ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ወጣቶችን በእውቀት በክህሎት በአመለካከት ከማሰልጠን ውጪ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በመቀበል እንዲሁም ሊሰሩት ያሰቡትን ቴክኖሎጂ ወደመሬት አውርደው ለራሳቸው ብሎም ለሃገራቸው የሚተርፍ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና ሃሳባቸውን ወደ ቢዝነስ ሃሳብ እንዲቀይሩ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡አሁንም በዚህ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ የተሳተፋችሁ እንዲሁም በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉ የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው የከተማችን ወጣቶች የፈጠራ ሃሳባቸውን ይዘው መጥተው ከፈጠራ ስራቸው ተጠቃሚ እንዲሆኑ በራካታ ስራዎችን በጋራ በመስራት ለራሳቸው ብሎም ለሃገር እንዲጠቅሙ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡በተጨማሪም ም/ዲኗ እንደገለጹት ኮሌጃችን በአሁኑ ሰአት በባቡር ቴክነሎጂ እንዲሁም በICT የትምህርት ዘርፎች የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ነው ስለዚህ የከተማችን ወጣቶች ይህንን እድል በአግባቡ ተጠቅመው እራሳቸውንም ሃገራቸውንም እንዲጠቅሙ በዚሁ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ ብለዋል፡፡
በመድረኩ ላይ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ አንጻር የሚንቀሳቀሱ ትምህርት ክፍሎች በኮሌጁ ውስጥ ተማሪዎች ቢመጡ ብምን አይነት መንገድ አብረን መስራት እንችላለን በሚል ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በመቀጠልም በተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ጉብኝት በማድረግ የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
የግል ኮሌጆችን በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ ላይ ማሳተፍ የግሉን ዘርፍ በማህበረሰብ ዓቀፍ አገልግሎት ውስጥ ሚናውን እንዲወጣ ያስችላል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተመላከተው መሰረት የግል የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት ለኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ መስጠት እንዲያስችላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ።
በዚህም የግል ኮሌጆች በንግድ እና አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ላይ ሁሉንም ኢንተርፕራይዞች በማዳረስ ረገድ የተፈጠረውን ጫና የሚጋሩ ይሆናል፤ በመሆኑም ሐረር ላይ ከተወሰደው ተሞክሮ በመነሳት በቀጣይ ወደ ተግባር ለማስገባት ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን በዳይሬክቶሬቱ የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ቡድን መሪ ወ/ሮ አለምፀሀይ ጌታቸው ተናግረዋል።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ የተገኙ የግል ኮሌጆችም ማህበረሰቡን ሊጠቅም በሚችል ስራዎች ላይ የመሳተፍ ቁርጠኝነታቸውን በማሳየት በቀጣይም ቢሮው በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ትግበራ ለመግባት ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን በማጠቃለያውም የኮሌጆቹን ተነሳሽነት በማድነቅ የግል እና የመንግስት ኮሌጆችን በማቀናጀት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ስራዎችን መስራት እንደሚገባ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ገልፀዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 21/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የባለድርሻ ተቋማት ቅንጅት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲየኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የኢንተርፕራይዞች ፍትሃዊ መንግስታዊ ድጋፎች ተጠቃሚ በማድረግ የኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አካሄደ።
ዳይሬክቶሬቱ በተለያዩ ዘርፎች ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ አስተማማኝነትን ለማረጋገጥና ከባለድርሻ አካላት በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል ሰነድ ቀርቦ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሚመለከታቸው የተቋማት ተወካዮች በተገኙበት የጋራ ስምምነትና መግባባት የተፈጠረበት ውይይት ማካሄድ ተችሏል፡፡
በውይይቱ ላይ የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደተናገሩት የዛሬ መድረክ ዋና ዓላማ በአስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፍ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎችን በቅንጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚከናወኑ ተግባራትን በጋራ በማከናወን ኢንተርፕራይዞችን በአጭር ጊዜ ወደ ስራ ገብተው ምርታማነታቸውንና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ እንደሆነ ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 20/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ የኤች.አይ.ቪ መከላከል" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ36ኛ ጊዜ በሀገራችን ለ35ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም ኤድስ ቀን የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች በፓናል ውይይት አከበሩ።
በፓናል ውይይቱም የኤች አይ ቪ ጉዳይ በማህበረሰባችን ዘንድ የሚታየው መዘናጋትና በበሽታው የሚከሰተውን ችግሮች መቅረፍ እንዲቻል ታላሚ ያደረገ ሲሆን ለዚህም ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የድርሻውን በትብብርና በኃላፊነት መወጣት እንዳለበት ተመላክቷል፡፡
የኤች አይ ቪ ስርጭት አሁን ላይ እጅግ አሳሳቢ በሆነ ደረጃ ላይ የሚገኝ መሆኑንና ከዚህም ጋር በተያያዘ በበሽታው የሚፈጠረው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ከፍተኛ መሆኑና በየአካባቢያቸው የሚመለከቷቸውን ለቫይረሱ ተጋላጭ የሚያደርጉ ጉዳዮችን የፓናሉ ተሳታፊዎች አንስተዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 21/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኮሌጁ የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈጻጸምና የ EASTRIP ፕሮጀክት አፈጻጸም ከስራና ክህሎት ሚንስቴር እና ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ በተወውጣጣ የSupervision team ግምገማ ተከናወነ፡፡
የኮሌጁ የመጀመሪያ ሩብ አመት አፈጻጸምና የ EASTRIP ፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማ ሂደቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ ትንሿ ኢትዮጵያ የፍቅር ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ በደህና መጣችሁ ፡፡ ይህ በአለም ባንክ ድጋፍ የሚተገበረው የ EASTRIP ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ብዙ ወጣቶችን የክህሎት፣የስራ ባለቤት እንዲሁም የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ እንደሆነ እና ከተማችንን የምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ማእከል እንደሚያደርግ እተማመናለሁ፡፡ በተጨማሪም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የ EASTRIP ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር ፕጀክቱ ከግብ እንዲደርስ ማቺንግ ፈንድ ከመመደብ በዘለለ ለፕሮጀክቱ መሳካት እንቅፋት የሆነውን የበጀት ልዩነቶችን በመጋራት ያሳየው ተነሳሽነት ለሌሎች ከተሞች አርአያ የሆነ ተግባር ፈጽመዋል ይህም ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡በተጨማሪም ኮሌጁ ስራዎችን ለማሳለጥ እንዲሁም የተቀላጠፈ አሰራሮችን ለማምጣት በማቀድ የተለያዩ ICTን መሰረት ያደረጉ አሰራሮችን በመዘርጋት እንዲሁም የተለያዩ ጥናቶችን በማጥናት ፕሮጀክቱ ቀጣይነት እንዲኖረው በትጋት የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
የግምገማ ሂደቱን ለማከናወን የመጣውን ልኢክ ቡድኑን የመረቱ አቶ መለሰ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አርአያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በተጨማሪም ፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ወቅት በከተማ አስተዳደሩና በኮሌጁ ማኔጅመንት የሚወሰዱት የመፍትሄ እርምጃዎች ለሌሎች ኮሌጆች እንደ መልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 20/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
መረጃውን በማድረስ ይተባበሩን!!
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው የቅጥር ማስታወቂያ ላይ ተመዝግባችሁ የፅሁፍ ፈተና ያለፋችሁ የከተማችን ወጣቶች የኢንተርቪው ፈተና ህዳር 25/2016 ዓ.ም ጀምሮ በሰንጠረዡ በተጠቀሰው ሰዓት ስለሚሰጥ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንድትገኙ ጥሪ ተላልፏል።
‘’ብዝሀነት እና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት’’ በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት እና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በጋራ በመሆን 18ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀንን አክብረዋል፡፡
"ብዝሃነትና እኩልነት
ለአገራዊ አንድነት!"
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች 18ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን አከበሩ።
በዓሉ በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ብዝሃነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን አውስተው፣ አገራዊ አንድነትን ለማጽናት ሕገ መንግሥቱን መሠረት በማድረግ ጥያቄዎችን በሰላማዊ አግባብ የሚያስተናግድ ሥርዓት መገንባት ቀዳሚ የመንግሥት ትኩረት እንደሆነ ተናግረዋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት እና የጋራ መብታቸው የተረጋገጠበት ሕገ መንግሥት የጸደቀበትን ኅዳር 29 ቀን መነሻ በማድረግ የሚከበር መሆኑንና በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡ መብቶችን አስጠብቀን ልንጓዝ የምንችለው ተግባራዊ ለማድረግ ሁላችንም የድርሻችንን ስንወጣ ይሆናል ብለዋል፡፡
የውይይቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የብሔር ብሔረሰቦች ቀን መከበሩ የሕዝቦችን እኩልነትና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ለማጠናከር ጠቀሜታው የጎላ እንደሆነ ገልጸው፣ አንድነትን ለማጠናከር ሰላምን የሚያደፈርሱ አጀንዳዎችን የማስወገድ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አሳስበዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 17/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የተለያየ ዘርፍ ስር ለሚገኙ ኢንደስትሪዎችና ኢንተርፕራይዞች አሰሪና ሰራተኞች ተከታታይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።
በቢሮው የውጭ አገር ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የሰራተኛውን ደህንነትና ጤና የማስጠበቅ ስራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚጫወተው ሚና ቀላል አይደለም።
በመሆኑም በአስተዳደሩ በሚገኙ ኢንደስትሪዎች እና ኢንተርፕራዞች የሙያ ደህንነትና ጤንነት ኮሚቴ አንዲደራጅና እንዲቋቋም ድጋፍ በማድረግ ለተመሰረቱት ኮሚቴዎችም በቀጣይ ስለሚያከናውኗቸው ሥራዎች በማስገንዘብ በተለይ የሙያ ደህንነቱና ጤናው የተጠበቀ የስራ አካባቢን በመፍጠር የኢንደስትሪውን ሰላም እና ደህንነት በማስጠበቁ ረገድ ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑንና በተጨባጭም ውጤት የሚያስገኝ ይሆናል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 15/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት የተለያየ ዘርፍ ስር ለሚገኙ አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት አሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ስልጠና ተሰጠ።
በቢሮው የውጭ አገር ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የሰራተኛውን ደህንነት የማስጠበቅ ስራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንዱስትሪውን ምርታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚጫወተው ሚና ቀላል አይደለም።
በተጨማሪም በተለይ በአሰሪና ሰራተኞች መካከል የሚፈጠረውን አለመግባባት በመቀነስ እንዲሁም የኢንደስትሪውን ሰላም በማስጠበቁ ረገድ ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑንና በተጨባጭም ውጤት እያስመዘገበ ይገኛል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 13/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
