1 091
Підписники
+324 години
+257 днів
+1730 день
Архів дописів
Repost from N/a
በጀርመን ሀገር ሚገኘው የአድራ ጀርመኒ የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስፍፃሚ ልኡካን ቡድናቸውን በመያዝ በአድራ ኢትዮጵያ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጉብኝት እካሄዱ::
አድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ የሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን ወርክሾፕ በማደራጀት እና ስልጠናውን ለመስጠት የሚያስችል አቅም በመፍጠር በአሁን ሰአት ከገጠር እና ከከተማ የተመለመሉ ሰልጣኞች 23 ከገጠር 20 ከከተማ በድምሩ 43 ሰልጣኞችን በመያዝ ስልጠናውን በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናውን በመስጠት ላይ ይገኛል::
ልኡካን ቡድኑም በቅድሚያ በአዲስ መልክ የተደራጀውን የፕሮጀክቱን ማሰልጠኛ ወርክ ሾፕ ተዝዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህም ሰልጣኞቹ የመግቢያ ፈተና ወስደው በተገኘው ውጤት መሰረት የ Life Skill ስልጠና ካገኙ በኋላ መሰረታዊ የኤሌክትሪክ እና የኮምፒውተር ስልጠና በመውሰድ ላይም እንደሚገኙ ተመልተው በቀጣይም ሰልጣኞቹ ወደ ሶላር ስልጠና እንደሚያመሩ ከአስተባባሪዎች ገለፃ ተደርጎላቸዋል::
የአድራ ጀርመኒ ዋና ስራ አስፈፃሚና ልኡካቸው በኮሌጁ የተገኙት ይህንን ጨምሮ በፕሮጀክቱ የተሰሩ አጠቃላይ ስራዋችን ለመገምገም እና የግብአት ጉድለቶችን ለማሟላት የሚያስችል ሁኔታዋችን ለመፍጠር እንዲሁም ሰልጣኞች ያሉበትን ሁኔታ ለማየት ሲሆን በፕሮጀክቱ የታዩትን ተግዳሮቶች እና በቀጣይ ሊሰሩ የሚችሉ ተግባራትን ከኮሌጁ ዲኖች እና ከአሰልጣኝ መምህራኑ ጋር በጥልቅ ተወያይተዋል::
በመጨረሻም ልዑካኑ ከአድራ ሶላር core string comittee ጋር በመገናኘትና ውይይት በማድረግ ፕሮጀክቱ ያለበትን ሁኔታ በመገምገም ያሉትን ማነቆዎች በማውጣት ቀጣይ የመፍትሄ አቅጣጫዎች ናቸው ያሏቸውን በዝርዝር ለይተው አስቅምጠዋል::
በተሰጠውም ግብረመልስ በፕሮጀክቱ አፈፃፀምና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ልዑካን ቡድኑ በእጅጉ መደሰቱበመግለፅ ለኮሌጁ ምስጋናቸውን ይቀረቡ ሲሆን በቀጣይም የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሶላር ዘርፍ በምስራቁ ክፍል center of exellence ሊሆን የሚችልበትን ሁኔታ ና አቅም ለመፍጠር ዝግጁ መሆናቸውንም ገልፀዋል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 14/2016 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የከተማውን ወጣቶች በአጫጭር እንዲሁም በመደበኛ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት ስልጠናዎችን እየሰጠ ወጣቶችን የስራ ፈጣሪ ብሎም ለኢንዱስትሪው ግብአት የሚሆኑ ወጣቶችን በማሰልጠን ለከተማችን እድገት መጫወት የሚችሉ ወጣቶችን እያፈራ ይገኛል።››
አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ
የኮሌጁ ም/ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ
****
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ‹‹ክረምትን በክህሎት በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ›› በሚል መሪ ቃል በዘንድሮ አመት 12ኛ ክፍል ላጠናቀቁ ተማሪዎች ሲሰጠው የነበረው በተለያዩ ዙሮች በክረምት መርሃ ግብር ስልጠና ሲሰለጥኑ የነበሩ ሰልጣኞችን የእውቅና ሰርተፊኬት መስጠትና ስለ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ገለጻ መድረክ በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት እና ለሰልጣኞች ሰርተፊኬት የሰጡት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ትምህርት እና ስልጠና ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ እድገት ቁልፍ መሳሪያ ነው። ይህን መሳርያ ደግሞ ለከተማችን ወጣቶች ማድረስ ይኖርብናል፡፡ለዚህም በዛሬው እለት በተለያዩ ሞያዎች በተለያዩ ዙሮች ስልጠናችሁን የተከታተላችሁ የከተማችን ወጣቶች አንዱ ማሳያ ናቸው ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ም/ዲን በማስቀጠል የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የከተማችንን ወጣቶች በሞያቸው በእውቀታቸው እንዲሁም በጉልበታቸው ሀገራቸውን ማገልገል እንዲችሉ እንዲሁም ለራሳቸው የስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ከፍተኛውን ሚና እየተጫወተ ይገኛል።በቀጣይም ለሌሎች ወጣቶች የተለያዩ ስልጠናዎችን በረጃጅምና በአጫጭር በማዘጋጀት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ ከዚም አልፈው ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ትልቅ ስራን የሚሰራ ይሆናል፡፡ ለዛሬ ቀን የደረሳችሁ ሰልጣኞች ለድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ አባሳደር ናችሁ እዚህ ያገኛችሁትን መልካም ተሞክሮ ለሌሎች ይህን እድል ላላገኙ ጓደኞቻችሁ በማድረስ ኮሌጃችንን ተመራጭ እንድታደርጉ ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡በመጨረሻም ይህ ስልጠና እንዲሳካ ላደረጉና ስልጠናውን ለሰጡ መምህራኖች እንዲሁም የአስተዳደር ሰራተኞች ምስጋና ማቅረብ እወዳሉ ብለዋል፡፡
በመጨረሻም በኮሌጁ ስልጠናዎችን ወስደው ለራሳቸው ብሎም ለሌሎች የስራ እድል በመፍጠር ስኬት ያስመዘገቡ የከተማችን ወጣቶች ለሰልጣኞች እንዲሁም ለመደበኛ ሰልጣኞች ያላቸውን የህይወት ተሞክሮና የስራ ልምድ ያካፈሉ ሲሆን በተጨማሪም በኮሌጁ ውስጥ የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ክፍሎች ስለ ትምህርት ክፍላቸው ገለጻ በማድረግ ኮሌጁን ተመራጭ አድርገው ትምህርትና ስልጠና በኮሌጁ እንዲያገኙ ቅስቀሳ አድርገዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
"ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው! በጋራ እንታገለዋለን!"
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው! በጋራ እንታገለዋለን!" በሚል በአገር አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን ምክንያት በማድረግ ከቢሮው ማህበረሰብ ጋር ተወያይቷል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት የሙስና ምክንያት የሆነውን የስነ-ምግባር ዝቅጠትንና ስግብግብነትን ለማረም እና አይቶ እንዳላየ ማለፍን ለማስቆም የቢሮው ሰራተኞችና አመራሮች ሚና ላቅ ያለ መሆኑን አስረድተዋል።
የፀረ-ሙስና ትግሉ በቢሮው የአገልግሎት አሰጣጥ ዘንድ እንዲቀጣጠልና በዋናነት የስነ ምግባር ግንባታው የድርሻውን ተወጥቶ የሚታመንና የሚተማመን ሰራተኛና አመራር መፍጠር እንደሚገባ በመድረኩ ውይይት ተመላክቷል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 14/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ብቃት" የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ትብብር ላደረጉ ተቋማት የተዘጋጀ የምስጋና እና የዕውቅና መድረክ ተካሄደ፤
በዚህም መድረክ ላይ የድሬዳዋ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመክፈቻ ንግግራቸው በዋናነት ከተማችን የምትለማው እና ሁለንተናዊ ለውጥ የምታስመዘግበው አምራቹ ወይም ባለሀብቱ ወጣቱን ወደ ሥራ ሲያስገባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በልዩ ሁኔታ ይህንን ቅጥር ለፈጸሙ ድርጅቶች አስተዳደሩ ከፍተኛ አድናቆት እና ክብር ያለው መሆኑንና ሌሎችም በድርጅታቸው እና በእጃቸው ሞያ ያስተማሯቸውን ወጣቶችን በመቅጠር እንደ መንግስት የተያዘውን ዕቅድ እንዲያሳኩ እና እንዲደግፉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
ኃላፊዋ አክለውም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ወጣቶችም ይህንን ያገኙትን ወርቃማ እድል እንዲጠቀሙበት በማሳሰብ ከዚህ በፊት የነበረውን ‹‹የድሬዳዋ ልጅ ሥራ አይወድም›› የሚባለውን የሰነፎች አባባል ውድቅ በማድረግ ለቤተሰቦቻቸው አልፎም ለሀገራቸው የኩራት ምንጭ እንዲሆኑ ጨምረው አሳስበዋል፡፡
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ አጠቃላይ በዚህ ፕሮጀክት ሥራ ፈላጊ ወጣቶችንና ኢንደስትሪዎችን በተመሳሳይ ጊዜ በብዙ ሊጠቅም የቻለ መሆኑን ጠቅሰው በተለይ ኢንደስትሪዎች ከተጠቃሚነታቸው ጎን ለጎን ማህበራዊ ኃላፊነትን ለመወጣት ዕድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
ዳይሬክተሩ ጨምረው በፕሮግራሙ የታቀፉ ወጣቶች ሥራ ባህል እና ፍላጎት መሻሻል ማሳየቱ፤ መንግስት አና የግል ሴክተር ተቀራርበው በመስራት የሥራ አጥነት ችግርን ለመፍታት አውንታዊ አስተዋጾ እንዳላቸው በተግባር ማሳየታቸው፤ ከፕሮግራሙ ግብ አንጻር ዝቅተኛ ቢሆንም አሁን 85 የሚሆን ድርጅቶች 141 ወጣቶችን መቅጠራቸውን የሚያበረታታ መሆኑን እና በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ ለተቋማቱ ምስጋና እና ዕውቅና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 12/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#በብድር_ዋስትና ፈንድ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ተሞክሮ
በርካታ ኢንተርፕራይዞች ህልማቸውን እውን ለማድረግ ትልቁ ፈተና የመነሻ ካፒታል ነው፡፡ ይህንን የተገነዘበው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከአንድ ማዕከል ጀምሮ በሚደረግ ልየታ እና ክትትል በትክክል ወደ ሥራ ተሰማርተው ለመቀየር ፍላጎት ላላቸው ኢንተርፕራይዞች የፋይንስ ችግራቸውን ለመፍታት አዲስ ስርዓት ተግባራዊ አድርጓል፡፡
ይህንን አዲስ አሰራር የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከዘርፉ ተቋማት ጋር እያካሄደ በሚገኘው የምክክር መድረክ ላይ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተሞክሮውን አጋርተዋል፡፡
እንደ አቶ ሮቤል ገለጻ ማንኛውም ኢንተርፕራይዝ እንደሚያደርገው 20 በመቶ ኢንተርፕራይዙ በማይክሮ ፋይናንስ እንዲቆጥብ በማድረግ ቀሪ 10 በመቶ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋሙ እና ቀሪ 70 በመቶ መንግስት ለማይክሮ ፋይናንስ ገንዘቡ ገቢ በማድረግ የብድር ዋስትና በመስጠት ኢንተርፕራይዞቹ ብድር አግኝተው ወደ ሥራ የሚገቡበት ሁኔታ ተመቻችቶላቸዋል፡፡
ለአንድ ኢንተርፕራይዝ እስከ 500ሺህ ብር ብድር የሚሰጥ ሲሆን በሩብ አመቱ 8.4 ሚሊዮን ብር በዋስትና ፈንድ አማካኝነት ለኢንተርፕራይዞች ብድር ተመቻችቷል፡፡
መረጃው:- የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተግባራት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ
በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት በሙሉ የ2016 ዓ.ም ስልጠና ዘመን የሰልጣኞች ቅበላ የመግቢያ ነጥብ ማሳወቅን ይመለከታል፤
ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መለቀቅን ተከትሎ በየአመቱ ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ገብተው መሰልጠን ለሚፈልጉ ሰልጣኞች የመግቢያ ነጥብ እየተዘጋጀ የሚላክ መሆኑ ይታወቃል፤
በመሆኑም በ2016 የስልጠና ዘመን በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚገቡ ሰልጣኞችን የመግያ ነጥብ በ12ኛ ክፍል ውጤታቸው መሰረት ተዘጋጅቶ ተልኮላችኋል፤
በዚህም ከህዳር 12 ቀን እስከ ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ የሰልጣኝ ቅበላው መጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲፈጸምና ከታህሳስ 1 ቀን እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ በ15 ቀን ውስጥ የሰልጣኝ ቅበላ መረጃው በዲፓርትመንት፣ በሙያ፣ ዓይነትና በደረጃ ተዘጋጅቶ በሶፍትና በሃርድ ኮፒ ለድሬዳዋ አስተዳደር ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ገቢ እንዲደረግ ያሳውቃል፡፡
የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
