The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Відкрити в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Показати більше3 299
Підписники
+624 години
+137 днів
+9130 день
Архів дописів
በቤጊ-ዳቡስ የቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ፕሮጀክት ሥር የሚገኙ የበርታና ጉአማ ቋንቋዎች፤ በቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም(Oral Bible Translators) የተሰሩ የአዳም፣ የኖህና የዮሴፍ ታሪኮችን ወደ ፅሁፍ የመቀየር የትርጉም ሂደት (transcription) አዲስ አበባ በሚገኘው የቤተ ክርስቲያኒቱ ብሔራዊ የትርጉም ማስተባበሪ እየተካሄደ ይገኛል።
የቃል የመጽሐፍ ቅዱስ የትርጉም አገልግሎት በይበልጥ በዘመናዊ ትምህርት ያልተደረሰ ማህበረሰብ እና የጽሑፍ ቋንቋ ለሌላቸው የቋንቋ አይነቶች የምንጠቀመው የአተረጓጎም አይነት ነው።
ይህንን የትርጉሞ ሂደት የቤተ ክርስቲያኒቱ የቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም አሰልጣኝ እና የኤክሴጂቲካል አማካሪ አቶ ረቡማ ሽፈራው እያማከሩት ይገኛል። ሂደቱም ለዚህኛው ዙሪ ሶስት ሳምንታትን እንደሚወስድ ይጠበቃል።
* * * * * * * * *
Under the Begi-dabus Oral Bible Translation(OBT) project, the transcription of the Berta and Guwama languages of the Adem, Noah and Joseph stories are taking place at the Church's national translation office in Addis Ababa.
The Oral Bible Translation ministry is a kind of translation used for communities with less literacy and no written Alphabet.
The Church's OBT trainer and exegetical advisor, Mr Rebuma Shiferaw is facilitating the process. The process is expected to take three weeks in this round.
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ታቦር ኢቫንጄሊካል ኮሌጅ በሥነ-መለኮት የትምህርት መሥክ ያሰለጠናቸውን 47 ተማሪዎችን አስመርቋል
* * * * * *
መንፈሳዊ ኮሌጁ በመደበኛ፣ በማታ እና በክረምት መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 21 ተማሪዎችን በሚስዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እና በመደበኛና በርቀት መርሃ ግብሮች በሚስዮሎጂ በዲፕሎማ ያሰለጠናቸውን 21 ተማሪዎችን አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱም ላይ የኮሌጁ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ እያሱ ጠጊቾ እና የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢና የደቡብ ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ ወልዴ አየለ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች የማበረታቻ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
የታቦር ኢቫንጄሊካል ኮሌጅ በ1968 ዓ.ም የሰርቲፊኬት ፕሮግራም በመስጠት የመጽሐፍ ቅዱስ ት/ቤት ሆኖ የተቋቋመ ሲሆን በደርግ መንግስት ተወርሶ አገልግሎት መስጠት ካቆመባቸው ዓመታት ባሻገር በርካታ ቲኦሎጂያንን ያፈራ ቀደምት የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ-መለኮት ተቋም ነው።
ከኮሌጁም ዲን አቶ ጎዴቦ ጎበና ለመረዳት እንደተቻለው ኮሌጁ በአሁኑ ሰዓት በማሰልጠን ላይ ከሚገኘው የዲፕሎማና ዲግሪ ፕሮግራሞች በተጨማሪ በቀጣይ አመት በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ለመረዳት ተችሏል።
#የሐዘን_መግለጫ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት እና በተለያዩ ሥራ ክፍሎች በክርስቲያናዊ ትህትና፤ በትጋት እና በታማኝነት ሲያገለግሉ የቆዩት ወ/ሮ ሳራ ኡላ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወዳገለግሉት እና ወደ ሚወዱት ጌታ ተሰብስበዋል።
ወ/ሮ ሳራ ኡላ ውልደታቸው በምዕራብ ኢትዮጵያ (ቀለም ወለጋ ዞን) ደምቢዶሎ ከተማ በ1960 ዓ.ም ሲሆን ትምህርታቸውን በቤተል ወንጌላዊት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትለዋል። በቤተ ክርስቲያኒቱም አገልግሎታቸውን በወጣትነት እድሜያቸው በ1980 ዎቹ መጀመሪያ በቤተል ሲኖዶሶች ማስተባበሪያ የጀመሩ ሲሆን ቀጥለው ወደ ዋናው ጽሕፈት ቤተ በመምጣት በመጨረሻ ሲያገለግሉበት የነበረውን የፕሬዚዳንቱን ቢሮ ጨምሮ በተለያዩ ክፍሎች አገልግሎታቸውን ላለፉት 35 ዓመታትና ከዚያም በላይ ያለ ምንም ቁጥብነት አበርክተዋል።
ወ/ሮ ሳራ ከዚህም በተጨማሪ በአባልነት ባገለገሉበት ማህበረ ምዕመናን በካየር አገልግሎት፣ በቤተ ክርስቲያን ሽማግሌነት እና የእርሳቸውን አስተዋፆ በሚፈልጉ ሥፍራዎች ሁሉ በምሳሌነት ማገልግላቸው የህይወት ታሪካቸው ምስክርነት ይገልጻል። በግል ህይወታቸውም ባለ ትዳር እና የሶስት ልጆች እናት ነበሩ።
የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና መላው የዋናው ጽሕፈት ቤቱ ሰራተኞች በህልፈተ ሞታቸው የተሰማንን ሀዘን እየገለጽን ለውድ ባለቤታቸው፣ ለልጆቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ፍጽም የሆነ መጽናናትን እንመኛለን፤ የሃዘናቸው ተካፋይ መሆናችንን እንገልጻለን።
እግዚአብሔር ለሁላችንም መጽናናቱን ይስጠን።
* * ***
#Ibsa_gaddaa
Waajjira olaanaa Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itiyoophiyaa fi kutaalee adda addaa keessaa gad of qabuun, ciminaan, amanamummaa Kiristaanummaadhaan tajaajilaa kan turte Aadde Saaraa Ulaa dhukkuba isheef yaala fayyaa argachaa osoo jirtuu gara Gooftaa tajaajilaa turaani fi jaallatanitti sassabamaniiru.
Aadde Saaraa Ulaan bara 1960 Lixaa Itiyoophiyaa (Godinaa Qeleem Wallagaa) magaalaa Dambidollo keessatti kan dhalatan yoo ta’u, mana barumsaa sadarkaa lammaffaa Warra Wangeelaa Beetel baratani. Jalqaba bara 1980'moota umurii dargagummaa isaanitti waldaa keessatti tajaajila isaani Sinodoosii Beetel qindeessuudhaan, achiis gara waajjira guddichaatti kan dhufan yoo ta’u, dhuma irratti Waajjira Pirezidaantii keessatti tajaajilaa kan turan yoo ta’u, waggoota 35 darbaniif fi sanaa ol nuffii tokko malee tajaajilaa turaani.
Aadde Saaraan miseensa waldaa ta'udhaan gumii faarfannaa keessaa, jaarsummaa waldaa kiristaanaa fi bakka gumaachi isaani barbaachisu hundatti fakkeenya ta'uudhaan tajaajilaniiru. Jireenya dhuunfaa isaani keessaatti immoo gaa'ela kan qabanii fi haadha ijoollee sadii turaani.
Gaggeessitoonni waldaa Kiristaanaatti fi hojjettoonni waajjira olaanaa hundi Abbaa warraa isaani jaallatamaa, ijoollotaa fi hiriyyoota isaanif boqochuu isaaniitti gadda guddaa nutti dhaga’ame ibsinaa.
Waaqayyo hunda keenyaaf jajjabina nuuf haa kennu.
#የሐዘን_መግለጫ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት እና በተለያዩ ሥራ ክፍሎች በክርስቲያናዊ ትህትና፤ በትጋት እና በታማኝነት ሲያገለግሉ የቆዩት ወ/ሮ ሳራ ኡላ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወዳገለግሉት እና ወደ ሚወዱት ጌታ ተሰብስበዋል።
ወ/ሮ ሳራ ኡላ ውልደታቸው በምዕራብ ኢትዮጵያ (ቀለም ወለጋ ዞን) ደምቢዶሎ ከተማ በ1960 ዓ.ም ሲሆን ትምህርታቸውን በቤተል ወንጌላዊት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትለዋል። በቤተ ክርስቲያኒቱም አገልግሎታቸውን በወጣትነት እድሜያቸው በ1980 ዎቹ መጀመሪያ በቤተል ሲኖዶሶች ማስተባበሪያ የጀመሩ ሲሆን ቀጥለው ወደ ዋናው ጽሕፈት ቤተ በመምጣት በመጨረሻ ሲያገለግሉበት የነበረውን የፕሬዚዳንቱን ቢሮ ጨምሮ በተለያዩ ክፍሎች አገልግሎታቸውን ላለፉት 35 ዓመታትና ከዚያም በላይ ያለ ምንም ቁጥብነት አበርክተዋል።
ወ/ሮ ሳራ ከዚህም በተጨማሪ በአባልነት ባገለገሉበት ማህበረ ምዕመናን በካየር አገልግሎት፣ በቤተ ክርስቲያን ሽማግሌነት እና የእርሳቸውን አስተዋፆ በሚፈልጉ ሥፍራዎች ሁሉ በምሳሌነት ማገልግላቸው የህይወት ታሪካቸው ምስክርነት ይገልጻል። በግል ህይወታቸውም ባለ ትዳር እና የሶስት ልጆች እናት ነበሩ።
የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና መላው የዋናው ጽሕፈት ቤቱ ሰራተኞች በህልፈተ ሞታቸው የተሰማንን ሀዘን እየገለጽን ለውድ ባለቤታቸው፣ ለልጆቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ፍጽም የሆነ መጽናናትን እንመኛለን፤ የሃዘናቸው ተካፋይ መሆናችንን እንገልጻለን።
እግዚአብሔር ለሁላችንም መጽናናቱን ይስጠን።
* * ***
#Ibsa_gaddaa
Waajjira olaanaa Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itiyoophiyaa fi kutaalee adda addaa keessaa gad of qabuun, ciminaan, amanamummaa Kiristaanummaadhaan tajaajilaa kan turte Aadde Saaraa Ulaa dhukkuba isheef yaala fayyaa argachaa osoo jirtuu gara Gooftaa tajaajilaa turaani fi jaallatanitti sassabamaniiru.
Aadde Saaraa Ulaan bara 1960 Lixaa Itiyoophiyaa (Godinaa Qeleem Wallagaa) magaalaa Dambidollo keessatti kan dhalatan yoo ta’u, mana barumsaa sadarkaa lammaffaa Warra Wangeelaa Beetel baratani. Jalqaba bara 1980'moota umurii dargagummaa isaanitti waldaa keessatti tajaajila isaani Sinodoosii Beetel qindeessuudhaan, achiis gara waajjira guddichaatti kan dhufan yoo ta’u, dhuma irratti Waajjira Pirezidaantii keessatti tajaajilaa kan turan yoo ta’u, waggoota 35 darbaniif fi sanaa ol nuffii tokko malee tajaajilaa turaani.
Aadde Saaraan miseensa waldaa ta'udhaan gumii faarfannaa keessaa, jaarsummaa waldaa kiristaanaa fi bakka gumaachi isaani barbaachisu hundatti fakkeenya ta'uudhaan tajaajilaniiru. Jireenya dhuunfaa isaani keessaatti immoo gaa'ela kan qabanii fi haadha ijoollee sadii turaani.
Gaggeessitoonni waldaa Kiristaanaatti fi hojjettoonni waajjira olaanaa hundi Abbaa warraa isaani jaallatamaa, ijoollotaa fi hiriyyoota isaanif boqochuu isaaniitti gadda guddaa nutti dhaga’ame ibsinaa.
Waaqayyo hunda keenyaaf jajjabina nuuf haa kennu.
ለሶስት አገልጋዮች የቅስና ሹመት ተሰጠ
_ _ _ _
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ሰሜን ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለቃሉ እና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ ለሶስት አገልጋዮች የቅስና ሃላፊነት ተሰጥቷል።
የቅስና ሃላፊነት የመስጠት ስነ ሥርዓቱ ዛሬ ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በከሚሴ ማህበረ ምዕመናን የተካሄደ ሲሆን አገልጋዮቹም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዘዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቅስና ሃላፊነታቸውን ተቀብለዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ታሪኩ ቶሎሳ፣ የወንጌልና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ዶ/ር ለሊሳ ዳንኤልን ጨምሮ የሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት እና አመራሮች፤ የኢሊባቡር ቤቴል ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት በስፍራው በመገኘት ለእጩ ቀሳውስቱ እጅ በመጫን ፀልየዋል።
በሰሜን ኢትዮጵያ እየሰፋ ስላለው የወንጌል አገልግሎት፤ ለቃሉ፣ ለእረኝነተና የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ስለተጠሩት አገልጋዮች የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን።
* * * * * * * * *
An ordination of three ministers has taken place
_ _ _ _
In the Ethiopian Evangelical Church Mekane, North Central Ethiopia Synod, three ministers are ordained to help with the service of the Word and Sacrament.
The service took place today, 22 June 2024 at Kemise Congregation, and the ministers received the authority of thier priesthood from the Church's president, Rev. Dr. Yonas Yigezu.
Vice president of the Church, Rev. Dr. Tariku Tolosa, Director of the Department of Mission and Theology of the Church, Rev. Dr. Lalisa Daniel, President of the synod and it's management, Ilubabur Betel Synod president, prayed for the newly ordained minister laying hand.
We thank God for the mission work expanding in the Northern part of Ethiopian and the newly called minister for service of the Word and Sacrament with the pastoral ministry.
#Hundinuu_Macaafa_Qulqulluuf
Fiigichaa daandii irraa magaala Bishooftuu
#ሁሉም_ለመጽሐፍ_ቅዱስ የጎዳና ላይ ሩጫ ቢሾፍቱ ከተማ
#All_for_the_Bible great run, Bishoftu city
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
