The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Открыть в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Больше3 315
Подписчики
+624 часа
+197 дней
+10430 день
Архив постов
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አመታዊው የልጆች እና ወጣቶች አገልጋዮች የህብረት: የስልጠና እና የምክክር ጊዜ በጉዲና ቱምሳ ሁለንተናዊ የስልጠና ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል::
በምክክሩም ከቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች እና ሥራ ክፍሎች የተወጣጡ የአገልግሎቱ መሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ::
የቤተክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ በምክክሩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ ልጆችን እና ወጣቶችን የእግዚአብሔርን ቃል እና የቤተ ክርስቲያኒቱን መሰረተ እምነት አስጠብቆ፣ ጊዜውንና ትውልዱን በሚመጥን መልኩ ማሳደግ እና ማብቃት አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ለመሪዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ወንድማገኝ ኡዴሳ ለአመታዊው የምክክር እና የስልጠና መርሃግብሩ ለመሪዎቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ፤ ይህ ጊዜ በጉጉት የሚጠበቅ ጊዜ መሆኑን በማንሳት መሪዎቹ በቆይታቸው፤ ባሳለፉት የአገልግሎት አመት ስላጋጠማቸው ተግዳሮቶችና ፈተናዎች የሚመክሩበት፣ ስላሉ መልካም ዕድሎችና ስኬቶች የልምድ ልውውጦችን የሚያደርጉበት እና በየሲኖዶሶቻቸውና የሥራ ክፍላቸው ስለሚኖረው ቀጣይ አገልግሎት ከስልጠናው እና ከምክክሩ አዳዲስ ስልቶችን እና ሃሳቦችን የሚሰንቁበት እንደሚሆን ገልፀዋል።
ከምክክሩ በመቀጠል የአገልግሎቱ ዳይሬክተሮችን እና ከየሲኖዶሱ የተወከሉ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት በጎ ፈቃድ አምባሳደሮችን ያሳተፈ ወጣቶችን ለመሪነት የማሳደግ ስልጠና የሚካሄድ ይሆናል።
Join us for a summer of creativity, growth, and fun at Mekane Yesus Seminary's Summer Camp for Kids! From music to media, let their spirits soar and imaginations run wild!
#SummerCamp #Inspire #Grow
Creative Potential at Mekane Yesus Seminary!
Join us from July 1-4 for an inspiring journey through music, film, and media. Whether you're a aspiring artist, a passionate musician, or looking to ignite your child's creativity, we have something for everyone!
Enroll now and let your talents shine!
#MekaneYesusSeminary #MusicAndMedia #CreativeJourney
በቤጊ-ዳቡስ የቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ፕሮጀክት ሥር የሚገኙ የበርታና ጉአማ ቋንቋዎች፤ በቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም(Oral Bible Translators) የተሰሩ የአዳም፣ የኖህና የዮሴፍ ታሪኮችን ወደ ፅሁፍ የመቀየር የትርጉም ሂደት (transcription) አዲስ አበባ በሚገኘው የቤተ ክርስቲያኒቱ ብሔራዊ የትርጉም ማስተባበሪ እየተካሄደ ይገኛል።
የቃል የመጽሐፍ ቅዱስ የትርጉም አገልግሎት በይበልጥ በዘመናዊ ትምህርት ያልተደረሰ ማህበረሰብ እና የጽሑፍ ቋንቋ ለሌላቸው የቋንቋ አይነቶች የምንጠቀመው የአተረጓጎም አይነት ነው።
ይህንን የትርጉሞ ሂደት የቤተ ክርስቲያኒቱ የቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም አሰልጣኝ እና የኤክሴጂቲካል አማካሪ አቶ ረቡማ ሽፈራው እያማከሩት ይገኛል። ሂደቱም ለዚህኛው ዙሪ ሶስት ሳምንታትን እንደሚወስድ ይጠበቃል።
* * * * * * * * *
Under the Begi-dabus Oral Bible Translation(OBT) project, the transcription of the Berta and Guwama languages of the Adem, Noah and Joseph stories are taking place at the Church's national translation office in Addis Ababa.
The Oral Bible Translation ministry is a kind of translation used for communities with less literacy and no written Alphabet.
The Church's OBT trainer and exegetical advisor, Mr Rebuma Shiferaw is facilitating the process. The process is expected to take three weeks in this round.
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ታቦር ኢቫንጄሊካል ኮሌጅ በሥነ-መለኮት የትምህርት መሥክ ያሰለጠናቸውን 47 ተማሪዎችን አስመርቋል
* * * * * *
መንፈሳዊ ኮሌጁ በመደበኛ፣ በማታ እና በክረምት መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 21 ተማሪዎችን በሚስዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እና በመደበኛና በርቀት መርሃ ግብሮች በሚስዮሎጂ በዲፕሎማ ያሰለጠናቸውን 21 ተማሪዎችን አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱም ላይ የኮሌጁ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ እያሱ ጠጊቾ እና የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢና የደቡብ ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ ወልዴ አየለ ተገኝተው ለተመራቂ ተማሪዎች የማበረታቻ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
የታቦር ኢቫንጄሊካል ኮሌጅ በ1968 ዓ.ም የሰርቲፊኬት ፕሮግራም በመስጠት የመጽሐፍ ቅዱስ ት/ቤት ሆኖ የተቋቋመ ሲሆን በደርግ መንግስት ተወርሶ አገልግሎት መስጠት ካቆመባቸው ዓመታት ባሻገር በርካታ ቲኦሎጂያንን ያፈራ ቀደምት የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ-መለኮት ተቋም ነው።
ከኮሌጁም ዲን አቶ ጎዴቦ ጎበና ለመረዳት እንደተቻለው ኮሌጁ በአሁኑ ሰዓት በማሰልጠን ላይ ከሚገኘው የዲፕሎማና ዲግሪ ፕሮግራሞች በተጨማሪ በቀጣይ አመት በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ለመረዳት ተችሏል።
#የሐዘን_መግለጫ
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ዋና ጽሕፈት ቤት እና በተለያዩ ሥራ ክፍሎች በክርስቲያናዊ ትህትና፤ በትጋት እና በታማኝነት ሲያገለግሉ የቆዩት ወ/ሮ ሳራ ኡላ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ወዳገለግሉት እና ወደ ሚወዱት ጌታ ተሰብስበዋል።
ወ/ሮ ሳራ ኡላ ውልደታቸው በምዕራብ ኢትዮጵያ (ቀለም ወለጋ ዞን) ደምቢዶሎ ከተማ በ1960 ዓ.ም ሲሆን ትምህርታቸውን በቤተል ወንጌላዊት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተከታትለዋል። በቤተ ክርስቲያኒቱም አገልግሎታቸውን በወጣትነት እድሜያቸው በ1980 ዎቹ መጀመሪያ በቤተል ሲኖዶሶች ማስተባበሪያ የጀመሩ ሲሆን ቀጥለው ወደ ዋናው ጽሕፈት ቤተ በመምጣት በመጨረሻ ሲያገለግሉበት የነበረውን የፕሬዚዳንቱን ቢሮ ጨምሮ በተለያዩ ክፍሎች አገልግሎታቸውን ላለፉት 35 ዓመታትና ከዚያም በላይ ያለ ምንም ቁጥብነት አበርክተዋል።
ወ/ሮ ሳራ ከዚህም በተጨማሪ በአባልነት ባገለገሉበት ማህበረ ምዕመናን በካየር አገልግሎት፣ በቤተ ክርስቲያን ሽማግሌነት እና የእርሳቸውን አስተዋፆ በሚፈልጉ ሥፍራዎች ሁሉ በምሳሌነት ማገልግላቸው የህይወት ታሪካቸው ምስክርነት ይገልጻል። በግል ህይወታቸውም ባለ ትዳር እና የሶስት ልጆች እናት ነበሩ።
የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና መላው የዋናው ጽሕፈት ቤቱ ሰራተኞች በህልፈተ ሞታቸው የተሰማንን ሀዘን እየገለጽን ለውድ ባለቤታቸው፣ ለልጆቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው ፍጽም የሆነ መጽናናትን እንመኛለን፤ የሃዘናቸው ተካፋይ መሆናችንን እንገልጻለን።
እግዚአብሔር ለሁላችንም መጽናናቱን ይስጠን።
* * ***
#Ibsa_gaddaa
Waajjira olaanaa Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itiyoophiyaa fi kutaalee adda addaa keessaa gad of qabuun, ciminaan, amanamummaa Kiristaanummaadhaan tajaajilaa kan turte Aadde Saaraa Ulaa dhukkuba isheef yaala fayyaa argachaa osoo jirtuu gara Gooftaa tajaajilaa turaani fi jaallatanitti sassabamaniiru.
Aadde Saaraa Ulaan bara 1960 Lixaa Itiyoophiyaa (Godinaa Qeleem Wallagaa) magaalaa Dambidollo keessatti kan dhalatan yoo ta’u, mana barumsaa sadarkaa lammaffaa Warra Wangeelaa Beetel baratani. Jalqaba bara 1980'moota umurii dargagummaa isaanitti waldaa keessatti tajaajila isaani Sinodoosii Beetel qindeessuudhaan, achiis gara waajjira guddichaatti kan dhufan yoo ta’u, dhuma irratti Waajjira Pirezidaantii keessatti tajaajilaa kan turan yoo ta’u, waggoota 35 darbaniif fi sanaa ol nuffii tokko malee tajaajilaa turaani.
Aadde Saaraan miseensa waldaa ta'udhaan gumii faarfannaa keessaa, jaarsummaa waldaa kiristaanaa fi bakka gumaachi isaani barbaachisu hundatti fakkeenya ta'uudhaan tajaajilaniiru. Jireenya dhuunfaa isaani keessaatti immoo gaa'ela kan qabanii fi haadha ijoollee sadii turaani.
Gaggeessitoonni waldaa Kiristaanaatti fi hojjettoonni waajjira olaanaa hundi Abbaa warraa isaani jaallatamaa, ijoollotaa fi hiriyyoota isaanif boqochuu isaaniitti gadda guddaa nutti dhaga’ame ibsinaa.
Waaqayyo hunda keenyaaf jajjabina nuuf haa kennu.
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
