The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
Відкрити в Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
Показати більше3 308
Підписники
+324 години
+157 днів
+9130 день
Архів дописів
የቤተ ክርስቲያኒቱ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም እና የቅዱሳት መጻሕፍት አጠቃቀም አመታዊ ኮንፍረንስ ተካሄደ
የ6ተኛው ዙር ኮንፍረንስ ከሁሉም የቋንቋ ትርጉም ቢሮዎች የመጡ ተርጓሚዎች እና ድጋፍ ሰጪዎች ባሳተፈ መልኩ “ትርጉም ለሁለንተናዊ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 1-3 ቀን 2018 ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም አገልግሎት ክፍል በሃገር አቀፍ ደረጃ 19 በሚሆኑ ቋንቋዎች የትርጉም አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ የአገልግሎቱ ብሔራዊ አስተባባሪ ቄስ ሰለሞን ሀይሌ ገልጸዋል። የትርጉሙም ሥራዎቹ በጽሁፍ፣ በቃል፣ በትረካ እና በሌሎች መንገዶች እየተሰሩ ለአገልግሎት እንደሚቀርቡ አስተባባሪው ጨምረው ገልጸዋል።
መርሃ ግብሩን በኦፊሴል በከፈቱበት ወቅት መጽሐፍ ቅዱስ የሚስዮን አገልግሎት መሳሪያ እንደሆነ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሚስዮን እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ የተናገሩ ሲሆን ለወንጌል መስፋፋት የትርጉም አገልግሎት አስተዋጽኦን በማስታወስ ተርጓሚዎች አገልግሎታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አበረታተዋል።
ለሶስት ተከታታይ ቀናት በቆየው ኮንፍረንስ "ትርጉም እና ሚስዮን"፣ " የትርጉም አገልግሎት እና አጋርነት"፣ "አርቲፊሻል ኢንተለደንስ እና የትርጉም አገልግሎት" በሚሉ እና በርካታ አርዕስቶች ዙሪያ ፅሁፎች የቀረቡ ሲሆን ተሳታፊዎች በውይይት ሀሳቦችን አዳብረዋል።
የኮንፍረንሱም ተሳታፊዎች ያሳለፏቸው የትምህርት፣ የምክክር እና የአንድነት ጊዜዎች በብዙ እንደጠቀማቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የካምፖስ አገልግሎት መሪዎች አውደ ጥናት ተካሄደ።
በቤተ ክርስቲያኒቱ የካምፓስ አገልግሎት በተዋቀሩ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ከሚካሄድባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ከመጡ የአገልግሎቱ መሪዎች ጋር ከጥር 20-21/20218 የሁለት ቀናት አውደ ጥናት በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የሥልጠና ማዕከል ተካሂዷል።
በአውደ ጥናቱም ላይ በተለያዩ አርዕስቶች ዙሪያ ጽሑፎች ቀርበዋል። ከተማሪ ህብረት መሪዎችም ጋር ባጋጠሟቸው ተግዳሮቶች፤ ከተቀባይ ማኀበራነ ምዕመናን ጋር ባሉ ግንኙነቶች እና ቀጣይ የአገልግሎቱ አቅጣጫዎች ዙሪያ ምክክር መካሄዱን የካምፖስ አገልግሎትና የከተማ ወንጌል ማዳረስ ዋና ክፍል አስተባባሪ ቄስ ወርቁ ኤባ ገልጸዋል።
በማጠቃለያውም የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮ እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ቄስ ጥላዬ ከበደ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ወጣቶችን እና ልጆችን አቅፋ የማታገለግል ቤተ ክርስቲያን ውጤታ መሆን እንደማትችል ገልጸዋል። አክለውም በአውደ ጥናቱ የተካፈሉ የህብረቶቹ መሪዎች ብዙ ሺህ ወጣቶችን ወክለው በዚህ እንደተገኙ በማስገንዘብ በስልጠና እና በውይይት ያዳበሯቸውን ሀሳቦች ተግባራዊ ለማድረግ እንዲተጉ አሳስበዋል።
አገልግሎቱ በዋነኛነት የሚመለከተው መምሪያም አስፈላጊ በሆኑ ጉዲዮች ሁሉ ድጋፍ ለማድረግ ዳይሬክተሩ ቃል የገቡ ሲሆን ተለታሳታፊ መሪዎች የመጽሐፍ ስጦታ አበርክተዋል።
የቤተ ክርስቲያኒቱ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሉተራን አስተምህሮ ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ ለማጎልበት የሚረዱ ሥልጠናዎችን በአካል እና በርቀት መስጠት የሚያስችሉ ፕሮራሞቻቸውን ከሉተራን ሀወር ሚኒስትሪ የመጡ አገልጋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
#ተዘጋጅተናል?
ዓመታዊው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሚስዩን ቀን በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን በነገው ዕለት ጥር 17 ቀን 2018 በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድምቀት ይከበራል።
"ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ መሥራት ይገባኛል" ዮሐንስ 9፥4
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ ደቡብ ሲኖዶስ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን ቅ/ጽ ቤት ከአጋር ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን በጌዴኦ ዞን ቡሌና ራጴ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች ያስገነባውን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አስመርቋል ።
የመሬት ናዳ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎች እየተደረጉ መሆናቸው የገለፁት ፕሬዝዳንቱ በቀጣይም ሌሎችን ድጋፎች ለማድረግ ዝግጁቶች እንዳሉ አመላክተዋል።
የጌዴኦ ዞን አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት ሀላፊ ተድላ ጌታሁን(ዶ/ር) ሲኖዶሱ የተፈጥሮ አደጋው ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎችን እያደረገ መቆየቱን ጠቅሰው አሁንም ለተጎዱ ወገኖች ለተገነባው የንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አመሥግነዋል።
ህብረተሰቡን ወደ ተሰራላቸው መኖሪያ ቤት በአጭር ጊዜ ለማስገባት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውንም አክለዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ ደቡብ ሲኖዶስ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን ቅ/ጽ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተድላ አረጋ በቡሌና ራጴ ወረዳ የመሬት ናዳ አደጋ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መቆየታቸውን ተናግረው በራጴና ቡሌ ወረዳ ለተፈናቀሉ ወገኖች 5 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተገንብቶ ለህብረተሰቡ ማስረከባቸውን አሰረድተዋል።
በቀጣይም ያሉትን ክፍተቶች በመለየት ድጋፉን ለማስቀጠል የተለያዩ ፕሮጀክቶች መታቀዳቸውንም ጠቁመዋል።
ዘገባው የጌዲዮ ቲቪ ነው። #Gedio #Tv
ቀን 15/05/2018 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አለም አቀፍ የሚስዮን ሳምንታት ክብረ በዓል በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅሮች፣ ሲኖዶሶች እና ማኀበራነ ምዕመናን በወንጌል ሥርጭት፣ በኮንፍራንስ እና ሴሚናሮች እየተከበረ ይገኛል።
የበዓሉም ማጠቃለያው የፊታችን እሁድ ጥር 17 ቀን 2018 በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን ስለ ሚስዮን አገልግሎት በመፀለይ፣ በማስተማር፣ ለአገልግሎቱ የፍቅር ሥጦታ በማሰባሰብ እና በሌሎች በርካታ መርሃ ግብሮች በታላቅ ድምቀት የሚከበር ይሆናል።
"ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ መሥራት ይገባኛል" ዮሐንስ 9፥4
🎬✨ የፊልምና የሚዲያ ሰርቲፊኬት መርሐ ግብር የማታ ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን።
✨🎶 የሙዚቃ ሰርቲፊኬት መርሐ ግብር የማታ ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን።
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
