ar
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

الذهاب إلى القناة على Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

إظهار المزيد
3 291
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+147 أيام
+9930 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ ደቡብ ሲኖዶስ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን ቅ/ጽ ቤት ከአጋር ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን በጌዴኦ ዞን ቡሌና ራጴ ወረዳ በተፈጥሮ አደጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች ያስገነባውን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አስመርቋል ። ‎ ‎ የመሬት ናዳ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎች እየተደረጉ መሆናቸው የገለፁት ፕሬዝዳንቱ በቀጣይም ሌሎችን ድጋፎች ለማድረግ ዝግጁቶች እንዳሉ አመላክተዋል። ‎ ‎የጌዴኦ ዞን አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት ሀላፊ ተድላ ጌታሁን(ዶ/ር) ሲኖዶሱ የተፈጥሮ አደጋው ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ሰብአዊ ድጋፎችን እያደረገ መቆየቱን ጠቅሰው አሁንም ለተጎዱ ወገኖች ለተገነባው የንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አመሥግነዋል። ‎ ‎ህብረተሰቡን ወደ ተሰራላቸው መኖሪያ ቤት በአጭር ጊዜ ለማስገባት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውንም አክለዋል። ‎ ‎የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ ደቡብ ሲኖዶስ ልማትና ማህበራዊ አገልግሎት ኮሚሽን ቅ/ጽ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ተድላ አረጋ በቡሌና ራጴ ወረዳ የመሬት ናዳ አደጋ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መቆየታቸውን ተናግረው በራጴና ቡሌ ወረዳ ለተፈናቀሉ ወገኖች 5 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ ንፁህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተገንብቶ ለህብረተሰቡ ማስረከባቸውን አሰረድተዋል። ‎ ‎በቀጣይም ያሉትን ክፍተቶች በመለየት ድጋፉን ለማስቀጠል የተለያዩ ፕሮጀክቶች መታቀዳቸውንም ጠቁመዋል። ‎ ዘገባው የጌዲዮ ቲቪ ነው። #Gedio #Tv ቀን 15/05/2018 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አለም አቀፍ የሚስዮን ሳምንታት ክብረ በዓል በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅሮች፣ ሲኖዶሶች እና ማኀበራነ ምዕመናን በወንጌል ሥርጭት፣ በኮንፍራንስ እና ሴሚናሮች እየተከበረ ይገኛል። የበዓሉም ማጠቃለያው የፊታችን እሁድ ጥር 17 ቀን 2018 በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን ስለ ሚስዮን አገልግሎት በመፀለይ፣ በማስተማር፣ ለአገልግሎቱ የፍቅር ሥጦታ በማሰባሰብ እና በሌሎች በርካታ መርሃ ግብሮች በታላቅ ድምቀት የሚከበር ይሆናል። "ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ መሥራት ይገባኛል" ዮሐንስ 9፥4

🎬✨ የፊልምና የሚዲያ ሰርቲፊኬት መርሐ ግብር የማታ ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን።
🎬✨ የፊልምና የሚዲያ ሰርቲፊኬት መርሐ ግብር የማታ ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን።

✨🎶 የሙዚቃ ሰርቲፊኬት መርሐ ግብር የማታ ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን።

ሁለንተናዊ የልጆችና ታዳጊዎች አገልግሎት ስልጠና በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሀዋሳ ከተማ ተሰጠ 'ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ታዳጊዎቻችን' በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና በማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በሲኖዶሱ ማዕከል ሀዋሳ ከተማ ተሰጥቷል። ስልጠናው የተሰጠው ከሲኖዶሱ ጋር በመተባበር በዋናው ጽ/ቤት የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ በኩል ሲሆን: ከሲኖዶሱ ሰበኮች እና ማ/ምዕመናናት የተወጣጡ መሪዎች እና የልጆችና ወጣቶች አገልጋዮች ተሳትፈዋል:: ከስልጠናው ጎን ለጎን ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚጠቅሙ: ታቅዶ እየተሰራበት ላለው ቤተ መጻህፍትን በእያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን የማስጀመር ራዕይ የሚረዱ የልጆች መጽሐፍ ቅዱሶች: የወጣቶች ማስተማርያ መጽሐፍቶች: ለአገልጋዮች እና ምዕመናን: ለደቀመዛሙርትነት እና ለሌሎች ለቤተክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ የሚረዱ የተለያዩ መጽሐፍቶች በመምሪያው በኩል በድጋፍ መልክ ተሰጥቷቸዋል:: ስልጠናውን የሰጡት የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሣ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት: Rafiki Foundation እና Lutheran Heritage Foundation እና ሌሎችንም በማመስገን : መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ማ/ምዕመናናት: ሴሚናሪዎች: መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በተጨማሪም ቤተክርስቲያኒቱ ባስቀመጠችው አቅጣጫ መሰረት ሲኖዶሱ የልጆች አገልግሎትን በመምሪያ ደረጃ በማደራጀት ቀዳሚ መሆኑን በማንሳት: ስለ ምሳሌያዊ ተግባራቸው አመስግነው ሌሎች ሲኖዶሶችም ይሄን መልካም ልምድ ወስደው በልጆች አገልግሎት ላይ ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ መልዕክት አስተላልፈዋል። በስልጠናው መክፈቻ የተገኙ የሲኖዶሱ ፕረዚዳንት ቄስ ኢያሱ ጠግቾ ስልጠናው የልጆች እና ታዳጊዎችን አገልግሎትን ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ አስፈላጊ እና ወቅቱን ያገናዘበ መሆኑን ገልጸው: ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና መሰረት ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል:: በተቀሩት የቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶችም ተመሳሳይ ስልጠና ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር የሚቀጥል ይሆናል:: === 📷 : Biniam, Alamura Congregation , Hawassa EECMY Children Ministry - MY Sunday School #Hawassa

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምስራች ድምጽ መገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል ፕሮግራም የፎቶ ምልከታ።