The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY
رفتن به کانال در Telegram
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.
نمایش بیشتر3 497
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+157 روز
+11030 روز
آرشیو پست ها
የአዶላ ገናሌ ሲኖዶስ ሶስተኛው መደበኛ ጉባኤ ለቀጣይ ዓራት አመታት ሲኖዶሱን የሚመሩ መሪዎችን መርጧል
* *
በፍፁም መደማመጥ እና መቀባበል የተጠናቀቀው የሲኖዶሱ ጉባኤ ቀጣይ አራት አመታትን ሲኖዶሱን የሚመሩ መሪዎችን በመምረጥ የጉባኤውን ፍፃሜ አድርጓል።
በዚህም መሠረት:-
1- ቄስ ጌሎ ጎሎልቻ የሲኖዶሱ ፕሬዝዳንት
2- ቄስ ደረሰ ኔንቆ የሲኖዶሱ ምክትል ፕሬዚዳንት እና
3- አቶ ረጋሳ ተ/ብርሃን ሎኮ የሲኖዶሱ አቃቤ ንዋይ በመሆን ቀጣይ አራት የአገልግሎት አመታትን ሲኖዶሱን የሚመሩ ይሆናል።
የቤተ ክርስቲያኒቱም ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ የተመረጡትን የሲኖዶሱን መሪዎች ሥለ ተቀበሉት ሀላፊነት እና ተጠያቂነት ቃለ መሀላ አስገብተዋል።
ከተለያዩ ሰበካዎች የመጡ እናቶችም የአከባቢውን የባህል ምግቦች ለጉባኤው የክብር እንግዶች ያቀረቡ ሲሆን በጉጂ ኦሮሞ ባህል መሠረት የቀረቡትን ማዕዶች ጉባኤተኛው ከተቃመሠ በኋላ በፀሎትና በመበራረክ ወደ መጣበት የአገልግሎት ሥፍራ ተጉዟል።
ቤተ ክርስቲያንም ለተመረጡት መሪዎች መካከል ምኞቷን እየገለፀች ለአገልግሎታቸው ሥኬት ትፀልያለች።
ሎሎች ዘገባዎችን ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:-
Facebook - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/
Telegram - https://t.me/EECMYeth
YouTube News- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd
YouTube Education - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አዶላ ገናሌ ሲኖዶስ 3ኛ መደበኛ ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል።
* * ****
መደበኛ ጉባኤው በሻኪሶ ከተማ ከሰኔ 17 - 18 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደ ሲሆን፤ ሲኖዶሱም ባለፉት 4 ዓመታት የሰጠው የወንጌል እና የልማት አገልግሎት በሚመለከት ሰፋፊ ሪፖርቶች ቀርበው ውይይቶች ተደርገዋል። ውሳኔ በሚሹ ጉዳዮችም ላይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
የሲኖዶሱም ፕሬዝዳንት ቄስ ጌሎ ጎሎልቻ በመክፈቻ ንግግራቸው ያለፉት ዓራት አመታት በእግዚአብሔር እርዳታ በተግዳሮቾች መካከል በውጤት የታለፈ የስኬት አመታት መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአሁኑም ሰዓት በሲኖዶሱ ለሚገኘው አገልግሎት በወርድ ፎር ዘ ወርልድ(Word for the World) መሪነት ተተርጉሞ ለአገልግሎት የበቃው የጉጂ አፋን ኦሮሞ ሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ(Kitaaba Woyyicha) ተጠናቆ ለምዕመናን በመሰራጨት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም ከሁለት ዓመታት በላይ የወሰደው እና የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋለ ንዋይ የፈሰሰበት በጉጂ አፋን ኦሮሞ የተዘጋጀው የቅዳሴ መጽሐፍ ካለፈው 1 ዓመት ጀምሮ በሲኖዶሱ ማኀበራነ ምዕመናን ለአምልኮ አገልግሎት መዋሉን በታላቅ ደስታ ገልፀዋል። ለዚህም ከፍተኛ አስተዋጽኦ የወርድ ፎር ዘ ወርልድን፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን የሚስዩንና ቲኦሎጂ መምሪያ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን የፕሬዚዳንት ቢሮ እና መሪዎችን አመስግነዋል።
አያይዘውም በሲኖዶሱ በተሰራው የወንጌል አገልግሎት ባለፉት ዓራት ዓመታት ብቻ ከ95 በላይ ማኀበራነ ምዕመናን የተጨመሩ ሲሆን ለአገልግሎት ተደራሽነት 3 ተጨማሪ ሰበካዎች መቋቋማቸውን ገልጸዋል። በቀረበውም ሪፖርት ላይ እንደተመላከተው በአሁኑ ሰዓት የሲኖዶሱ አባላት ቁጥር ከግማሽ ሚሊዩን ማለፉን ተጠቅሷል።
ሲኖዶሱም ከአገልግሎት ቀጠናው ውጪ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች እና በባህር ማዶ በወንጌልን የማዳረስ የሚስዮን ስራ በመስራት ላይ መሆኑ እና በዚህም አገልግሎት አማካኝነት ከ80 በላይ የስብከተ ወንጌል ጣቢያዎች መቋቋማቸውን ፕሬዝዳንቱ በንግግራቸው አመላክተዋል።
ሲኖዶሱም በአገልግሎት ላይ የሚገኙ የሙሉ ጊዜ አገልጋዩችን አቅም ለመገንባት የመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪን ጨምሮ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ መለኮት ተቋማት አገልጋዮችን በማስተማር ላይ እንደሚገኝ ቄስ ጌሎ ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት ብቻ በሁለተ ዲግሪ፣ በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማ እና ሰርቴፊኬት 96 አገልጋዮች መመረቃቸውን ጠቅሰዋል።
ስለተገኙትም ውጤቶች እግዚአብሔርን አመስግነዋል። በተመሳሳይ መልኩ በአከባቢው የወንጌል አገልግሎት ፋና ወጊ የነበሩ አባቶችን እና ከሲኖዶሱ ምስረታ ጀምሮ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ መሪች እና አገልጋዮች እውቅና ሰጥተዋል።
በሲኖዶሱም 3ተኛ ጉባኤ የተገኙ ከፍተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ከተመሠረተ 8 ዓመታት ብቻ ያስቆጠረው ሲኖዶስ ፈጣን እድገት ማሳየቱን መስክረዋል። ለዚህም የነቃ ተሳትፎ የሲኖዶሱን ምዕመናንን፤ በየደረጃው የሚገኙ የአገልግሎት መዋቅሮችን እና መሪዎችን አመስግነዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ አዶላ ገናሌ ሲኖዶስ 3ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማለዳ በሻኪሶ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
ጉባኤውም ዛሬ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና የጌታ እራትን በጋራ በመካፈል ጅማሬውን ያደረገ ሲሆን ቀጣይ የጉባኤው ተግባራት በተቀመጠላቸው የአጀንዳ ቅደም ተከተል መሠረት እንዲቀጥሉ ተቀምጧል።
በዚህም ጉባኤ ለመካፈል የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዩናስ ይገዙ፣ የአጎራባች ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት የሆኑት ቄስ ደስታ ሐሮ ከደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ እና ጥሪ የተደረገላችው እንዶች በሻኪሶ ከተማ ተገኝተዋል።
በማለዳውም የፀሎት መርሃ ግብር የሲኖዶሱ ፕሬዚዳንት ቄስ ጌሎ ጎሎልቻ የቅዳሴ ሥርዓቱን የመሩ ሲሆን የቤተ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል።
ቀጣይ የሲኖዶሱን ጉባኤና ሌሎች ዘገባዎች ለመከታተል የሚከተሉትን አካውንቶች ፎሎ በማድረግ ይከታተሉ:-
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/share/1GDpuFoseh/
ቴሌግራም - https://t.me/EECMYeth
ዩትዮብ ዜና- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=cPuWOIVvHYDI01nd
ዩትዩብ ትምህርት - https://youtube.com/@mekaneyesus1959?si=0XKpyBECeLaTIZFg
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ5 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ሰጠች።
* * ***
የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በጭረ እና አከባቢው ሲኖዶስ ለ5 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ሰጥታለች።
የቅስሀ ላፊነቱን የሰጡት የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ ሲሆኑ ሰፊ መልዕክት ለምዕመናን አስተላልፈዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱም ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ ለዕለቱ በተመደበው ጥቅስ ላይ ቃለ እግዚአብሔርን አስተምረዋል።
የጭረ እና አከባቢው ሲኖዶስም እራሱን ችሎ ከተቋቋመ አራት አመታትን ብቻ ያስቆጠረ ሲኖዶስ ነው። ይህም በአጭር የአገልግሎት ቆይታው ከአዳዲስ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች መካከል ያስመድበዋል።
ሲኖዶሱም ለቃሉ እና የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት ቀሳውስትን ሲያቀስስ የመጀመሪያው ሲሆን በቀጣይ በሲኖዶሱ ያለውን የእረኝነት አገልግሎት ተደራሽነት ለማስፋት የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ተቋቁሞ አገልጋዮች በትምህርት ላይ መሆናቸውን የሲኖዶሱ ፕሬዝዳንት ቄስ ቦልካ አሰፋ ገልጸዋል።
በቅስና አሰጣጥ መርሃ ግቡሩም የሲኖዶሱ ማኔጅመን፣ የሰበካ ተጠሪዎች፣ የእጩ ቀሳውስት ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ለመከሩ አገልግሎት ታማኝ አገልጋዮችን የጨመረልን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን።
የቅድመ ቅስና ስልጠና ለ5 እጩ ቀሳውስት በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ጭሪ እና አከባቢው ሲኖዶስ ተሰጠ።
ለቅስና አገልግሎት በማኀበረ ምዕመናን ጥሪ ቀርቦላቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን የአገልግሎት ቅድመ ዝግጅት ማሟላታቸው ለተረጋገጠ አምስት እጩ ቀሳውስት እና የትዳር አጋሮቻቸው የቅድመ ቅስና ስልጠና ተሰጥቷል።
ሥልጠናውንም የሰጡት የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ ሲሆኑ የቤተ ክርስቲያኒቱን የቅዳሴ ሥርዓት ቅደም ተከተልና ሥነ መለኮታዊ አንደምታ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን የእምነት አቋሞችና መግለጫዎች፤ የማማከር አገልግሎትና የአባላት ክትትል፤ ማህበራዊ ተሳትፎ እና በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ተዳሰዋል።
ሥልጠናው በዋነኛነት ለእጩ ቀሳውስቱ የተዘጋጀ ቢሆንም ነባር ቀሳውስትም ተሳትፈዋል። ከሲኖዶሱ ጋር በመነጋገር ይህንን መሰል ስልጠና ሰፊ ጊዜ ተወስዶ እንደሚሰጥ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አስታውቀዋል።
ከጭሪና አከባቢው ሲኖዶስ ሰባካዎች፤ እንዲሁም ከሲኖዶሱ ማኀበራነ ምዕመናን ከመጡ መሪዎችና አገልግሎቶች ጋር የምክክር ጊዜ ተካሄደ።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ በጭሪ ሲኖዶስ በመገኘት ከሲኖዶሱ ቄሶች፣ ወንጌላዊያን እና የማኀበራነ ምዕመናን ሽማግሌዎች ጋር መክረዋል።
በምክክሩም ወቅት ፕሬዚዳንቱ በቤተ ክርስቲያቱ ሉተራዊ ማንነት፣ አስተምህሮ፣ ሥርዓተ አምልኮ እና የምዕመናን ጥበቃ ዙሪያ ሰፊ ገለፃ አድርገዋል። አክለውም በቤተ ክርስቲያቱ እየተሸረሸሩ የሚገኙ የአስተምህሮና የልምምድ ጉዳዩችን ከማስተካከል አንጻር ቤተ ክርስቲያኒቱ የፀና አቋም እንዳላት በአጽኖት ተናግረዋል።
ከምክክሩም ባሻገር ፕሬዝዳንቱ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶለሳ ጋር በመሆን በከፍተኛ ወጪ በግንባታ ላይ የሚገኘውን የጭሪ ማኀበረ ምዕመናን የአምልኮ አዳራሽ እና በማህበሩ የሚካሄዱ ገቢ ማስገኛ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተው አበረታተዋል።
በምስራቅ ኢትዮጵያ ላሉት መሪዎች እና የልጆችና ወጣቶች አገልጋዮች ስልጠና ተሰጠ
* * * * * * * * *
'ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን' በሚል ርዕስ ልጆች እና ወጣቶች በሁለንተዊ መልኩ ታንጸው እንዲያድጉ፣ የተፈጠሩበትን ዓላማ ለይተው፣ እግዚአብሔር በውስጣቸው ባስቀመጠው ልዩ የተፈጥሮ ችሎታ እና መንፈሳዊ ጸጋ መልካም ተጽዕኖ ፈጥረው ለትውልድ በረከት እንዲሆኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ከምስራቅ ኢትዮጵያ እና ምዕራብ ሀረርጌ ሰበኮች እና ማ/ምዕመናናት ለተወጣጡ የልጆች እና ወጣቶች አገልጋዮች: ቄሶች እና ወንጌላውያን በዋናው ጽ/ቤት የልጆች እና ወጣቶች መምሪያ በኩል በሀረር ከተማ ስልጠና ተሰጥቷል:: በስልጠናው ለተሳተፉት ሰልጣኞች ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚጠቅሙ: ታቅዶ እየተሰራበት ላለው ቤተመጻህፍትን በእያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን የማስጀመር ራዕይ የሚረዱ የልጆች መጽሐፍ ቅዱሶች: የወጣቶች ማስተማርያ መጽሐፍቶች: እና ለቤተክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ የሚረዱ የተለያዩ መጽሐፍቶች በመምሪያው በኩል በድጋፍ መልክ ተሰጥቷቸዋል::
ስልጠናውን የሰጡት የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሣ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት: 'Rafiki Foundation' fi 'Lutheran Heritage Foundation' እና ሌሎችንም በማመስገን : ተመሳሳይ ስልጠናዎች ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር
በተቀሩት ሲኖዶሶችም እንደሚቀጥል ገልጸዋል::
የሲኖዶሱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት አስተባባሪ ቄስ ደረጀ ገመቹ የልጆች እና ወጣቶችን አገልግሎት ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ ስልጠናው አስፈላጊ እና ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ገልጸው: ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና መሰረት ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል::
- - - - - -
Baha Itoophiyaatti Leenjiin Geggeessitootaa fi Tajaajiltoota Ijoollee fi Dargaggootaatiif kenname
* * * * * * * * *
'Guddinna Hundagaleessa Ijoollee fi Dargaggoota Keenyaaf' mat-duree jedhuun, ijoollee fi dargaggootni keenya guddinni isaanii karaa hundumaan, hunda-galeessa akka ta’uuf, ijoollee fi dargaggootni kaayoo Waaqayyo isaan uumeef adda baafatanee, kennaa fi dandeettii addaa Inni isaaniif kenneen dhiibbaa gaarii uumanii dhalootaaf eebba akka ta'anuuf, geggeessitoota, tajaajiltoota ijoollee fi dargaggootaa, lubootaa fi hojjattoota wangeelaa Sinoodoosii G/galeessa Itoophiyaa, sabakoota fi waldaalee amantootaa baha Itooohiyaatti argamaniif karaa Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa WKWWMYI'tiin magaalaa Hararitti leenjiin kennameera.
Leenjifamtoota leenjii kana irratti hirmaataniif tajaajila ijoollee fi dargaggootaaf kan fayyadan, akkaataa karoorfamee irratti hojjatamaa jiruun Manneen Kitaabaa Waldaa Amantootaa hundumaatti jalqabsiisuuf kan gargaaran, Kitaabni Qulqulluun ijoollee garagaraa, kitaabileen tajaajila dargaggoof ta'an, akkasumas kitaabonni hafuuraa adda addaa barsiisa bu'uura amantii Kiristaanaatiif gargaaran garagaraa karaa qajeelchichaatiin bifa gargaarsaatiin kennameefii jira.
Leenjicha kan kennaman Daarektarri Qajeelcha Tajaajila Ijoollee fi Dargaggootaa WKWWMYI Luba Wondmagegn Udessa, dhaabbilee kitaabota hafuuraa tajaajila ijoollee fi dargaggootaa gargaaran garagaraatiin kan deeggarsa Waldattiif taasisan Dhaabbata Lutheran Heritage Foundation fi Rafiki Foundation galateeffatanii, leenjiin wal fakkaataan sinoodoosota warra hafanitti bifa wal fakkaataan walta’iinsaan kennamuu kan itti fufu ta'uu ibsaniiru.
Qindeessaa Tajaajila Ijoollee fi Dargaggoo Sinodosichaa kan ta'an Lubni Darajjee Gammachuu, tajaajila daa’immanii fi dargaggootaa akka yeroon gaafatutti guddisuuf leenjichi barbaachisaa fi yeroosaa kan eeggate ta'uu ibsaniin booda, leenjifamtootni leenjii fudhatan kana hojiitti akka hiikan cimsanii ergaa dabarsaniiru.
ለሀገር ሰላምና አንድነት መረጋገጥ የእምነት ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ
* **
ይህ የተገለፀው ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ቤተል ሲኖዶስ በሸካ ዞን የኪ ወረዳ የኩቢጦ ሰበካ ጽ/ቤት ግንባታ መሠረተ ድንጋይ በተቀመጠበት ወቅት ነው።
የግንባታውን መሠረተ ድንጋይ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በቴል ሲኖዶስ ፕሬዚዳንት ቄስ አዘነበ ደሰኖ አስቀምጠዋል።
ፕሬዝዳንቱ በስፍራው ባደረጉት ንግግር የእምነት ተቋማት ከመንፈሳዊ ስራዎች ባሻገር ለአካባቢ ተጨማሪ ውበት የሚሰጡ ግንባታዎችን የመገንባት ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል።
ቤተክርስቲያኒቱ የአምልኮ አዳራሾችና የተለያዩ ግንባታዎችን በማካሄድ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን እየሰጠች መሆኑንም ገልጸዋል።
ለሀገር ሰላምና አንድነት እንዲሁም ልማት እንዲረጋገጥ መጸለይና ምዕመናን በተለያዩ የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ እንዲሳተፉ ማስተማርም የቤተ ክርስቲያኒቱ ትልቅ ተግባር ነው ስሉም ገልጸዋል።
በተለይም ያለፈው ሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ አገልጋዮችና ምዕመናን በጸሎት ይተጉ እንደነበር በመግለፅ ለሰፈነው ስላም የአማኞች ሚና ከፍተኛ እንደነበር አስታውሰዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ቤተል ሲኖዶስ ኩቢጦ ፕረስቢተሪ ጸኃፊው ቄስ አባቴ ኃይሌ በበኩላቸው ግንባታውን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እቅድ መያዙን ገልጸው ምዕመናን ፣ባለሃብቶችና ሌሎች ግለሰቦች ድጋፋቸውን እያደረጉ ስለመሆናቸው ተናግረዋል።
ግንባታው በውስጡ የተለያዩ ቢሮዎችንና የመሰብሰቢያ አዳራሽን ያካተተ መሆኑንም ጸኃፊው ገልጸዋል ።
በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ መንፈሳዊ ፕሮግራሞች የተከናወኑ ስሆኑ በዕለቱ ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል ።
በስፍራው የሲኖዶሱ መሪዎችን ጨምሮ አገልጋዮች፣ምዕመናን እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል ።
ዘገባው የሸካ ቴቪ ማሻ
06/10/2018
በተሻለ ተካልኝ
Kabajni ayyaana biyyoolessaa torbee Macaafa Qulqulluu Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesus Itiyoophiyaa waggaa 5ffaan waldaa amantootaa Waldattii hundumatti Waxabajjii 8-14, 2018 qophiilee adda addaatiin ni kabajama.
Kabajni ayyaana bara kanaas mataduree, “Sagalee Waaqayyoo maatii hundumaa keessatti, guyyaa hundumaa” jedhuun kan kabajamu yoo ta’u, tajaajila hiikkaa Macaafa Qulqulluu waldaa kanaan gaggeeffamaa jiruuf kadhannaan ni kadhatama, akkaataa itti fayyadama kaalandara dubbisa Macaafa Qulqulluu leeksikaalii(LBRC) waldaa irratti hubannoo bal’aan ni kennama, itti fufiinsa tajaajilichaaf kennaan ni kennama.
#National_Bible_Week_2026
#Lexical_Bible_Reading_Calendar
