uk
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

Відкрити в Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

Показати більше
3 363
Підписники
Немає даних24 години
+127 днів
+5730 день
Архів дописів
ሁሉን አቀፍ የናቪሽን የሂሳብ አስተዳደር ስልጠና ተሰጠ። * * * * * * የኢትዮጲያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በአስተዳደር እና ፋይናንስ መምሪያ የተዘጋጀው የናቬሽን የሂሳብ አስተዳደር ስልጠና በስኬት ተካሂዷል። በስልጠናውም ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶች እና የጋራ ተቋማት የመጡ የሂሳብ ባለሙያዎች እና የመምሪያ ዳይሬክተሮች ተካፍለዋል። የቤተ ክርስቲያኒቱ የአስተዳደር እና ፋይናንስ መምሪያ ዳይሬክተ ወ/ሮ ሰብለ ገመችስ በመዝጊያ ንግግራቸው የሥልጠናው ዋና አላማ የሂሳብ ባለሙያዎቹ የሂሳብ ነክ መረጃዎችን በአግባቡ እንዲመዘግብ፤ የቁጥጥርና ጊዜውን የጠበቀ ሪፓርቲንግን ክህሎትን እንዲያዳብሩ መሆኑን የገልፀዋል። አያይዘውም የስልጠናውን ውጤት ማረጋገጥ እንዲያስችል ተግራዊ የሶፍትዌር አጠቃቀም ስልጠና መሰጠቱን አክለዋል። ሰልጣኞቹም በስልጠናው ከወሰዱት እውቀት ባሻገር በውይይት እና የጥያቄና መልስ ክፍለ ጊዜ ብዙ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል። በመካነ ኢየሱስ ሴሚናሪዮም ቻፕል በተካሄደው ስልጠና ማጠቃለ ለስልጠናው ተካፋዮች የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምክክር አውደ ጥናት ዛሬ በመካሄድ ላይ ይገኛል። * * *   * * * የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥነ መለኮት አቋም ማስጠበቅ፤ የአምልኮ ሥርዓተ ጥንቃቄ፤ ሐሰተኛ ትምህርቶችን እና ልምምዶችን መከላከል ላይ ያተኮረው የመሪዎች አውደ ጥናት በጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የሥልጣና ማዕከል ባሳለፍነው ዕለት መካሄድ ጀምሯል። በዚህም አውደ ጥናት የሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች፤ ዋና ፀሐፊዎችና የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተሮች እና ከጋራ ተቋማት የመጡ መሪዎች እየተሳተፉበት ይገኛል። አውደ ጥናቱን ያዘጋጀው የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የምክክር አውደ ጥናቱን አላማ የገለፁ ሲሆን ይህንን የጋራ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አገልጋዮች እያጋጠሙ ባሉ ውጫዊ ተፅዕኖዎች እና  ሊደረጉ በሚገቡ ጥንቃቄዎች ዙሪያ የሚመክሩበት ሰፊ እድል እንደሆነ ገልጸዋል። በአውደ ጥናቱ ወቅታዊነትና ጠቀሜታ ዙሪያ አጽንዖት በመስጠት ተሳታፊዎች በትኩረት በመከታተል ግብአት በመስጠት  አስተዋፆ እንዲያደርጉ ፣ እስከ ማህበረ ምዕመናን በማዉረድ የምክክሩ ዉጤቶች እንዲተገበሩ  የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠቅላይ ጸሐፊ ቄስ ዶ/ር ተሾመ አመኑ አሳስበዋል። አዉደ ጥናቱ በተለያዩ ርዕሶች ላይ ከመምሪያዉ ባልደረቦች ለዉይይት መነሻ የሚሆኑ ፁሑፎች የሚቀርቡ ሲሆን  በማለዳውም ክፍለ ጊዜ የቤተ ክርስቲያኒቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ታሪኩ ቶሎሳ "የብልጽግና ወንጌል በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ እያደረሰ ያለዉ ተጽዕኖ" በሚል ርዕስ ሰፊ ጽሑፍ አቅርበዋል። በተያያዘ መልኩ በዚህ አውደ ጥናት ለመካፈል በአሜሪካ ሐገር ኪንታኪ ከተማ ከምትገኘዉ  የሄብሮን ሉተራዊት ማህበረ ምዕመናን የመጡ አገልጋዩች ሰላምታ አቅርበዋል። አውደ ጥናቱም በተዘጋጀለት የፕሮግራም ሰሌዳ እንደሚቀጥል ከመምሪያው ለመረዳት ተችሏል።

የልጆች የክረምት ካምፕ ምዝገባ ላይ ነን!
የልጆች የክረምት ካምፕ ምዝገባ ላይ ነን!

የልጆች የክረምት ካምፕ ምዝገባ ላይ ነን!

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ለ33 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት ሰጠች * * *** የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና የቅዱሳት ሚስጥራዊ አገልግሎት እንዲያግዝ፤ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፤ ማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለ33 አገልጋዮች የቅስ ሀላፊነት ሰጥቷል። ይህም ሥነ-ሥርዓት በሀዋሳ ከተማ ሪፈራል ማህበረ ምዕመናን የተካሄደ ሲሆን የቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልእኮና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ጥላዬ ከበደ የእግዚአብሔርን ቃል ለጉባኤው በማስተማር የቅስና አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓቱን መርተዋል። የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ሰፊ የቆዳ ስፋት በመሸፈን አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲኖዶስ ሲሆን በርካታ ሲኖዶሶችንም አፍርቷል። አዳዲስ ቀሳውስቱም ወደ መጡባቸው ማኀበራነ ምዕመናን ተመልሰው በሚሰጧቸው አገልግሎች በሲኖዶሱ የሚታየውን የቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት አጥረት በጉልህ እንደሚቀንስ ይታመናል። የማዕከላዊ ደቡብ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በአሁኑ ሰዓት በ978 ማኀበራ ምዕምናን እና በርካታ የወንጌል ስብከት ጣቢያዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። የሲኖዶሱም ፕሬዚዳንት ቄስ እያሱ ጠጊቾ በሲኖዶሱ የሚሰጠውን የእረኝነት አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሳደግ አገልጋዮች በሴሚናሪ ትምህርት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል። በዕለቱም የሲኖዶሱ ማኔጅመንት፤ የሰበካ ተጠሪዎች፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የእጩ ቀሳውስት ቤተሰቦች ተገኝተዋል። ለመከሩ አገልግሎት ታማኝ አገልጋዮችን የጨመረልን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ሐዋሳ፤ ኢትዮጵያዊ ፎቶ - EECMY Referal Congregation

You're Invited! Mekane Yesus Seminary is pleased to announce the Official Inauguration of the Ethiopian Theological Journal (
You're Invited! Mekane Yesus Seminary is pleased to announce the Official Inauguration of the Ethiopian Theological Journal (ETJ) and the Doctor of Ministry (DMin) Program. This milestone marks a significant step in advancing theological scholarship, academic excellence, and ministerial leadership in Ethiopia and beyond. The Ethiopian Theological Journal will serve as a platform for biblical, theological, and contextual research, while the Doctor of Ministry Program is designed to equip experienced church leaders for transformative ministry in today's world. Date: July 7, 2026 Time: 9:00 AM Venue: Helges Center, 5th Floor, Emmanuel G/Selassie Hall We warmly invite church leaders, scholars, students, partners, and friends of Mekane Yesus Seminary to join us as we celebrate this historic occasion. For more information: 📞 +251 961 127 550 📞 +251 973 561 643