uk
Feedback
Gumaa Saaqqataa

Gumaa Saaqqataa

Відкрити в Telegram

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Gumaa Saaqqataa

Канал Gumaa Saaqqataa (@gumaaoro) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 40 606 підписників, посідаючи 1 552 місце в категорії Релігія і духовність та 806 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 40 606 підписників.

За останніми даними від 23 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -98, а за останні 24 години на -26, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 22.03%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 11.74% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 8 953 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 4 771 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 52.

📝 Опис та контентна політика

Опис каналу не надано.

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 24 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

40 606
Підписники
-2624 години
+1087 днів
-9830 день
Архів дописів
Umurii dargagummaa, dhiisee ofiif jiraachuu Fuudhees horadhee ilmaa, bultiin mana dhaabbachuu… Ofiikootti waakkadheenii, siif joora halkaniif guyyaa Biyyaafi sabakoof jedheenii, awwaale fedhii kiyyaa…” Siif kennee lubbuu kiyya..😭

የደመቀ ዥዋዥዌነት የቆመው አስር ሺህ ካ/ሜ መሬት እንዳገኘ ቋሚ አ ቃ ጣ ሪ የሆነው።

የዚህን (ሀጫሉ) የተባለ ወጣት ታሪክ ከ2022 ጀምሮ እጽፈው ነበር። ዛሬም እነሆ ደገምኩት... . ወለጋ ላይ ከአራት አመት በፊት (በ 2022 የተፈጸመ) . የመንግስት ሀይሎች በምስሉ የምንመለከተው
የዚህን (ሀጫሉ) የተባለ ወጣት ታሪክ ከ2022 ጀምሮ እጽፈው ነበር። ዛሬም እነሆ ደገምኩት... . ወለጋ ላይ ከአራት አመት በፊት (በ 2022 የተፈጸመ) . የመንግስት ሀይሎች በምስሉ የምንመለከተው ወጣት እናት ቤት ይገቡና እንዲህ የሚል ማስጠንቀቂያ ሰጧት "ልጅሽ የኦሮሞ ነጻነት ሀይሎችን ተቀላቅሏል። የምንሰጥሽ አማራጭ አንድና አንድ ብቻ ነው። ነገ በዚህ ሰአት ተመልሰን ስንመጣ ልጅሽን ካለበት አምጥተሽው እንድናገኝሽ። አለበለዚያ መሞቻሽ ነገ ነው" በማለት አስጠንቅቀዋት ወጡ። . ያላት አንድ ወንድ ልጅ ብቻ ሲሆን የመንግስት ወታደሮች የገደሏቸውን የሰፈሩን አራት ልጆች ለመቅበር ከቤት ወጥተው የቀብር ጉድጓድ እየቆፈሩ ባለበት ወታደሮች ደርሰው ከመካከላቸው ወጣቶችን እየመረጡ ሲገድሉ አምልጦ የኦሮሞን ሰራዊት የተቀላቀለ ነው። . በነጋታው የቀጠሮዋ ሰአት ደረሰች። ልጇን አምጥታ በፊቷ ልታስገድለው አልፈለገችም። ትናንት አስጠንቅቀዋት የሄዱት ሰዎች ቤቷ ሲገቡ እናት እራሷን በገመድ ሰቅላ ተገኘች። . ለእናቱ አንድ ልጅ የሆነው ሀጫሉ ትግል ውስጥ ባለበት ሁኔታዎች ባይመቹት (ከአባላቶቹ ጋር ባለመግባባት) የብልጽግናን ጥሪ በማመን ወደ ሰላማዊ ህይወት የተቀላቀሉትን ወጣቶች ተከትሎ ገባ ። ካምፕ ውስጥ ባለበት እምነት ያልጣለበት አራርሳ መርዳሳ ለፖሊሶቹ ትእዛዝ አስተላለፈ ለሊት ላይ ፖሊሶች ወደ ወለጋ ወስደውት በጥይት ደብድበው ገደሉት። እነሆ የእናት እና አንድ ልጇ ታሪክም ሆነ የዘር ሀረግ እዚህ ላይ ተቋረጠ።

#Walloo Guyyaa Har'aa Lola irratti warra wareegama kanfalaan keessa tokkoo Aliyee Hassanii Rabbii rahmata haa godhuuf

“Shufeerri Miskiinni Jimaa baddeessaa fe’ee finfinnee dhufu hin ajjeefamin, Maafiyaan wal ijaartee miskiina hiitee cafaqxee Mallaqa baankii isaa keessaa saamuun dhaabatuu qaba jechuun Abiyitti hinaafuudhaa? . . . Nama ajjeesanitti Hinaafaa?”

#Walloo Guyyaa Har'aa Lola Aanaa Harxummaa Fursee karaa Jaarraatiin ture irratti warra wareegaman keessa tokko Ahmad Usiyyoo
#Walloo Guyyaa Har'aa Lola Aanaa Harxummaa Fursee karaa Jaarraatiin ture irratti warra wareegaman keessa tokko Ahmad Usiyyoo manguddoo hawaasa naannawa sanii fi mataa hawaasa sanii ture. Nama 11 wareegama kanfalee😥

salaaleen dur gara Baalee fi Arsiitti baqate ture har'a eessatti haa baqatu dhiiroo?
salaaleen dur gara Baalee fi Arsiitti baqate ture har'a eessatti haa baqatu dhiiroo?

ብልጽግና የዘንድሮውን ምርጫ ሙለ በሙሉ ማሸነፉ ሲነገር🤫

ከመንደር ወደ አለም አለምአቀፍ ያደገው የሻሸመኔ ማፍያ =================================== . . ከዚህ በፊት በሻሸመኔ ከተማ ላይ ስለሚንቀሳቀሰው 120 ስለሚባለው የማፊያ ቡድን ምርመራ አድርጌ ባቀረብኩላችሁ ጊዜ፣ ዳንኤል ዋሾ እና አምቦ ጁላ በከንቲባው ስር በመደራጀት ሰዎችን አግተው በመሰወር ከፍተኛ ገንዘብ እያስከፈሉ እንደነበር መግለጼ ይታወሳል። ያ የሻሸመኔ ማፊያ ቡድን ስርቆቱን ለመሸፈን በጎሳ ስም እንደሚደበቅ እና ማርሻል ብርሃኑ ጁላንም እንደ ከለላ እንደሚጠቀም መጥቀሴ ይታወሳል። . በወቅቱ በስርቆትና በጎሳ የተደራጀው ልወደስ ባይ (አጨብጫቢ) ወርዶ ለማስተባበል ሲሞክር ነበር። እኔ በዚያን ጊዜ ሪፖርት ያደረግኩትን ይኸው የፊንፊኔ (የአዲስ አበባ) ፖሊስ ባለፈው ሳምንት ይፋ አድርጎታል። ሶስት የሲሪላንካ ዜጎች ታግተው ለእያንዳንዳቸው ከቤተሰቦቻቸው ሰላሳ ሺህ ዶላር ተጠይቆ ነበር። በሲሪላንካ ኤምባሲ ጥቆማ በተደረገው ክትትል፣ ሦስቱ የታገቱት ሰዎች ሻሸመኔ ውስጥ በአንድ ቤት ውስጥ ተዘግቶባቸው ተገኝተዋል። ይህንን የእገታ ሴራ ከፈጸሙት መካከል አራት የፓኪስታን እና ሁለት የኢትዮጵያ ዜጎች መያዛቸውም ተዘግቧል። . ከሁለቱ ኢትዮጵያውያን መካከል አንደኛው ማን እንደሆነ ይመስላቹሀል? ጌቱ ገመዳ ገላልቻ ይባላል። እርሱ በሻሸመኔ የ120 ማፊያ አባል ሲሆን፣ “እኔ የብርሃኑ ጁላ ወንድም ነኝ” በማለት ህዝቡን ሲዘርፍ የቆየ ነው። አባቶቻቸው ወንድማማቾች ናቸው (ጌቱ ገመዳ ገላልቻ፣ ብርሃኑ ጁላ ገላልቻ)። በዚህ የውጭ ዜጎች እገታ ላይ፣ የፊንፊኔ ፖሊስ የጌቱ ሚና አሽከርካሪ (ሾፌር) ሆኖ ሰዎቹን ወደ ሻሸመኔ ማድረስ ብቻ እንደሆነ አድርገው አስቀምጠዋል። ይህ ስህተት ነው። ያገተውን ቡድን የሚመራው እሱ ራሱ ነው። በሻሸመኔ ከተማ ከተፈጸሙት በርካታ የሰዎች እገታዎች ጀርባ እሱ ነበረበት። ከእሱ በላይ ደግሞ አምቦ ጁላ አለ። ዳንኤል ዋሾ ከሀገር ቢወጣም፣ ከሩቅ ሆኖ ሁኔታዎችን ያመቻቻል። የፓኪስታን ዜጎችም የመጡት በዚያው መንገድ ነው። የሲሪላንካ ዜጎችም እንዲሁ ተታለው ነው የመጡት። በሻሸመኔ ከተማ እንደ አስፈፃሚ (ጉልበተኛ) በመሆን የዳንኤል ዋሾን ቦታ ተክቶ ሰዎችን የሚደበድበው ማቲዎስ ግርማ ኤደማ ይባላል። እርሱ የከንቲባው የግል ጠባቂ (ቦዲጋርድ) ነው። እዚህ ላይ በአፅንኦት መናገር የምፈልገው አንድ ጉዳይ አለ። የሻሸመኔው ማፊያ ከከንቲባው ጀምሮ እስከ ጌቱ ገመዳ ድረስ የተከበረውን የጎሳ ስም እና የማርሻል ብርሃኑ ጁላን ስም ይጠቀማሉ። የሀገር ሽማግሌዎች የጎሳውን ስም ከእነዚህ ሌቦች አርቁ፣ ጠብቁት። ማርሻል ብርሃኑ በሻሸመኔ በሚፈጸሙት ዘረፋዎችና ማስፈራሪያዎች ላይ ሁሉ ስሙ እየተጠቀሙበት ነው። ሊጎዱት ከሚፈልጉት ሰው አጠገብ ተቀምጠው በመደወል ድምፁን እያሰሙ በማስፈራራት ገንዘብ ይበዘብዛሉ። በዚህ ጥፋት ውስጥ በቀጥታ እጁ የሌለበት ከሆነ፣ እነዚህን ሰዎች ከራሱ ላይ በማራቅ ስሙን ማስከበር አለበት። . ለማንኛውም የሻሸመኔው ማፊያ ከሻሸመኔ ከተማ ተነስቶ ሀገር በመሻገር አለምአቀፍ (international) ሆኗል። እኛ ግን ቀስ በቀስ ስሩን ቆርጠን እናጠፋዋለን። . Jawar Mohammed

ከመንደር ወደ አለም አለምአቀፍ ያደገው የሻሸመኔ ማፍያ =================================== . . ከዚህ በፊት በሻሸመኔ ከተማ ላይ ስለሚንቀሳቀሰው 120 ስለሚባለው የማፊያ ቡድን
+6
ከመንደር ወደ አለም አለምአቀፍ ያደገው የሻሸመኔ ማፍያ =================================== . . ከዚህ በፊት በሻሸመኔ ከተማ ላይ ስለሚንቀሳቀሰው 120 ስለሚባለው የማፊያ ቡድን ምርመራ አድርጌ ባቀረብኩላችሁ ጊዜ፣ ዳንኤል ዋሾ እና አምቦ ጁላ በከንቲባው ስር በመደራጀት ሰዎችን አግተው በመሰወር ከፍተኛ ገንዘብ እያስከፈሉ እንደነበር መግለጼ ይታወሳል። ያ የሻሸመኔ ማፊያ ቡድን ስርቆቱን ለመሸፈን በጎሳ ስም እንደሚደበቅ እና ማርሻል ብርሃኑ ጁላንም እንደ ከለላ እንደሚጠቀም መጥቀሴ ይታወሳል። . በወቅቱ በስርቆትና በጎሳ የተደራጀው ልወደስ ባይ (አጨብጫቢ) ወርዶ ለማስተባበል ሲሞክር ነበር። እኔ በዚያን ጊዜ ሪፖርት ያደረግኩትን ይኸው የፊንፊኔ (የአዲስ አበባ) ፖሊስ ባለፈው ሳምንት ይፋ አድርጎታል። ሶስት የሲሪላንካ ዜጎች ታግተው ለእያንዳንዳቸው ከቤተሰቦቻቸው ሰላሳ ሺህ ዶላር ተጠይቆ ነበር። በሲሪላንካ ኤምባሲ ጥቆማ በተደረገው ክትትል፣ ሦስቱ የታገቱት ሰዎች ሻሸመኔ ውስጥ በአንድ ቤት ውስጥ ተዘግቶባቸው ተገኝተዋል። ይህንን የእገታ ሴራ ከፈጸሙት መካከል አራት የፓኪስታን እና ሁለት የኢትዮጵያ ዜጎች መያዛቸውም ተዘግቧል። ሙሉውን ከታች ባለው ገጽ

"በታሰርኩበት ቆርቆሮ ቤት ቀዳዳ ወደ ዉጪ ስመለከት ከአፋኞቼ አንዱ ጃኬቴን ለብሶ ኳስ ይጫወታል"

--------------------የቶላ ገዳ ግድያ--------------- . (ቶላ ገዳን ራሳቸው ገ ድ ለ ው አርሲና ወለጋን ለማጋጨት የተሸረበው ሴራ ) . . ቶላ ገዳ በትውልዱ ምዕራብ አርሲ ነጌሌ አርሲ ወረዳ ጎርቢ አርባ ቀበሌ ነው። አባቱ አዝማች ገዳ በመባል የሚታወቁ ሲሆን ባለሀብትና የሀገር ሽማግሌ ነበሩ። ቶላ ወደ ኦህዴድ ከተቀላቀለ በኋላ በዚያው አካባቢ በተለያዩ ደረጃዎች ስልጣን ተሰጥቶት ሲሰራ ቆይቷል። በስልጣኑም በነጌሌ አርሲ አካባቢ ታጋዮችን ሲበድል ነበር። ቆይቶም ወደ ክልል በማደግ የኦሮሚያ መንገዶች መሪ ሆኖ እያለ ወደ ወለጋ ተመድቦ ሄደ። . ከለውጡ በኋላ በ2019 በወለጋ የ ኦ ነ ግ (W B O) እንቅስቃሴ በበረታበት ወቅት፣ የአካባቢው ተወላጅ የሆኑ የዞንና የወረዳ አመራሮችን ማመን ስለተሳነ ተሰብስበው ወደ ተሃድሶ እንዲገቡ ተደረገ። በነሱ ምትክ በትውልዳቸው የሌላ ዞን የሆኑ አመራሮችን ‘የደጋፊ ካቢኔ’ በሚል ስም በወለጋ ዞኖችና ወረዳዎች ውስጥ መድበው ላኳቸው። በዚህ መሰረት ቶላ ገዳ ወደ ቄለም ወለጋ ሰዮ ወረዳ ተመድቦ ሄደ። . እንግዲህ የእሱ የግድያ ሴራ የጀመረው ከዚሁ ምደባ ላይ ነበር። በወቅቱ በወለጋ የአመራሮች ግድያ በርትቶ ስለነበር፣ ወደዚያ መላክ እንደ ሞት ፍርድ ይታይ ነበር። ብዙ አመራሮች እንዲሄዱ ተመድበው እምቢ በማለታቸው ከስራ መባረራቸው የሚታወቅ ነው። አንዳንዶቹ ደግሞ ለከፍተኛ አመራሮች ገንዘብ በመስጠትና በሽምግልና ቀሩ። ከፍተኛ አመራሮቹም ቂም ያለባቸውን ወይም ለስልጣን የሚፎካከሯቸውን ሰዎች ለመቅጣት ወደዚያ ይልኩ ነበር። . ቶላ ገዳም ከስልጣን ፉክክር ውስጥ ለማስወገድ ከተላኩት መካከል አንዱ ነው። ቶላ እንደ ወርቅነህ ገበየሁ ካሉ ከፍተኛ ስልጣን ካላቸው ሰዎች ጋር ጠንካራ ትስስር ስለነበረው፣ ከአርሲ ለከፍተኛ ስልጣን ዕድል አላቸው ተብለው ከሚታሰቡት ሰዎች አንዱ ነበር። ይህ ደግሞ ከግምባር ቀደም ካለው ሰልፍ ላይ ቆሞ ይጠባበቅ ለነበረው ለአወሉ አብዲ አደጋ ነበር። በተጨማሪም በወያኔ ዘመን በሀሳሳ ውስጥ አወሉ ያስፈጸመውን የደህንነት ወንጀል ዶክመንተሪ በማጠናቀር ውስጥ ቶላ ገዳ እጅ አለበት ብሎ ይጠረጥር ነበር። ስለዚህ ወደ ወለጋ የደጋፊ ካቢኔ የመላክ ጉዳይ በመጣ ጊዜ፣ አወሉ ፍቃዱ ጩዌን (ተሰማን) በማሳመን ቶላ ገዳን በቅድሚያ ተሰላፊነት አስመዘገበው። . ቶላ እንዳይሄድ ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ ቢመክሩትም፣ እንዲህ ያለውን ከባድ ኃላፊነት መወጣት ለምኞቴና ለሥልጣን ፉክክር ይረዳኛል ብሎ ስላመነ ወደ ቄለም ሰዮ ሄደ። ነገር ግን እዚያ እንደደረሰ ወዲያውኑ ችግር መጋፈጥ ጀመረ። "የሰላም ፈንድ" ተብሎ በካቢኔ ድጋፍ አማካኝነት ለወረዳዎች የሚሰጥ ገንዘብ ነበር። ከዚህ ፈንድ ውስጥ የተወሰነው መጠን በሙስና ተዘዋውሮ ተመልሶ ለኦሮሚያ ባለሥልጣናት ይሰጣል። ቶላ ከተመደበበት ቦታ ፈንድ ቆርጦ ወደ ላይ መላክ እምቢ አለ። ይህንን ብቻ ሳይሆን ይህንን ጉዳይ ለእሱ ቅርብ ለሆኑ የፌዴራል ባለሥልጣናት ነገረ። በዚህ ድርጊቱ ለራሱ መገደል ፈረመ። . በዚህ መሃል ለስብሰባ ወደ ክልል ተጠራ፤ የፌዴራል ባለሥልጣናትንም አግኝቶ ስለ ፈንዱ ጉዳይ በአካል ነገራቸው። ስብሰባው አልቆ ከሌሎች ባለሥልጣናት ጋር ወደ ቄለም እየተጓዘ ነቀምቴ ሲደርሱ፣ ከዚያ ወዲያ በባለሥልጣናት መኪና መሄድ እንደሌለባቸው ተነገራቸው። የቀረበውም ምክንያት "በመንግሥት መኪና ከሄዳችሁ ሸኔ በቀላሉ ለይታ ይመታችኋል፤ ስለዚህ ከሕዝብ ትራንስፖርት ጋር ተመሳስላችሁ ሂዱ" የሚል ነበር። ቶላና ሌሎች ባለሥልጣናትም እንደተባሉት የሕዝብ ትራንስፖርት መኪና ተሳፍረው ጉዟቸውን ቀጠሉ። . አንድ የፒክአፕ (pickup) መኪና ያንን የሕዝብ አውቶቡስ ለረጅም ጊዜ ሲከተል ነበር። በማጫራ፣ ጋባ ሮቢ እና ጨንቃ መካከል ሲደርሱ ከፒክአፕ መኪናው ውስጥ ሁለት ሰዎች ወርደው አውቶቡሱን አስቆሙና ውስጥ ገቡ። ከመላው አውቶቡስ ውስጥ የቶላ ገዳን ስም ጠርተው እንደሚፈለግ ሲነግሩት ተነሥቶ አብሯቸው ወረደ። ቶላ በዚያን ጊዜ ሽጉጥ በእጁ ቢኖረውም፣ ሁለቱ ሰዎች የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መሆናቸውን ስላወቀ ምንም ሳይከላከል አብሯቸው ወረደ። እነሱ ግን ወስደው ዓይኑን አውጥተው (በጭካኔ) ገደሉት። የክልሉ መንግሥትም "ሸኔ ነው የገደለው" ብሎ ሪፖርት አደረገ። አውቶቡሱን ያሽከረክር የነበረው ሹፌር "ለምን በዚያ ቦታ አስቆምክ?" ተብሎ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ለቶላ ቤተሰቦችና ለሀገር ሽማግሌዎች ቢነገራቸውም፣ ቆይቶ ግን ተለቀቀ። ለሕግ ቀርቦ የተቀጣ አንድም ሰው የለም። . የኦሮሚያ የአስተዳደርና የጸጥታ ባለሥልጣናት ቶላን ለመግደል ያሴሩ እንደነበር የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ያውቅ ነበር። መጀመሪያ ሰዮ እንደሄደ ሊገድሉት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የፌዴራል መረጃዎች (ደኅንነቶች) አክሽፈውት ነበር። ለስብሰባ ወደ አዲስ አበባ በመጣ ጊዜም ወደ ወለጋ እንዳይመለስ እነዚህ የፌዴራል ደኅንነት ሰዎች ነግረውት ነበር። ቶላ ግን መሄዱን ቀጠለ። እነዚያ የደኅንነት ሰዎችም ይህንን የቶላን የግድያ ሴራ ሪፖርት ለከፍተኛ የፌዴራል ባለሥልጣናት ቢያቀርቡም፣ ምንም ዓይነት እርምጃ ሳይወሰድ ተድበስብሶ ቀረ። የቶላ ገዳዮች ያሴሩት ሴራ በዚያ አላበቃም። አስከሬኑን ለቤተሰቦቹ ባስረከቡበት ወቅት፣ አወሉ አብዲ እና ግብረአበሮቹ የአርሲ ኦሮሞ አባገዳዎችንና ሽማግሌዎችን በአንድነት በመሰብሰብ “የልጃችሁን ህይወት የቀጠፈው የወለጋው ሸኔ ስለሆነ ደ ሙ መመለስ (ጉማ) አለበት” አሏቸው። . የዚህ የደም መመለስ ጥሪ ዋና ዓላማ፣ በአርሲ ዞኖች ውስጥ ወለጋን የሚያወግዝ ሰፊ ሰልፍና ሁከት በመቀስቀስ የሁለቱን አካባቢዎች ተወላጆች እርስ በርስ ማጋጨት ነበር። ይህ ስልት ደግሞ “ሸኔ ከወለጋ ውጭ የመስፋፋት ዕድሏን ለማጥበብ ይጠቅማል” ተብሎ የታሰበበት ነበር። . ነገር ግን ነገሩ እዚያ ሳይደርስ ከሸፈ። ሽማግሌዎቹ ተቀምጠው የደም መመለስ (ጉማ) አዋጅ ውይይት እንደጀመሩ፣ የቶላ ገዳን አስከሬን ከወለጋ ይዞ የመጣ አንድ ባለስልጣን፣ ሽማግሌዎቹ “የወለጋው ሸኔ” የተባለውን ነገር በወለጋ ውስጥ እንዳለ የኦሮሞ ጎሳ አድርገው እንደተረዱት ተገነዘበ። በመሆኑም “ሸኔ መንግስትን የሚወጋ የታጠቀ የፖለቲካ ድርጅት እንጂ ጎሳ አይደለም” በማለት አስረዳቸው። ሽማግሌዎቹም “እኛ በፖለቲካ ድርጅት ስም የደም መመለስ (ጉማ) የምናውጅበት ሥርዓት የለንም” በማለት ጉዳዩን ዘጉት። በዚህ መልኩ ቶላ ገዳን ራሳቸው ገድለው አርሲና ወለጋን ለማጋጨት የተሸረበው ሴራ ሳይሳካ ቀረ። ባጭሩ ቶላ ገዳ ማፊያ የሆኑ የመንግስት ባለስልጣናት መጀመሪያ ገድለው በሸኔ ላይ በማሳበብ የፖለቲካ ትርፍ ካሰሉባቸው 120 ሰዎች መካከል አንዱ ነው። ከዚያ በኋላ ኮሚሽነር ሰለሞን እና ሌሎችም እያለ ይቀጥላል። . ማሳሰቢያ፦ የዚህ ጥናት የመረጃ ምንጮች • ከፌዴራል ደህንነት የተገኘ የሰው እና የቴክኒክ ምርመራ መዝገብ (የመረጃ ምንጨ እንዳይታወቅ አሁን ባላዝመውም፣ ጊዜው ሲደርስ ለህዝብ ይፋ አደርገዋለሁ)ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ የፌዴራል ደህንነት አባላትበወቅቱ የነበረውን እሰጣ አገባና ፉክክር የሚያውቁ የፖለቲካ እና የፀጥታ አመራሮችበሰዮ የነበሩ እንዲሁም የቶላን አስከሬን ያነሱ የኦሮሚያ ፖሊስ አዛዦች እና አባላትበዚያ አውቶቡስ ውስጥ የነበሩ የዓይን እማኞች

--------------------የቶላ ገዳ ግድያ--------------- . (ቶላ ገዳን ራሳቸው ገ ድ ለ ው አርሲና ወለጋን ለማጋጨት የተሸረበው ሴራ ) . .ሙሉውን ከታች ታገኙታላቹ👇
--------------------የቶላ ገዳ ግድያ--------------- . (ቶላ ገዳን ራሳቸው ገ ድ ለ ው አርሲና ወለጋን ለማጋጨት የተሸረበው ሴራ ) . .ሙሉውን ከታች ታገኙታላቹ👇

#Milishaan_Harargeef kilaasha takka yoo itti keennaan dalagaan waa sadeen kun kan inni raawatu itti fakkaata Seera Baastun...isuma Seera Hiikuun...kan isaa Seera Raawwatuun...mirga itti keename

+1
በዚህ መልኩ ጎረምሳ ወጣቶቾን ራቁታቸውን እየገረፉ ቪድዮ የሚቀርጿቸው ሊቢያ ላይ ሳይሆን ኢትዮጵያ (ኦሮሚያ ውስጥ ወሊሶ ) ላይ ነው።

እቺ የሽሜ ንግግር በደርግ ዘመነ መንግስት በጎጃም ክፍለ ሃገር የእናርጅና እናውጋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ቆምጫምባውን አስታወሰኝ አንዴ #አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫና በመቃወም የክተት አዋጅ ጭምር በመጥራት ልክ ሊያገቧት በማሰብ ማስጠንቀቂያውን በኢትዮጵያ ሬድዮ በቀጥታ ተላለፈ። የኢትዮጲያ ሬድዮ ያስተላለፈው የቆምጫምባው መልእክት ርእስም ፦ "የጎጃም ገበሬዎች የአሜሪካን ኢምፔሪያሊዝምን አስጠነቀቁ" የሚል ሲሆን አሜሪካ ካላረፈች ልክ ሊያስገቧት የሚችሉበት አቅም እንዳላቸው ነበር የገለጹት። (በነገራችን ላይ አቶ ቆምጫምባው አሁን ላይ በጥብቅና የሙያ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ አባት ናቸው)

ዛሬ የአሜሪካ መንግስት ሴኔት እገዳ መጣሉን ስለማ እንደዛሬው ሁሉ በ2021 እገዳ ሲጥሉ ጌቾ ለመጀመሪያ ግዜ የሰጠው ቃለምልልስ እነሆ

በድሬዳዋ በምርጫው የግል ተወዳዳሪ የነበረው ዶክተር ሀብታሙ በትናንትናው እለት መታሰሩ ተነግሯል ================================ . . ድሬዳዋ ላይ ሲደረግ በነበረው ምርጫ የግል ተወዳዳሪ ሆኖ ቀርቦ የነበረው ዶክተር ሀብታሙ ዓለሙ ትናንት የቤተሰቡ መኖሪያ ቤት በታጠቁ ሀይሎች ተከቦ ከዋለ ቦሀላ በቁጥጥር ስር መዋሉን ከስፍራው ማረጋገጥ ችለናል። . ዶክተሩን ለማሰር የተኬደበትን እና ከአሁን ቀደም " ምርጫውን ለመወዳደር በማያስችል ጫና ላይ በመውደቄ ኤራሴን ከውድድር አግልያለሁ" በማለት ዝርዝሩን በመጻፉ ምክንያት የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን የሰራውን ድራማ እንደገና ትናንት ዶክተር ሀብታሙን ከማሰራቸው በፊት ሊነሳባቸው ይችላል በማለት የሰሩትን ቁጥር ሁለት ድራማን ዝርዝር የምገልጸው "እንመራሀለን" የሚሉትን ማህበረሰብ ምን ያህል እንደሚንቁት ቁልጭ ያለ ማሳያ በመሆኑ ነው። . ከ15 ቀን በፊት ዶክተር ሀብታሙ በምን ምክንያት እራሱን ከምርጫ እንዳገለለ (May 23.) የጻፍኩት እንደሚከተለው ነው... . "በድሬዳዋ ከተማ እጩ የምርጫ ተወዳዳሪ እንደሆነ ሲገልጽ የነበረው ዶክተር ሀብታሙ አለሙ ትናንትና ከውድድሩ እራሱን ማግለሉን እና ያንን ውሳኔ እንዲወስድ ካስገደዱት ምክንያቶች መካከል የድሬዳዋ የሌሊት ታክሲ ሹፌሮች ማህበር አባል የሆነ ሰው ውድድሩን እንዳቋርጥ የተለያዩ ጥቃቶች ሲፈጽምብኝ ለፖሊስ አመልክቼ በህግ ፊት ማቅረብ ሲገባ፣ ግለሰቡ ካድሬ በመሆኑ ብቻ በድሬዳዋ የፀጥታ አካላት ከለላ እየተሰጠው መሆኑን እና በዚህ መልኩ አልቀጥልም" በማለት ውድድሩን ማቋረጡን ትናንት ምሽት ላይ ገለጸ" የሚል ሲሆን በዛውን እለት የድሬዳዋ ፖሊስ የዶክተሩን ክስ ይሸፍንልኛል በማለት በድሬዳዋ ፖሊስ የFacebook ገጽ "ታማኝነት በተግባር" በሚል ርእስ ምርጫውን ሲወዳደር የነበረው ዶክተር ሀብታሙ ላይ ጥቃት የፈጸመውን ሰው ስም በመጥቀስ "የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ አባል የሆነው ወጣት በአካውንቱ የገባን 50ሺህ ብር መለሰ" ብሎን ጉደኛ ስከሳ ሰክሶን አለፈ። "እህ" ብለን በዝምታ ባለንበት ትናንት ዶክተሩን እንዳሰሩ እንደባለፈው ሁሉ በዛው በተለመደው በድሬዳዋ ፖሊስ የ Facebook ገጽ የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር የመሰረቱትን እና አመራር የሚሰጡትን የሁለቱን (የኮሚሽነሩን እና የወንጀል መከላከል ሀላፊ የተባለውን ሰው) ምስል የተጠቀመው የድሬዳዋ ፖሊስ ገጽ "የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር ከ 1.2 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የገነቧቸውን ቤቶች ለአቅመ ደካሞች አስረከበ" የሚል ህዝብን የናቀ ነውረኛ የሆነ ሽፋን ሰጡበት (በነገራችን ላይ ስለተባለው ቤት ሙሉ ማስረጃ በዚህች ሁለት ቀን ውስጥ ጠብቁኝ) እንግዲህ 1.2 ሚሊየን ብር ወጪ አደረጉ የተባሉት የማህበሩ አባላት ቁጥራቸው ከ350- 400 የማያልፍ ናቸው። ይሄ "የድሬዳዋ የለሊት ታክሲ ማህበር" የሚባለው እንዴት ተመሰረተ፣ እነማን መሰረቱት ፣ ለምን አላማ ተመሰረተ የሚለውን ቀንጨብ አድርጌ ለማቅረብ እሞክራለሁ የተመሰረተው በድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽነር የበላይ ፈቃድ ም/ኮማንደር ይሄነው የትራፊክ ፖሊስ አዛዥ በነበረበት ወቅት ከባጃጅ እና ፎርስ ሾፌሮች መካከል ለነርሱ ታማኝ እና ለሚፈለግባቸው ተልእኮ ይሆናሉ ብለው በጥንቃቄ መርጠው ያዋቀሯቸው ሾፌሮች ናቸው። የተመሰረተበት አላማ "ለሊት ማህበረሰቡን በትራንስፖርት ሰራ እንዲያገለግሉ"የሚለው ሽፋን መጠሪያ ሲሆን የወጣቶቹ ተልእኮ የኮሚሽነሩን እና ኮማንደሩን ተልእኮዎች መፈጸም ነው። የሁለቱን የፖሊስ አመራሮች ስም ይበልጥ በሶሻል ሚድያም ሆነ በሰፈር ውስጥ "አማ" የተባለን ማንም ይሁን አድነው በነርሱ አጠራር "ልክ ማስገባት" የሚል ነው። እነዚህ በቁጥር በ350-400 የሚሆኑት ወጣቶች ልክ እንደ ሂ ት ለ ሩ ጌስታፖ የሚከሳቸው የለም። በቀንም ይሁን በለሊት በር ሰብረው ግቢ በመግባት "የኮሚሽነራችንን ስም አጠለሻቹ፣ ኮማንደራችንን በክፉ አይን ትመለከታላቹ " ያሏቸውን እንደ ኦሮሚያው 12ዐ ማፍያ ቪድዮ እየቀረጹ ይደበድባሉ ፣ ጥርስ ያወልቃሉ። ይህን ሲፈጽሙ በተቃራኒው እነሱ የሚጠቀሙት ደግሞ በድሬዳዋ ከተማ ውስጥ ሶስት ሰአት ካለፈ ቦሀላ የ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡት እነርሱ ብቻ ናቸው ። እነርሱ በያዙት ተሽከርካሪ ላይ ያለውን የለሊት ታክሲ ምልክት የሌለው ቤተሰብ ሊሸኝ እንኳ ከቤት ወጥቶ ከያዙት አንጠልጥለው ጣቢያ ይከቱታል። ሁለተኛ ደግሞ በኪሎሜትር የተደነገገላቸው ታሪፍ የለም። ለሁለት ኪ/ሜ ሁለት ሺህ ብር ካሉህ ከመክፈል ውጪ ምንም ምታመጣው የለም። ወደ ህግ ቦታ ብትቀርብም "ያሉህን ክፈል ነው መልሱ። . በኮሚሽነሩ እና ኮማንደሩ ትእዛዝ የሚሰማሩት የለሊት ታክሲ ሾፌር ሽፋን የተሰጣቸው ወጣቶች በዶክተር ሀብታሙ ላይ የፈጸሙት ድብደባ እና በቤቱ ፣ ስራው ቦታ ብሎም በእያንዳንዷ በሚንቀሳቀስባቸው እየተከተሉ ሲያደርሱበት የነበረው የስነልቦና ጉዳት ሊረዳለት የሚችለው እነዚያን ከሰው የተፈጠሩ የማይመስሉ እጅግ ለመግለጽ ጭምር የሚከብድ መረንነት የተላበሱት ተላላኪዎችን ለማውራት የሞከረ ብቻ ነው። . የዶክተሩ ቁስል እኔ ያለፍኩበት መንገድ ነው። ታናሽ እህቴ ላይ ተልከው ቀን ከሌት ሳይሉ መግቢያ መውጫዋ ላይ እየተከተሉ በሚፈጽሙት የስድብ እና ማስፈራራት ቤቷን አከራይታ ድሬዳዋን እስከመልቀቅ ደርሳለች ፣ ታላቅ እህቴ ስራዋን ትታ ቤቷ የተቀመጠችው እነዚህ አድርጉ የተባሉትን ከማድረግ ወደ ሁዋላ የማያውቁ በእድሜም በህሊናም እንጭጭ የሆኑ መልእክተኞች ቤቷን በተከታታይ Live ደውለውልኝ በሯን በርግደው በመግባት እሷን ጭምር እያሳዩኝ " የምታደርገውን ዘመቻ ታቆማለህ አታቆምም" የሚሉ... . ወገኖች መቼም ሁላችንም ከእናት ነው የተወለድነው ከእናቴ ጋር አብሮ የሚኖረውን እና በፖሊስ ውስጥ ያለውን አንድ ወንድሜን "አመራሮቻችን ላይ የምታደርገውን ዘመቻ ካላቆምክ" በማለት ወንድሜም በታጠቁት ሀይሎች እንዲገደል ካሁን ቀደም ፖሊሶቹ በተገደሉበት ቦታ ከመደቡት ቦሀላ ብቻዋን ያገኟት እናትን እነዚህ ህሊና ቢስ ወጣቶች ቤቷ ድረስ ሄደው እየቀረጹ በቪድዮ እስከማስፈራራት የደረሱ ሰዎች ናቸው። ይህ ነው እውነታው። ከሀገራቸው ውጪ ሆነው በአስተዳደሩ ዙሪያ ጥያቄ ያነሱ ሰዎችን ዝም የሚያስብሉት ትናንት አብዲ ኢሌ የነ ሙስጠፌን ወንድሞች አስሮ እየደበደበ እነ ሙስጠፌ መቃወማቸውን ከቀጠሉ ዱላውን እንደሚቀጥል በቪድዮ አስደግፎ ሲልክ የነበረውን መሰል ተግባር የወረሰው እንደ ጀርመኑ ጌስታፖ በድሬዳዋው ፖሊስ ኮሚሽነር የሚመራው 120 የማፍያ ስብስብ ነው። ቀኑ እሩቅ አይደለም። የምታሰማሯቸውን ወጣቶች ማንነት በምስልም ሆነ በድምጽ ተሰባስቦ የእውነት ቀንን ይጠብቃል። በመጨረሻ ግን እውነት እንደምታሸንፍ ፤ እናንተም ለፈጸማችሁት ሁሉ ከመጠየቅ እንደማታመልጡ እሙን ነው። . (በዚህ አጋጣሚ ከአሁን ቀደምም እንደገለጽኩት በመላው ቤተሰቤ ላይ ስለምታስደርሱት ብቻ ሳይሆን ከአሁን ቀደም ላደረሳችሁት ለሚደርስባቸው ሁሉ በግምባር ቀደምትነት ለእነዚያ ጋጠወጥ ወጣቶች ስምሪት የሚሰጠው ኮማንደር ይሄነው የተባለ የድሬዳዋ ከተማ ወንጀል መከላከል ሀላፊ ተደርጎ እየሰራ ያለ ሰው ተጠያቂነቱን የሚወስድ ነው)

በድሬዳዋ በምርጫው የግል ተወዳዳሪ የነበረው ዶክተር ሀብታሙ በትናንትናው እለት መታሰሩ ተነግሯል ================================ . . ድሬዳዋ ላይ ሲደረግ በነበረው ምርጫ የግል
በድሬዳዋ በምርጫው የግል ተወዳዳሪ የነበረው ዶክተር ሀብታሙ በትናንትናው እለት መታሰሩ ተነግሯል ================================ . . ድሬዳዋ ላይ ሲደረግ በነበረው ምርጫ የግል ተወዳዳሪ ሆኖ ቀርቦ የነበረው ዶክተር ሀብታሙ ዓለሙ ትናንት የቤተሰቡ መኖሪያ ቤት በታጠቁ ሀይሎች ተከቦ ከዋለ ቦሀላ በቁጥጥር ስር መዋሉን ከስፍራው ማረጋገጥ ችለናል። . ዶክተሩን ለማሰር የተኬደበትን እና ከአሁን ቀደም " ምርጫውን ለመወዳደር በማያስችል ጫና ላይ በመውደቄ ኤራሴን ከውድድር አግልያለሁ" በማለት ዝርዝሩን በመጻፉ ምክንያት የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን የሰራውን ድራማ እንደገና ትናንት ዶክተር ሀብታሙን ከማሰራቸው በፊት ሊነሳባቸው ይችላል በማለት የሰሩትን ቁጥር ሁለት ድራማን ዝርዝር የምገልጸው "እንመራሀለን" የሚሉትን ማህበረሰብ ምን ያህል እንደሚንቁት ቁልጭ ያለ ማሳያ በመሆኑ ነው። . ሙሉውን ታሪክ በቀጣዩ ገጽ👇 .

Milishaan harargee kun bar kan nama irraa dhalatte hin fakkattuu