Joseph Math Tutor
Відкрити в Telegram
Hello, welcome to Joseph Math Tutor channel! https://youtu.be/D8K0MVqynVA?si=y_uFeHG7awC1oX9Y Subscribe our youtube channel On tiktok : josephmathtutor Owner: Yosef Adefris @yosef_2580
Показати більше1 771
Підписники
+524 години
+297 днів
+9330 день
Архів дописів
1 771
#Grade_12_Result
➡️ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ከመደረጉ በፊት ትምህርት ሚኒስቴር ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ይፋዊ መግለጫ ይሰጣል። የተማሪዎች ዉጤትም ሌሊት 6 ሰዓት ጀምሮ መታየት ይጀምራል ብለን እንገምታለን ::
➡️ ይሄንን ይፋዊ የትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ "Joseph Math Tutor" በእያንዳንዱ ደቂቃ እየተከታተለ የሚያቀርብላችሁ ይሆናል::
➡️ ውጤት ሲገለፅ በቀላሉ ለማየት ከዚህ በታች ያሉትን አማራጮች መጠቀም ትችላላችሁ!!!
1. eaes.et
2. eaes.gov.et
3. eaes.edu.et
4. result.neaea.gov.et
5. SMS 6284
6.https://t.me/EAESbot
📌 አዲስ ነገር ሲኖር ወዲያውኑ እየተከታተልን የምናደርሳችሁ ይሆናል:: ዉጤት ለሚጠብቁ ተማሪዎች share አድርጉ::
መልካም ዕድል ለተፈታኞች
1 771
+1
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል።
የትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ አሳውቋል።
የፈተና ውጤቱን አስመልክቶ ነገ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ መግለጫ ይሰጣል።
#MoE
1 771
+1
" ሲያልቅልን ውጤት ይፋ የሚደረግበትን ትክክለኛ ቀን እናሳውቃችኋለን " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
በርካታ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች " የ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መቼ ነው ይፋ የሚደረገው ? ከዚህ ቀደም የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ጳጉሜን 4/2017 ዓ/ም ይፋ ይደረጋል ብለው ነበር ሳይደረግ አለፈ ውጤት ይፋ የሚደረገው መቼ ነው ? " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተማሪዎች እና ወላጆችን ጥያቄ ይዞ አንድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከፍተኛ አመራርን አነጋግሯል።
እኚህ አመራር " ውጤት ሲያልቅ እንገልፃለን በተቻለ መጠን በአጭር ጊዜ ይለቀቃል፤ ትክክለኛው ቀን ሲወሰንም በይፋ ሚዲያ ጠርተን እናሳውቃለን " ብለዋል።
" የተለያዩ የማህበራዊ ሚድያዎች ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ በማስተላለፍ ተማሪዎችን እያወናበዱ ነው " ያሉት አመራሩ ተማሪዎች ውጤቱ ይፋ የሚደረግበትን ቀን ከተቋሙ እስኪሰሙ በትዕግስት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል።
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች (በፌስቡክ ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ) " ስለ ውጤት መረጃ አገኘን በዚህ ቀን ይወጣል " እያሉ የሚያሰራጩት መረጃዎችም ሀሰተኛ እንደሆነ ተጠቁሟል።
" እኛ በሚያልቅ ጊዜ እናንተን ጨምሮ ሚድያዎችን ጠርተን እናሳውቃለን " ያሉም ሲሆን " ' በዚህ ቀን ይወጣል ተብሎ ነበር ' የሚለው ሳይሆን ጥርት ብሎ ሲያልቅልን በፍጥነት እናሳውቃለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከ580 ሺህ በላይ ተማሪዎች መውሰዳቸው አይዘነጋም።
1 771
እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ።
አዲሱን ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፤የደስታ፣የመከባበር፣የመተሳሰብ፣ የአንድነት ዓመት ያድርግልን።
መልካም በዓል ለሁላችንም
JOSEPH MATH TUTOR
1 771
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በተመለከተ 2 ነገሮች በስፋት እየተወሩ ነው
1. ወደ መስከረም 1 ተራዝሟል
2. ዛሬ ማታ ይለቀቅና ነገ መግለጫ ይሰጣል።
እስከ ማታ የተረጋገጠ መረጃ ስለሚወጣ በትዕግሥት ጠብቁ።
1 771
+9
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተመረቀ
እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያውያን!!!
❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
1 771
JMT Charity
🎯 ዓላማው
- አቅመ ደካማ የሆኑ ሰዎችን ለመርዳት
- በገንዘብ ምክንያት ትምህርታቸውን መከታተል ላቃታቸው ተማሪዎች ድጋፍ ለማድረግ እና ትምህርታቸውን ለማስቀጠል
ትግበራ
- የሚሰበሰበው በወር 100 ብር ነው።
መዋቅር
1. ስራ አስኪያጅ = 1 ሰው
2. ፀሐፊ = 1 ሰው
3. ቁጥጥር = 2 ሰው
4. አስተባባሪ = 5 ሰው
5. አባላት
ሕግና ደንብ
1. ማንኛውም አባል የሆነ ሰው በየወሩ የመክፈል ግዴታ አለበት።
2. ብሩ ተሰብስቦ እርዳታ ላይ በሚውልበት ሰዓት የሁሉም የማህበሩ አባላት ውሳኔ መወሰን አለባቸው።
3. ያለ ውሳኔ እና ፍቃድ ገንዘቡን ከባንክ አካውንቱ ማውጣት አይቻልም።
4. በወር ውስጥ ቢያንስ አንድ ቀን ስብሰባ ይኖራል።
5. በስብሰባው ላይ መገኘት የሁሉም አባላት ግዴታ ነው።
የስብሰባ ቦታ
ASTU , Block 515 (Space-A)
ማሳሰቢያ
- ማንኛውም የASTU ተማሪ መግባት ይችላል።
- እርዳታው ዘር፣ እምነት አይለይም።
ለመመዝገብ እና አባል ለመሆን:-
Telegram= @yosef_2580
Phone = 0911708941
0910775924
"50 ሎሚ ለ1 ሰው ሸክም ለ50 ሰው ጌጥ ነው"
JOSEPH MATH TUTORIAL CHARITY
#ASTU
1 771
#ዉጤት ከመገለፁ በፊት ትምህርት ሚኒስቴር በይፋ መግለጫ ይሰጣል:: ትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ከሰጠ በኃላ ነው ዉጤት ማየት ምትጀምሩት:: ስለዚህ በትዕግስት ጠብቁ 🙏🙏
#ዉጤት ሲገለፅ በቀላሉ የምታዩባቸው መንገዶች !!!
1. eaes.et
2. eaes.gov.et
3. eaes.edu.et
4. result.neaea.gov.et
5. SMS 6284
6.https://t.me/EAESbot
1 771
የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል።
የሁሉም መደበኛ ተማሪዎች (ቅድመ፣ ድህረ እንዲሁም የዶክትሬት ተማሪዎች) ምዝገባ መስከረም 7 እና 8 /2018 ዓ/ም መሆኑ ተገልጿል።
መስከረም 9 እና 10 ደግሞ በ2017 የሬሜዲያል ትምህርት ተከታትለው የማለፊያ ውጤት ያመጡ እንዲሁም አዲስ የመጀመሪያ አመት ፍሬሽ ማን እና የሬሜዲያል ተማሪዎች ምዝገባ ቀን እንደሆነ ተገልጿል።
አምቦ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር
@Joseph_maths_tutorial
1 771
ለኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ
የኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ የነባር መደበኛ ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን እናሳዉቃለን፡፡ ትምህርት የሚጀምረዉ መስከረም 12፣ 2018 ዓ.ም ይሆናል፡፡
በ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን በኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ተከታትላችሁ ማለፍያ ነጥብ ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች፤ የ2018 ዓ.ም አዲስ ገቢ (ፍሬሽማን) ተማሪዎች ምደባ በትምህርት ሚኒስቴር ይፋ ሲደረግ ወደፊት በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ የሚደረግላችሁ ይሆናል፡፡
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 771
+1
#DebreBerhanUniversity
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለነባር ተማሪዎቹ ጥሪ አድርጓል፡፡
በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁ ነባር የቅድመ እና የድኅረ ምረቃ መደበኛ እና የኤክስቴንሽን ተማሪዎች የ2018 ዓ.ም የምዝገባ ጊዜ መስከረም 08 እና 09/2018 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች መግቢያ ጊዜ ወደፊት ይገለጻል ተብሏል፡፡
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 771
#BulehoraUniversity
#ጥሪማስታወቂያ
ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ
ዩኒቨርሲቲያችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቱን እየገለጸ፡ ነባር የቅድመ-ምረቃ እና የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደዉ መስከረም 5-6/2018 ዓ.ም ስለሆነ ማንኛዉም ተማሪ በአካል ቀርቦ በተጠቀሰዉ ቀነ ገደብ ዉስጥ እንዲመዘገብ እየገለጽን ከተባለዉ ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆናችንን በጥብቅ እናሳዉቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
• በ2017 የትምህርት ዘመን 1ኛ ዓመት ያጠናቀቃችሁ ተማሪዎች የትምህርት ክፍል ምርጫ የሚካሄደዉ መስከረም 06/2018 ዓ.ም እና ዉጤታችሁ ደግሞ የሚገለጸዉ መስከረም 08/2018 ዓ.ም ይሆናል፡፡
• የቅድመ ምረቃና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች ትምህርት ከመጀመሩ በፊት በ(e-SHE) የተዘጋጀዉን (student Success Suit (SSS)) ሥልጠና የሚትወስዱ መሆኑን ከወዲሁ እናሳዉቃለን፡፡
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 771
#WachamoUniversity
#የጥሪማስታውቂያ
ለዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ነባር መደበኛ ቅድመ ምረቃ እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ!!
የ2018 ትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚካሄደው መስከረም 8 እና 9 2018 ዓ.ም መሆኑን እየገለጽን በተጠቀሰው ቀን በአካል ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡- በ2018 ዓ.ም ወደ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለሚመደቡ እና በ2017 ዓ.ም የሪሜድያል ፕሮግራም ተከታትለው ማለፍያ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ወደ ፊት በሌላ ማስታወቂያ የምናሳዉቅ ይሆናል።
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
-------------------------------------------
1 771
#AASTU
#የጥሪማስታወቂያ
ለአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመደበኛ እና የተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ
እንኳን ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሰላም አደረሳችሁ እያለ የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያው ወሰነ ትምህርት ምግባ ከዚህ በታች በተገለጸው መሰረት የሚከናወን መሆኑን እናሳውቃለን፡
1. ሁሉም የመጀመሪያ ድግሪ እና የድኅረ-ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች - መስከረም 08-09/2018 ዓ.ም (ሃሙስ እና አርብ)
2. ሁሉም የተከታታይ መጀመሪያ ድግሪ እና የድኅረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች - መሰከረም 10-11/2018 ዓ.ም (ቅዳሜ እና እሁድ)
ማሳሰቢያ፡
1. ከተጠቀሱት ቀናት ውጭ ምዝገባ የማይካሄድ መሆኑን እናሳውቃለን።
2. ምዝገባ የሚከናወነው በአካል ነው።
3. የመጀመሪያ ድግሪ መደበኛ ተማሪዎች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) እንድታወጡ እናሳሰባለን።
@Joseph_maths_tutorial
1 771
#MattuUniversity
የጥሪ ማስታወቂያ!!
ይህ መቱ ዩኒቨርሲቲ ነባር የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ ተማሪዎች የ2018 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ መስከረም 08 እና 09 ቀን 2018 ዓ.ም መሆኑን አስታውቋል።
የ2018 ዓ.ም ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 12/2018 ዓ.ም መሆኑን ተገልጿል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
የ2018 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ አመት (አዲስ) ተማሪዎች፣ እንዲሁም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2017 የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ያጠናቀቁና የትምህርት ሚኒስቴር የማለፊያ ነጥብ ያገኙ ተማሪዎች መግቢያ ከትምህርት ሚኒስቴር የአዲስ ገቢ ተማሪዎች መረጃ እንደደረሰን ወድያውኑ የምናሳውቅ ይሆናል።
ከላይ ከተጠቀሱት ቀናት ቀድመውም ሆነ ዘግይተው የሚመጡ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
@Joseph_maths_tutorial
1 771
እስካሁን ጥሪ ያቀረቡ ዩኒቨርሲቲዎች
▪️አሶሳ ዩኒቨርሲቲ:- ሁሉም ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9
▪️ጎንደር ዩንቨርሲቲ:- ሁሉም ነባር ተማሪዎች መስከረም 5 እና 6 እንዲሁም አዲስ ገቢ መደበኛ መስከረም 7 እና 8
▪️አዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ:- ሁሉም ነባር ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9
▪️ወልደያ ዩኒቨርሲቲ :- ለጤና ሳይንስ እና እንስሳት ህክምና ክፍል ነባር ተማሪዎች መስከረም 5 እና 6
▪️አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ:- ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች መስከረም 5 እና 6 እንዲሁም ለሁሉም መደበኛና ተከታታይ ተማሪዎች መስከረም 8( በቅጣት 12)
▪️ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ:- ለሁሉም ቅድመ ምረቃ( አዲስ ገቢ ጨምሮ) እና ድህረ ምረቃ ተማሪዎች መስከረም 8 እና 9
▪️ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ :- ከremedial ውጪ ያሉ መግቢያ ቀን መስከረም 10
▪️ጂግጂጋ ዩኒቨርሲቲ :- ለአዲስ ገቢ(remedial ጨምሮ) መስከረም 5 እና 6 እንዲሁም ነባር ተማሪዎች 8 እና 9
▪️ቀብሪዳር ዩንቨርስቲ :-
ሁሉም ተማሪዎች አዲስ የሚመደቡትንም ጨምሮ መስከረም 8 እና 9
#share
#share
JOIN: @Joseph_maths_tutorial
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
