AAU - Muslim Students Union
Відкрити в Telegram
This is the official channel of AAU-MSU. Group: @aaumsu_discussion Youtube: youtube.com/@aaumsu Twitter: x.com/aaumsu12 Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303 Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1 Email: aaumsu12@gmail.com
Показати більше7 948
Підписники
Немає даних24 години
+27 днів
+76130 днів
Архів дописів
#ሚሽካት
ከበኒ ኢስራኢል ምድር ....ጧሉትና ጃሉት
ክፍል 3
አሏህ ሱብሀነ ወተዓላ አንድን ሰው(ህዝብ) አምናለሁ ስላለ ብቻ አይተወውም። ይፈትነዋል።
<< ሰዎቹ አምነናል በማለታቸው ብቻ እነሱ ሳይፈተኑ የሚተው መኾናቸውን ጠረጠሩን>>(ሱረቱል ዐንከቡት:2)
ኢማን ውድ ነገር ነው —እንደ ወርቅ ነው። የወርቅ ዋጋው የሚታወቀው በእሳት ሲፈተን እንደሆነ ሁሉ የኢማን እውነተኝነትም የሚገለጠው በፈተና ጊዜ ነው።
ጧሉት ሰራዊቱን ይዞ ወደ ጠላታቸው ተነስቷል። ምናልባት ብዙዎቹ ፈተናው ጃሉትን ሲገናኙ እንደሆነ አስበዋል። ነገር ግን አሏህ ከጦርነት በፊት ሌላ ፈተናን አዘጋጅቶላቸዋል—ወንዙን —ጣሉትም፦አላህ በወንዝ ይፈትናችኋል፣ ከእርሱ የጠጣ ሰው ከእኔ አይደለም ያልቀመሰው፣ በእጁ መዝገንን የዘገነ ሰው ብቻ ሲቀር እርሱ ከእኔ ነው አላቸው።አሁን የተጠየቁት ሰይፍ ማንሳት አልነበረም። ራሳቸውን መቆጣጠር ብቻ ከወንዙ አለመጠጣት።
አብዝሀኞቹ ጠጡ ያጧሉትን ትእዛዝ የጠበቁቶ ጥቂቶች ብቻ ነበሩ። ሰራዊቱ ቁጥሩ በእጅጉ ቀነሷል አሁን የቀሩት ፈተናውን ያለፉት ብቻ ናቸው። ሌላ ፈተና ደግሞ መጣ.... ጃሉትና ብዙሃኑ ሰራዊቱ የጠላት ብዛት አዩ፤የራሳቸውንም ጥቂትነት ተመለከቱ ።
ከፊሎችም በጃሉትና ሰራዊቱ ላይ አቅም እንደሌላቸው አሰቡ።
<<قَالُوا لَا طَاقَةَ لَنَا الْيَوْمَ بِجَالُوتَ وَجُنُودِ>>
«ጃሉትንና ሠራዊቱን በመዋጋት ለኛ ዛሬ ችሎታ የለንም» አሉት፡፡
እነዚያ በእምነታቸው የጸኑት፣ ጌታቸውንም እንደሚገናኙ የጠረጠሩት ሁኔታውን በሌላ መንገድ ነበር ያዩት።ምላሻቸው እንዲህ ነበር፦
<<كَم مِّن فِئَةٍ قَلِيلَةٍ غَلَبَتْ فِئَةً كَثِيرَةً بِإِذْنِ اللَّهِ وَاللَّهُ مَعَ الصَّابِرِينَ >>
«ከጥቂት ጭፍራ በአላህ ፈቃድ ብዙን ጭፍራ ያሸነፈች ብዙ ናት፤ አላህም ከታጋሾች ጋር ነው»
ጉዳዩ ስንት ነን አይደለም! አሏህ ከማን ጋር ነው!?የሚለው ነው።
ሀቅ ላይ ነን? ተበድለናል?ተገፍተናል?ትክክለኛ መመካትን በአሏህ ላይ ተመክተናል?በቃቃቃቃ አብሽሩ
إن الله معنا
ይህ ነው የአማኝ መለያ የብዛቱ ማነስ አያስፈራውም
ምነኛ ያማረ ንግግር ነው??
የአሏህ መልክተኛ: ከልብ ጓደኛቸው ጋር ዋሻ ውስጥ ሆነው በዛ አጣብቂኝ ሊያበቃላቸው በሚመስል ሁኔታ ላይ አትዘን አሏህ ከኛ ጋር ነው ሲሉት
ምነኛ ያማረ ንግግር ነው??
ኢብራሂም:እሳት ፊት ሆኖ ጌታዬ በቂ ነው ሲል
ምነኛ ያማረ ንግግር ነው??
ሙሳ: ተከታዮቹ አለቀልን ባሉት ጊዜ ጌታዬ ከኔ ጋር ነው ሲል
ምነኛ ያማረ ንግግር ነው??
ሀጀራ: በዚያ በረሃ አሏህ አይተውኝም ስትል
ያ ኡመተ መሀመድ!!ፅናታችን፣ኢማናችን፣በአሏህ ላይ ያለን እምነት እንጂ ቁጥራችን ነፃ አያወጣንም!።
ይቀጥላል .....
@aaumsu
ትምህርት ቅንጦት አይደለም
~
ያ ኡመተል ኢስላም! ልጆችህን ትምህርት አስተምር። ካልሆነ ግን በገዛ ምድርህ ባይተዋር ትሆናለህ። ካልሆነ ግን ሌላው በተቋም እና በመዋቅር ሲዋጋህ አንተ በለቅሶ ነው የምትከላከለው። ካልሆነ ግን በገዛ ቀየህ ላይ "የእስላም አገሩ መካ፣ የአሞራ አገሩ ዋርካ" ይተረትብሃል። ካልሆነ ግን ግብር የምትከፍልበት ተቋም የምትወገርበት ዱላ ይሆናል። ካልሆነ ግን ለሚደርስብህ መድሎና መገለል ምላሽህ ለቅሶ ብቻ ይሆናል። ካልሆነ ግን መብትህን የምታገኘው ሌሎች ሰፍረው ለክተው በሚሰጡህ መጠን ብቻ ይሆናል። ካልሆነ ግን በአስተማሪነት፣ በሰራተኝነት በሚመጡ አካላት በገዛ ቀየህ ላይ የባህል ወረራ ይፈፀምብሃል። ማንነትህ ይደባለቃል።
አለመማር አንድምታው ብዙ ነው። አላስተምርም ካልክ ሚሽነሪ ገብቶ ልጆችህን በትምህርትና በጤና አገልግሎት ስም ይወስድልሃል። እነ ላጲሶ የሚሸነሪ ሰለባዎች ናቸው። አላስተምርም ካልክ ሴረኛ ፖሊሲዎችና ደንቦች እየተረቀቁ ከንግዱ ሴክተር ሳይቀር በካልቾ ትባረራለህ። አላስተምርም ካልክ ታሪክህን እያወላገደ፣ እምነትህን እያንጋደደ ለሚያጠለሽ አካል ቦታውን ትለቃለህ። አለመማር በጤናው፣ በፀጥታው፣ በአስተዳደሩ፣ ... ሴክተር የሚኖረው ክፍተት ከምናስበው በጣም የራቀ ነው። በዚህ ዘመን በስልኩ የተላከለትን መልእክት የማያነብ፣ የሰፈሩ አጥር ላይ የተለጠፈን ማሳሰቢያ የማያውቅ፣ ባንክ ቤት ገብቶ ስሙን መፃፍ አቅቶት ሰው የሚጠብቅ ወጣት ማፍራት እጅግ አደገኛ ነገር ነው። አስተምር ልጆችህን። በትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ችግሮችን ልጆችህን በማራቅ አትፈታቸውም። አንተ ራስህን ካራቅክላቸው በኋላ ላንተ በመቆርቆር ምቹ ከባቢ አደላድለው ይጠሩኛል ብለህ እንዳትጠብቅ። ይልቁንም እየተማርክ፣ እያስተማርክ ታገል። ጎን በጎን ክፍተቶችን በራስህ በቤትህ ወይም ተደራጅተህ ሙላ። ብታስተምር ይሻልሃል!
ልጆችህን አስተምር። በተለያዩ የዓለም ጫፎች የምንሰማቸው ሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ግፎች አንዱ ምክንያታቸው የተራቀቁ ቴክኖሎጂዎችን እና ጠላትን መገዳደር የሚያስችሉ ዘመኑን የዋጁ የጦር መሳሪያዎችን ማምረት ላይ ስለሌለን ነው። እነዚህ ቴክኖሎጂዎችና የተራቀቁ የጦር መሳሪያዎች ደግሞ የዘመናዊ ትምህርት ውጤቶች ናቸው። ጠላት እጅግ አውዳሚና ጅምላ ጨራሽ፣ አህጉር አቋራጭ መሳሪያ እስከ አፍንጫው ታጥቆ ሳለ አንተ በኮንትሮባንድ ያገኘኸውን ጥቂት ክላሽንኮቭ ይዘህ እንገጅ እንገጅ ብትል ውጤቱ የትም የማይደርስ ሰሞንኛ መፈራገጥ ብቻ ነው የሚሆነው።
ባጭሩ ስለ ትምህርት ሲወራ ስለ ቅጥር እንጀራ ብቻ አናስብ። የመማር ትርጉሙ ከዚያ ያለፈ ነው። ስለ ትምህርት ሲወራ ከአንድ ከሁለት አቅጣጫ ብቻ መመልከት አይገባም። መማርም፣ አለመማርም ተጽእኗቸው መልኩም አይነቱም ብዙ ነው። በሚያሳዝን ሁኔታ አካባቢያችን፣ ወገናችን ከሌሎች በትምህርት ወደ ኋላ እንዳይቀር እንዴት የተሻለ ስራ እንስራ በሚል ልንመካከር በሚገባን ጊዜ ከፊሉ ገና የመማርን አስፈላጊነትና ያለመማርን አደጋ ለመረዳት ማገዶ እየፈጀ ነው ያለው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 10/2017)
@aaumsu
ወደ ዩኒቨርሲቲ ለምትገቡ አዲስ ተማሪዎች፦
ከላይ የተቀመጠው መረጃ የየዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎችን መረጃ የያዘ ሲሆን በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች በመደወል ስለ ዩኒቨርስቲዎቹ፤ ጀመዓዎች እንዲሁም ሌሎች መረጃዎች መጠየቅ ትችላላችሁ።
አላህ ለስኬት መሠረት የሆነን ቆይታ ያድላችሁ።
©EHEMSU
@aaumsu
ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችን:-
በመጀመሪያ የአላህ ሰላም እዝነት እና ረድዔት በእናንተ ላይ ይሁን። ምስጋና ሁሉ ሁሉንም ችግር አልፋችሁ በውጤት ለእዚህ ስኬት እንድትበቁ ላስቻለው ጌታችን አላህ የተገባ ይሁን። እንደ አንድ ሰውነት ሆነን እንድንደጋገፍ እና እንድንረዳዳ ባስተማሩን አዛኙ ነብይ ላይም የአላህ ውዳሴ እና ሰላም ይስፈን።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ሙስሊም እህት ወንድሞቹን በኢስላማዊ ፍቅር እና እንክብካቤ አቅፎ ለማስተናገድ ዝግጅቱን አጠናቋል። ስለሆነም እናንተ እህት ወንድሞቻችን ከምንም በላይ ከደም በላይ የሚያጋምደንን የኢስላም እህት ወንድማማችነት በማሰብ ማንኛውም የምትፈልጉትን መረጃ እና እገዛ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በኩል ትጠይቁ ዘንድ እንጠይቃለን።
📌 AAU MUSLIM STUDENTS UNION - 0909524252
Main and FBE Campus
📌 አሊፍ ሓጂ - Main Campus - 0955942642
AAiT (5 Kilo) Campus
📌 ሙሐመድ አብራር - AAIT - 0953442423
4 Kilo Campus
📌 አይመን ሙሐመድ - 4kilo - 0977207747
Sefere Selam Campus
📌 አብዱልዓዚዝ ዩሱፍ - s.selam campus - 0951907014
Ldeta Campus
📌 አብዱልዓዚዝ ጁማቶ - Ldeta Campus - 0961497962
Tikur Anbessa Campus
📌 አይመን ሚፍታህ - Tikur Anbessa Campus -
0977777095
Bishoftu Campus
📌 መነልከሪም አብዱልጀባር - Bishoftu Campus -
0917962262
https://t.me/aaumsu
If you lost the location or training place, you can call to:
0956053643
■ They are waiting for you to come up!!
ደጋግሜ ብየዋለሁ የሆነ ተቋም መብታችሁን ቢነፍግና ቢከለክል ምን ልታደርጉ ነው? ልትሸሹ?! ልትተዉ?! ሌላ ቦታ፤ ሌላ ሀገር፤ ሌላ ተቋም፤ ሌላ ዩኒቨርስቲ ልትፈልጉ?!!!! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኒቃብ ይከለክላል ወይ? ኒቃብ የማይከለከልበት ዩኒቨርስቲ የቱ ነው? ሶላትስ? ጀለብያስ? ቁርዓንስ? ሌላም ሌላም እያሉ የሚጠይቁ ብዙ ናቸው። የእኔ ጥያቄ ደግሞ ከላይ እንዳልኩት እዚህ ስለተከለከለ ጅቡቲ ወይንም ሴኔጋል ሄዳችሁ ልትማሩ ነው?!
ሰዎች፦ ኢትዮጵያኮ ሀገራችሁ ናት። እነዚህም ተቋማት በእናንተ ግብር እና ላብ የተገነቡ ናቸው። ሌላው ቢቀር በበደል ላይ እንዲዘወተር ስላደረጋችሁ በአላህ ፊት እንጠየቃለን ብላችሁ አታስቡም?! እስልምና ደግሞ ሀይማኖታችሁ ነው። በር ላይ ጥለነው የምንገባው ሀይማኖት አይደለም። እንድንኖረው ነው የታዘዝነው። እንኖረዋለንም።
ቀደምቶች ባደረጉት ትግል አሁን ላይ ያለው ሁኔታ የተሻለ ቢሆንም አሁን ያለው ሁኔታ እንዲፀና፤ የተሻለ ጊዜም እንዲመጣ መትጋት ግዴታችሁ ነው። ያለፈው ትውልድ የከፈለው ዋጋ ለእናንተ አማና ነው። ቀጣዩ ትውልድ በተሻለ ይኖር ዘንድ ደግሞ እናንተም አማና አለባችሁ። በዚያ ልክ አስቡ። ሁላችንም መንገደኞች ነው። የዚህ አለም ሰዎች አይደለንም። ያማረች ዱንያን ሰርተን እናልፍ ዘንድ እናልም።
©️
@aaumsu
በቦሌ ቡልቡላ ከሚገኘው አንሷር መስጂድ ከተላለፈ የኹጥባ መልዕክት፦
በቅርብ ቀናት ውስጥ የሚገኙት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተለይም ምክንያቶች ሃይማኖታቸውን፣ የሃይማኖታቸውን ድንጋጌ እንዳይስፋፋ የሚገፉ፣ ከትምህርት ማዕከል ራሳቸውንም፣ ቤተሰቦቻቸውንም ሃገራቸውን እንዳይመጥኑ ከሚያደርጉት ጥረት፣ ከሚያደነቃፏቸው አካላት አላህ ሱብሃነ ወተዓላ እንዳያግዛቸው በምንችለው ነገር ሁሉ በሃሳባችን፣ በምክራችን እንዲሁም በዱዓችን እነሱን ማገዝ ይገባናል። ይህ በእኛ ላይ ትንሹ ግዴታ ነው።
@aaumsu
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ያስተላለፋት መልዕክት:
አሰላም አለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካትሁ
ቢስሚላህ በመጀመሪያ ጥሪያችንን አክብራችሁ በመገኘት ወንድም ሱደይስ፣ አብዲ ኮርማ፣ አብሮን ሊታደም ያልቻለውን ዶ/ር አብዱሰላምን ጨምሮ፣ እንዲሁም መላው ተሳታፊ ወንድም እና እህቶች በአላህ ስም እጅግ አድርገን እናመሰግናለን።
በመቀጠል እኛ እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ እና ተማሪዎቻችን ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓ ያለፈ ( ከኮሮና ጀምሮ እስከ ረመዳን 2017) የትግል ጉዞ ብዙ የወሰድናቸው ትምህርቶች አሉ። ከዛም መካከል አንድ የወንድማችን ንግግር ማስታወስ እወዳለሁ፡
ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር): "ችግር ሲመጣ ሌላ የሚፈታ አካል እንዲመጣ መፈለግ ሳይሆን "እኔ አለሁለት!" የሚል አቋም ሊኖራችሁ ይገባል።" የሚለው ምክራቸው ሁላችንም ልብ ውስጥ ተቀምጧል ብዬ አስባለሁ።
አጠቃላይ በእንቅስቃሴያቸው ውስጥ የነበረው ጥንካሬ እና ህብረት እጅግ የሚያስደንቅ ነው። በአላህ ፈቃድ ትግል ካለ ድል እንደሚመጣ ህያው መስክር ሆኖ ቀርቦልናል።
ይህንን ተከትሎ ጀመዓችን ወይም አአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ጅማ ላይ ጀግንነት እና ቁርጠኝነት ባሳዩት ወንድም እና እህቶች እንዲሁም በጀማአቸው ስም ስጦታ ማበርከት ይፈልጋል። ስጦታውንም በአዲሱ ዓመት መግቢያ ፕሮግራም ላይ አሚሮች መጥተው ይቀበሉ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።
ሙሐመድ ኢድሪስ
ፕሬዝዳንት
@aaumsu
የምስጋና እና አክብሮት መልዕክት ከቀድሞ የጅማ ዩኒቨርሲቲ (አግሪ ግቢ) አሚር አብዲ ኮርማ የተላለፈ ፦
በቅድሚያ ለሁላችሁም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። በአላህ ፈቃድ በግልም ሆነ በህብረት ለሰራችሁት ትልቅ ስራ፣ በተለይም ደግሞ ሌሎች ሰዎችን በማነቃቃት እና በማበረታታት በኩል ለነበራችሁ ሚና የከበረ ምስጋና እና አክብሮት አለኝ። አላህ በቀጣይም ለሌሎች ችግሮች መፍትሔ እንዲያደርጋችሁ እመኛለሁ።
በ 2016/17 ዓ.ል በነበረው ፈታኝ ወቅት፣ በቀንም ሆነ በሌሊት የ 24 ሰዓት መረጃዎችን እና ጥሪዎችን በመለዋወጥ፣ ምክር እና ድጋፍ በመስጠት አብራችሁን ስትታገሉ ነበር። ምስጋና ከሁሉም በላይ ለሆነው ለአላህ ይሁን፤ ከእሱ በመቀጠል ግን እናንተ መንገድ በማሳየት እና በመደገፍ ላበረከታችሁት አስተዋጽኦ ትልቅ ክብር ይገባችኋል። ውጤት የሚመጣው እንዲህ አይነት አንድነት እና ድምር ጥረት ሲኖር ነው!
በተለይም በወቅቱ በተማሪዎች ግሩፕ ውስጥ የነበሩ አባላት ያሳዩት ትልቅ አንድነት የሚደነቅ ነበር። ያንን ውስብስብ ሁኔታ ለመፍታት ከ Remedial እስከ GC ተማሪዎች ድረስ ወንዶች ብቻ ሳይሆኑ እህቶችም ጭምር እጅ ለእጅ ተያይዘው ትልቅ እገዛ አድርገዋል።
በዚህ አጋጣሚ ለሰራችሁት ሁሉ ጀዛኩሙላሁ አህሰነል ጀዛእ እያልኩኝ፣ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAU MSU)፤ እና ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ለሆኑት ወንድማችን ሙሀመድ አሚን ካሳው በወቅቱ ላሳዩት የስራ አመራር፣ ላደረጉት ያልተቋረጠ ድጋፍ እና አብሮነት የላቀ ምስጋናዬን እና አክብሮቴን ማቅረብ እወዳለሁ።
በመጨረሻም፣ ይህ አዎንታዊ ተሞክሮ እና ህብረት በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ዘንድ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና አብረን መስራት እንድንችል መልእክቴን አስተላልፋለሁ። ጠንክሩ!
@aaumsu
ሕያው ምስክር - 2
የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል!
አቅራቢ፦ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)
አዘጋጅ፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !!
@aaumsu
Please note that the exam has been rescheduled to Friday, September 18, instead of September 21.
Don't forget to bring A4 size paper and pencil for the consultation.
🔖Thursday Sep 17, morning at 3:00 LT.
+9
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን በ Self sponsorship የተመዘገቡ ተማሪዎች ወደ የትምህርት መስኮች መግቢያ ነጥብን ይፋ አድርጓል።
@aaumsu
ለ2019 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመደበኛው መርሃ ግብር ለመማር ቅበላ ላገኛችሁ የአንደኛ ዓመት ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ
ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትመጡ ተማሪዎች መስከረም 06 እና 07 2019 ዓ.ም በየተመደባችሁበት የዩኒቨርስቲው ካምፓሶች በመገኘት ሪፖርት እንድታደርጉ ያሳውቃል፡፡ ተማሪዎች ለምዝገባ ስትመጡ
1. የአስራ ሁለተኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውንና ኮፒ፣
2. አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
3. የማደሪያ ምድብ (Dormitory) ለተሰጣችሁ ብርድልብስና አንሶላ እንዲሁም የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ ያስታውቃል፡፡
4. ከአዲስ አበባ ውጪ ለምትኖሩ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው የተመደበላችሁን የመኝታ ክፍል የዩኒቨርሲቲውን የመግቢያ ፈተና በተፈተናችሁበት UGA2019…. ቁጥር በመጠቀም ከታች ባለው ሊንክ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡ https://portal.aau.edu.et/NewStudents/DormitoryPlacement
5. በተጠቀሱት ቀናት (መስከረም 06 እና 07) ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚመጡ ተማሪዎች በመርካቶ አውቶብስ ተራ፣ በላም በረት፣ በአቃቂ እና በአስኮ የመኪና መናኸሪያዎች እንዲሁም በቦሌ የአገር ውስጥ አውሮፕላን ጣቢያ ዩኒቨርስቲው ወደ አዲስ አበባ እና ቢሾፍቱ ወደሚገኙት ካምፓሶቻችን የትራንስፖርት አገልግሎት የሚያቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
6. ነዋሪነታችሁ አዲስ አበባ ከተማ ሆኖ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅበላ ያገኛችሁ ተማሪዎች ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎችና ዶክመንቶች ይዛችሁ ሪፖርት የምታደርጉት መስከረም 07 ቀን 2019 ዓ.ም መሆኑን ያሳውቃል፡፡
7. ለሁሉም ተማሪዎች አጠቃላይ ስለ ዩኒቨርስቲዉ ገለፃ የሚደረገዉ ዐርብ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም ይደረጋል፡፡
8. ዘግይቶ የትምህርት ኮርሶች ምዝገባ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ም ሲሆን
9. የ2019 ዓ.ም የመጀመሪያዉ ሴሚስተር ትምህርት የሚጀመረዉ መስከረም 11 ቀን 2019 ዓ.ም ይሆናል፡፡
10. ስለመቁረጫ ነጥብ ስለምዝገባ ሂደቶች በተመለከተ እና ተጨማሪ መረጃ ከታች ካሉት ሊንኮች ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን::
Ø https://portal.aau.edu.et/NewStudents/Welcome
Ø www.aau.edu.et
Ø https://t.me/aauGAT
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር
@aaumsu
የኒቃቢስቷ መልዕክት!
ከአል-በያን ገጾች የተወሰደ...
የሰው ልጅ በሚኖርበት ምህዋር ውስጥ ይህቺ የሚኖርባት አለም: አለም ሆና ማንነቷን ይዛ ትቀጥል ዘንድ ሚናቸውን የተወጡ ብዙ ትናንሽ አለሞች አሉ። እምነት በራሱ አለምን አለም ያደረጋት አንዱ ግብአት ነው። ከእምነት ውስጥ ደግሞ እስልምና የአለሞች ሁሉ ውብ አለም ነው። ሰላት፣ ዱአ፣ ኢባዳ፣ ሰደቃ ፣ መሃባ እና ብዙ ደግሞ ኢስላምን ውብ የሆነ አለም አድርገው ያቆሙት የኢስላም የተዋቀሩ ጌጦች አሉ።
እነዚህ የተሰደሩ የሆኑ ጌጦች በጥንቃቄ እየተጠበቁ ካልቀጠልን የአንዱ ጌጥ መውጣት ስርዓተ-ጥለቱን ያጠፋል። የዲናችንን ውበትም ያደበዝዛል። ቀስ በቀስ እየተሸረሸረ ደግሞ ሌሎች ጌጦቻችንን አውድሞ ከአለሞች ሁሉ ደካማው አለም የሚል ስያሜን ያሰጠናል።
ወዳጄ!! አለም ላይ ያሉ በጣም ውድ ነገሮች በሙሉ ለማንም ክፍት አይደሉም። የተሸፈኑና ከዛም በላይ በጥበቃ ውስጥ ያሉ ናቸው። ኢስላም ሴትን በሂጃባ ወይም በኒቃቧ ሊጠብቃት ኖሯል። ኒቃብ ጨርቅ ቢመስልም ከጨርቅ በላይ ነው። የኢስላም 1 ጌጥ፣ መጠበቂያ፣ መታወቂያ፣ መከበሪያ፣ የሴትነት ክብር መገለጫም ጭምር ነው። አንድን ሰው ኒቃብ ጠል ሆኖ ስታገኘው ጨርቅ ጠል ሆኖ ሳይሆን ጥብቅነትን፣ ስርአትንና ኢስላምን ጠልቶ ነው። እናም ጥላቻውን፣ ግፉንና በደሉን እሰየው ብለህ የተቀበልክ ቀን ሰላትህም፣ ጀማዐህም፣ መስጂድህም፣ ዲንህም ይጎዳ ዘንድ እሰየው ብለህ እንደተቀበልክ ቁጠረው። ስለዚህ ጠላት ኒቃብ አይሆንም ሲል ኢስላማ አይሆንም እንዳለ የተረዳህ ቀን ደግሞ ታጋይ መሆን ትጀምራለህ። ጥልቅ የሆነና እምነትህን የሚገባ የሆነ ቦታው ላይ ሆኖ እስክታየው ድረስ እንቅልፍ የሚነሳህ፣ ያለህበትን ሁኔታ የሚገልጥልህ፣ ያለፈውን አስታውሶ የሚያነቃህ፣ ለዲንህ ደግሞ መስዋእትነትን የሚያስከፍልህ ትግል ማለት ነው።
ወዳጄ!! እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለዲናችን መስዋእት የመሆን፣ ጠላት ፊት ቆሞ ለሞትና ለሸሂድነት ዝግጁ የመሆን ችግር የለብንም። ግን ያ ድሮ ወይ ዘንድሮም ቢሆን ለታጣቂ እንጂ ለእኛ አይሆንም። ምክንያቱም እንደምናየው በደም ትግል ውስጥ የመጡ መብቶቻችን በሙሉ ጊዜያዊ መብት እየሆኑ ተቸግረናል። ስለዚህ ልንነቃ ይገባል። ጊዜያዊ ሳይሆን ቋሚ የሆነ የትግል መስመር ሊኖረን ይገባል። በየትኛውም የህይወት እርከን ላይ ስናልፍ የሀገራችን እና የኢስላማዊ መብታችንን ሁኔታ ሳንዘነጋ ከስራችንም ከላያችንም ካለው ሙስሊም ወገናችን ጋር በየመሳጂዶቻችን፣ ስራዎቻችን እና ትምህርት ቤቶቻችን የተጠና እቅድ እና እምቅ የሆነ ኃይል ኖሮን መሃላችን ላይ ያለውን ክፍተት በሙሉ እየደፈንን ልንጓዝ ይገባል።
መልእክቴ ነቃቤ ተነክቷል፤ መማር አቅቶኛል። እርዱኝ ሳይሆን በኒቃብ ስያሜ ሊያጠቁ ያሰቡት የጋራ እስልምናችንን ነውና እንንቃ!! ነው።
@aaumsu
የ SBE ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት Architecture department መቀላቀል ለምትፈልጉ አዲስ ተማሪዎች ( 2nd year ) ለ መግቢያ ፈተና consultation እያዘጋጀ ይገኛል። እንዲዘጋጅ ትፈልጋላችሁ?
#ሚሽካት
ከበኒ ኢስራኢል ምድር ....ጧሉትና ጃሉት
ክፍል 2
የኢስራኢል ልጆች ለነብያቸው በአላህ መንገድ እንደሚዋጉ ቃል ቢገቡም ፈተናው በእውነት ሲመጣ ግን በዚያ ቃል መጽናት አልቻሉም።
<<فَلَمَّا كُتِبَ عَلَيْهِمُ الْقِتَالُ تَوَلَّوْا إِلَّا قَلِيلًا مِّنْهُمْ ۗ وَاللَّهُ عَلِيمٌ بِالظَّالِمِينَ>>
<<በእነርሱ ላይ መዋጋት በተጻፈባቸውም ጊዜ ከእነርሱ ጥቂቶች ሲቀሩ አፈገፈጉ፡፡ አላህም በዳዮቹን ዐዋቂ ነው፡፡>>
አንድን ነገር እንመኛለን፣ እንጠይቃለን፣ እንዲለወጥም እንሻለን ነገር ግን ከለውጡ ጋር የሚመጣውን ፈተና ለመቀበል ዝግጁ ነን??
ይህ ሁላችንም ልናጤነው የሚገባ ነገር ነው!።የትኛውም ድል ከመስዋትነት ጋር እንጂ አልተገኘም። ዛሬ ላይ እኛ በድሎት የምናደርጋቸው፣ ያለስጋት የምናጸባርቃቸው የዲናችን ምልክቶች ከዚህ ቀደም ብዙ አባቶችን፣ እናቶችን፣ ወንድሞችንና እህቶችን ዋጋ ያስከፈለ ነው። ዛሬ እኔ ለታናሼ፣ ለቀጣዩ ትውልድ ዋጋን ለመክፈል ዝግጁ ነኝ??
ነቢያቸውም መሪ እንዲሾምላቸው በጠየቁት መሰረት አሏህ ጧሉትን እንደሾመላቸው ይነግራቸዋል። የኢስራኢል ልጆች ግን ምርጫውን ተቃወሙ። መመዘኛቸው ሀብትና ጎሳ ሆነና ጧሉትን እንደ መሪ ለመቀበል ተቸገሩ። አላህ ጧሉትን ከእነሱ በላይ በ2 ነገሮች አስበለጠው— እውቀትና የአካል ጥንካሬን ሰጠው። በእነሱም ላይ ሾመባቸው፤ አላህም የተሻለ አዋቂ ነው።
<<وَقَالَ لَهُمْ نَبِيُّهُمْ إِنَّ اللَّهَ قَدْ بَعَثَ لَكُمْ طَالُوتَ مَلِكًا ۚ قَالُوا أَنَّىٰ يَكُونُ لَهُ الْمُلْكُ عَلَيْنَا وَنَحْنُ أَحَقُّ بِالْمُلْكِ مِنْهُ وَلَمْ يُؤْتَ سَعَةً مِّنَ الْمَالِ ۚ قَالَ إِنَّ اللَّهَ اصْطَفَاهُ عَلَيْكُمْ وَزَادَهُ بَسْطَةً فِي الْعِلْمِ وَالْجِسْمِ ۖ وَاللَّهُ يُؤْتِي مُلْكَهُ مَن يَشَاءُ ۚ وَاللَّهُ وَاسِعٌ عَلِيمٌ>>
<<ነቢያቸውም ለእነርሱ፡- «አላህ ጧሉትን (ሳኦልን) ንጉሥ አድርጎ በእርግጥ ላከላችሁ» አላቸው፡፡ (እነርሱም)፡- «እኛ ከእርሱ ይልቅ በንግሥና ተገቢዎች ስንኾን ከሀብትም ስፋትን ያልተሰጠ ሲኾን ለእርሱ በኛ ላይ እንዴት ንግሥና ይኖረዋል?» አሉ፡፡
(ነቢያቸውም)፡-«አላህ በእናንተ ላይ መረጠው፡፡ በዕውቀትና በአካልም ስፋትን ጨመረለት፡፡ አላህም ንግሥናውን ለሚሻው ሰው ይሰጣል፡፡ አላህም ችሮታው ሰፊ ዐዋቂ ነው» አላቸው፡፡>>
ነብያቸውም ጧሉት በእርግጥ ከአሏህ የተመረጠ ንጉስ መሆኑን የሚያሳየው ምልክት ከሙሳና ከሀሩን ቤተሰቦች ቅሪት፣ ከጌታቸውም ሰኪና የሆነውን ታቦት ወይም ሳጥን ማስመለሱ መሆኑን ነገራቸው።
<<وَقَالَ لَهُمْ نَبِيُّهُمْ إِنَّ آيَةَ مُلْكِهِ أَن يَأْتِيَكُمُ التَّابُوتُ فِيهِ سَكِينَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَبَقِيَّةٌ مِّمَّا تَرَكَ آلُ مُوسَىٰ وَآلُ هَارُونَ تَحْمِلُهُ الْمَلَائِكَةُ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لَّكُمْ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ>>
ነቢያቸውም ለእነርሱ፡- «የንግሥናው ምልክት ከጌታችሁ የኾነ እርጋታ የሙሳ ቤተሰብና የሃሩን ቤተሰብ ከተውትም ቅርስ በውስጡ ያለበት መላእክት የሚሸከሙት ኾኖ ሳጥኑ ሊመጣላችሁ ነው፡፡ አማኞች ብትኾኑ በዚህ ለእናንተ እርግጠኛ ምልክት አልለ» አላቸው፡፡
ጧሉትም በአሏህ መንገድ ሊጋደል ሰራዊቱን ይዞ ወጣ...እስከ መጨረሻው ማን በአሏህ መንገድ ይፀናል??
ይቀጥላል ....
@aaumsu
+8
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ከደሴ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመሆን "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ከትላንት እስከ ዛሬ!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጁት ታላቅ የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ተካሄደ።
በመድረኩ ከሸይኽ ሙሐመድ አንሲ ነፍስን የሚያናግሩ እና ለሕይዎት ስንቅ የሚሆኑ ምክሮች ተላልፈዋል። በወንድም ሙሐመድአሚን ካሳው ስለሙስሊም ተማሪዎች ውጣወረድ እና መፍትሄዎቻቸው ዳሰሳ ቀርቧል።
መድረኩ በደቡብ ወሎ ዞን ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ስራ አስኪያጅ ዶ/ር ሐሰን አህመድ የተመራ ሲሆን ከታዳሚዎችም ጋር ገንቢ ውይይቶች እና የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደዋል።
@aaumsu
ከበኒ ኢስራኢል ምድር ....ጧሉትና ጃሉት
ክፍል 1
ጊዜው ከሙሳ ዐለይሂ ሰላም በኋላ ነው፤ የኢስራኢል ልጆች በሙሳ መንገድ ፀንተው በተወራትም ህግጋት ሲመሩ ነበር። ዘመናት በራቀ ቁጥር ግን ቀልቦቻቸው ደረቁ፤ በዲናቸውም አዳዲስ ነገሮችን አስገቡ፤ ከፊሎቻቸውም ጣኦታትን ማምለክ ጀመሩ። ከክፋታቸው ይመለሱ፣ በመልካም ይታዘዙ፣ ከክፉም ነገር ይታቀቡ ዘንድ እንዲሁም በመካከላቸው በተውራት ህግጋት እንዲፈርዱ አሏህ መልእክተኞችን አከታትሎ መላክን ቀጠለ።
ቀደም ባለ ጊዜ የኢስራኢል ልጆችን የሚዋጋ ሁሉ ይሸነፍ ነበር። ምክንያቱ ደግሞ ከአላህ ጋር በቀጥታ ከተነጋገሩት ሙሳ ዐለይሂ ሰላም ጀምሮ ከትውልድ ወደ ወደ ትውልድ ሲወራረሱት የነበረ ተውራትና ታቦትን ይዘው ስለነበር ነው። (ይህ ሲባል ታቦቱ /ሳጥኑ ውስጥ የሙሳ እና ሀሩን ቅርስ የነበረ ሲሆን ጦርነት ሲሄዱ ተሸክመውት ሄደው ከአላህ በሆነ ተአምር በርሱ በረካ ነስርን ያረጋግጥላቸው ነበር)
የኢስራኢል ልጆችም እነዚያን ክፉ ስራዎች መፈጸማቸውን በቀጠሉ ጊዜ አላህ ጠላቶቻቸውን በእነርሱ ላይ ሾመባቸው። ብዙዎች ጦር ሜዳ ላይ አለቁ፣ ልጆቻቸው እና ሴቶቻቸው ተማረኩ፣ጠላቶቻቸው በሀገራቸው ሰፊ ክፍሎችን ተቆጣጠሩ፡፡
ነገሩ እንዲህ ነው በቃ የአንድ ህዝብ ልቅናውም ሆነ ውድቀቱ ሚጀምረው ለጌታውን ትእዛዝ ከሚሰጠው ቦታ ነው።አሁን ላለንበት የበታችነትና በካፊሮች እጅ ስር መጨፍደድ አንዱ ምክንያት ከአሏህ መራቅ ነው።ሙስሊሙ ውጥንቅጡ ወጥቷል፤ ከቁርአን ብርሀን፣ ከነብዩም፣ ከሰሀቦቻቸው፣ ከድንቅ ተተኪዎችም በኋላ መርህ እንደሌለው ተራ ሰው ዘቀጥን ዱንያም ዋጠችን...ውጤቱንም እንደምናየው ነው– በየቦታው ችግራችን በዛ ከብዛታችንም ሀይል አጣን ተዳከምን።
የኢስራኢል ልጆች ታቦቱንና ተውራትን በአንድ የጠላት ንጉስ እስኪያስነጥቁ ድረስ በጥመት መቀጠላቸውን አላቆሙም ነበር። ከዚህም በኋላ ከመካከላቸው አንድን ነብይ አሏህ ላከ። ወደ አላህ እርሱን ብቻ እንዲያመልኩ እንዲጠራ አዘዘው። ነብያቸውም የኢስራኢል ልጆችን ወደ አላህ ጠራቸው።እነርሱም በመካከላቸው ንግስና አብቅቶ ነበርና ጠላቶቻቸውን በእርሱ መሪነት በአሏህ መንገድ ለመዋጋት አንድን ንጉስ እንዲሾምላቸው ጠየቁ።
<<أَلَمْ تَرَ إِلَى الْمَلَإِ مِن بَنِي إِسْرَائِيلَ مِن بَعْدِ مُوسَىٰ إِذْ قَالُوا لِنَبِيٍّ لَّهُمُ ابْعَثْ لَنَا مَلِكًا نُّقَاتِلْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ>>
"ከኢስራኢል ልጆች ከሙሳ በኋላ ወደ ነበሩት ጭፍሮች ለነቢያቸው ፡- «ለእኛ ንጉሥን አስነሳልን በአላህ መንገድ እንዋጋለን፤» ባሉ ጊዜ አላየህምን? (አላወቅህምን?)"
ነብያቸውም እንዲህ አላቸው:-
<<قَالَ هَلْ عَسَيْتُمْ إِن كُتِبَ عَلَيْكُمُ الْقِتَالُ أَلَّا تُقَاتِلُوا ۖ>>
"ከአሏህ ዘንድ በግዳጅነት ቢፃፍባችሁ ላለመዋጋት ትሻላችሁን??"
<< قَالُوا وَمَا لَنَا أَلَّا نُقَاتِلَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَقَدْ أُخْرِجْنَا مِن دِيَارِنَا وَأَبْنَائِنَا>>
"ከሀገሮቻችን እና ከልጆቻችን የተባረርን ስንሆን በአላህ መንገድ የማንዋጋ ለእኛ ምን አለን?" በማለትም መልሱ
መሪ እንዲሰጣቸው ጠየቁ.....ነገር ግን ፈተናውን ለመቀበል ዝግጁ ነበሩ ይሆን!?
ይቀጥላል....
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በGovernment Sponsorship መግባት ለሚፈልጉ ተማሪዎች የመግቢያ ነጥብን ይፋ አድርጓል። በዚሁ መሰረት፦
📌 ለNatural Science፡ 76.17
📌 ለSocial Science: 58.75
ውጤት የሚሰላው 50% Entrance exam፤ 50% UAT በማድረግ ከ100% ይሆናል።
@aaumsu
