AAU - Muslim Students Union
الذهاب إلى القناة على Telegram
This is the official channel of AAU-MSU. Group: @aaumsu_discussion Youtube: youtube.com/@aaumsu Twitter: x.com/aaumsu12 Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303 Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1 Email: aaumsu12@gmail.com
إظهار المزيد6 565
المشتركون
+3624 ساعات
+737 أيام
+1 04230 أيام
أرشيف المشاركات
የፓናል ውይይት ስለ መብቶቻችን
- የዚህ ታላቅ ታሪካዊ ዝግጅት አካል እንሁን
ነገ እሁድ ጠዋት 2:30 ወደ ጦር ሀይሎች (ረያን መስጅድ)
- ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል !
@aaumsu
ነገ አይቀርም!
እኔ አልቀርም ... እርስዎስ?!
ሙሐመድአሚን ካሳው ... የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፕሬዚዳንት ! ! !
አንድ ቀን ብቻ ቀርቷል __ ለታሪካዊው ቀን ...
ከላይ ያለው ምስል ስቶሪ ይደረግ ... ከፕሮፋይልም ይቀመጥ ! ! !
ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ከ100 በላይ ኪሎሜትሮችን ተጉዘው ሊታደሙ የሚመጡ አሉ። በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ተማሪዎች በፕሮግራሙ ለመታደም ይመጣሉ። የመድረሳ ተማሪዎች፤ የሀይስኩል ተማሪዎች፤ የኮሌጅ ተማሪዎች፤ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፤ እናት አባቶቻችን፤ እህት ወንድሞቻችን፤ ኡስታዞቻችን፣ መሾይኾች፣ ሁሉም ስለአንድ አላማ በአንድ መድረክ ይሰባሰባሉ።
የታሪክ ምሁሩ አብዱልጀሊል በታሪክ ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰውን ያብራራል ... የሕግ ፕሮፌሰሩ ዘላለም እየተጣሱ ስላሉት መብቶች ከሕግ አንፃር ያለውን እውነታ ያስቃኛል ... ኡስታዝ ሺሃቡዲን ሸህ ኑራም በእንዲህ አይነት ሁኔታዎች ውስጥ የእኛ ሚና ምን መሆን እንዳለበት ያስቀምጣሉ። ስለ አሁኑ እና ስለወደፊቱ ከተማሪዎች በኩል ያለውንም እናደምጣለን።
ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል
እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ
ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ
ከላይ ያለውን ምስል ስቶሪ አድርጉ ... ከፕሮፋይላችሁ ላይም አስቀምጡት ! ! !
የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች
ከፓናሊስቶቻችን 3 - ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸይኽ ኑራ!
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በባህርዳር ዩኒቨርስቲ በሰሩበት ወቅት የጀመዓው አሚር ነበሩ። የዚያኔ ስለሙስሊም ተማሪዎች የታገሉ ሲሆን ደማቅ አሻራን አሳርፈው አልፈዋል። ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች በማምራትም የተለያዩ ድግሪዎችን ሰርተዋል። በአራት የተለያዩ ዲፓርትመንቶች የማስተርስ ዲግሪ አላቸው። በአሁኑ ሰዓትም የPHD ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነው።
ከዚህም ባሻገር የአዲስ አበባ መጅሊስን በምክትል ፕሬዚዳንትነት፤ ኢምፓክት ሜከርስ ፋውንዴሽንን በዳይሬክተርነት እየመሩ ጉልህ አስተዋፅዕ በማበርከት ላይ ናቸው። ለተለያዩ ተቋማትም የአመራርነት ስልጠናን በመስጠት ብቁ መሪዎች ይኖሩ ዘንድ ተግተው እየሰሩ ነው።
ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸህ ኑራ
የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ ፓናሊስት ናቸው።
ቀጠሯችንን ከዚያው እናድርግ። በሰዓቱ እንገኝ! ለተሻለ ነገ መሠረት የምንጥልበትን ዛሬ እንያዝ!!
ዝግጁ ?! የኢማም አሕመድ ልጆች ዝግጁ?! የጦልሓ ጀዕፈር ምትኮች ዝግጁ?! የኡሙአይመን ልጆች _ ዝግጁ?!!!
@aaumsu
የፓናሉ መሪ _ ዲኑ ዓሊ !
የሚዲያ ባለሙያ ነው። በሙስሊሞች ላይ አንዳች የመብት ጥሰት ሲፈፀም ከፊት ለፊት ይገኛል። ኸይር ፈላጊ የሚልን ተቋም አቋቁሞ ማህበረሰቡን በማስተባበር ብዙ መስጂዶችን እና መድረሳዎችን ገንብቷል። በርካታ የውሐ ጉድጓዶችንም በገጠሩ የሀገራችን ክፍል በማስቆፈር ለብዙዎች ደርሷል።
ከዚህም ባሻገር በተለያዩ ኸይር ስራዎች ተፅዕኖ ሲፈጥር ይታወቃል። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ የፓናሉ መሪ ሆኖ ቀርቧል። እሁድ ሰኔ 7 / 2018 ዓ.ል ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ በሚካሄደው ፕሮግራም ላይ ማለት ነው።
በሰዓቱ እንገኝ! ከቀደምቶች የሚገኝን ልምድ በመቅሰም ስለአሁኑ በደንቡን የምንሰራበትን ስንቅ እንሸምት ዘንድ። በዳዮችን በመጋፈጥ ረገድ ሊያገለግለን የሚችልን እውቀት እንይዝ ዘንድ። ፍትሕ እንዲሰፍን በምናደርገው ትግል ውስጥ የሚጠቅመንን ነገር እናገኝ ዘንድ።
ዝግጁ? ያኡመተ-ሙሐመድ! የሱመያ ልጆች ... የቢላል ወራሾች _ ዝግጁ?!
@aaumsu
በፍትሕ ይመሩን ዘንድ ከቦታው የተቀመጡ ባለከፍተኛ ማዕረግተኞች የማይመስል ምክንያትን አቅርበው መብታችንን በመመሪያ አገዱ። ዶክተር የሚልን ማዕረግ የያዙ ሰዎች ተሰብስበው ሐይማኖታዊ መገለጫችንን የደህንኑት ስጋት ነው፤ መማር ማስተማርን ያደናቅፋል፤ ለአገልግሎት አያመችም የሚልን ምክንያት በመደርደር ሐይማኖታችንን ሰደቡ፤ ተማሪዎቻችንንም አንገላቱ፤ ከትምህርት እንደናቀፍ ዘንድ፤ የደህንነት ስጋት ይሰማን ዘንድ፤ አገልግሎት በአግባብ እንዳናገኝ ሰሩ። ጥያቄያችንን በሰላማዊ መንገድ ልንጠይቅ ስንሰበሰብ ንቀውን ዝም አሉ። ሆኖም በፅናት እስከ ምሽት ቀጠልን። በጥያቄያችን ስንገፋም "ሰብስበን አባረን ገበሬ ትሆናላችሁ!" አሉን።
አልደረስንባቸውም .. የደረሱብን እነርሱ ናቸው። የጣስነው ሕግ የለም ... ሕገ-መንግስቱን የሚጥስ መመሪያ ያወጡት እነርሱ ናቸው። መብቱን የነካንበት አካል የለም ... መብታችንን የጣሱት እነርሱ ናቸው።
ይህ የለመዱት ቢሆንም ... ልማድ አይሆንም ብለን ተነስተናል። በእኛ ቀደምቶች ላይ የደረሰ ቢሆንም ... ልጆቻችን ላይ አይደርስም ብለናል። ሀላፊነቱ የእኛ ነው ... መመሪያውን ያወጡበትን ቀን እስኪረግሙ፤ ተፀፅተውም መመሪያውን እስኪያሻሽሉ፤ መብቶቻችንን የጣሱ አካላት እስኪጠየቁ ድረስ እንሰራለን፤ ሳንታክት ... ሳንደክም ... ሳናርፍ እንሰራለን።
"የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች !"
ጦርሓይሎች
ረያን መስጂድ
እሁድ 07 / 2018 ዓ.ል
ከጧቱ 2:30 ጀምሮ
እንሰባሰብ!
አላህ ይጨመርበት!! ለዚህ መንገድ የማንሰስተውን ጥንካሬም ያድለን!!!
በባለቤቱ የተበደለ ፈረስ እያነባ ለነቢ ስሞታ አቅርቦ ነበር ... እርሳቸውም ዝም አላሉትም ... ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ ከባለቤቱ በመሄድ መደረግ ያለበትን አደረጉ --- የእኛ ነብይ እንዲህ ናቸው ... ከሰው ዘር አልፈው ለተበደሉ እንስሳት ጥብቅና የሚቆሙ ... ፍትሕ እንዲሰፍንላቸው የሚተጉ ነብይ ነበሩ ...
በደልን እንድንፀየፍ አስተማሩን
ከበዳይ ፊት ሐቅን መናገር ከጂሐድ እንደሆነ አስተማሩን
ፍትሕ ይሰፍን ዘንድ በአንድነት እንድንሰባሰብ አስተማሩን
በእርሳቸው ላይ ሰለዋት አውርዱ
አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሙሐመድ !😍!
የእርሳቸው ኡማ እንደመሆናችን በትምህርት ተቋማት ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት ዝም አንልም። ፍትሕ እስኪሰፍን እንጠይቃለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን እንሰራለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን እንሰባሰባለን ... ፍትሕ እስኪሰፍን መደረግ ያለበትን ሁሉ እናደርጋለን!!
በመጪው እሁድ ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ እንገናኝ ! !
ከፓናሊስቶቻችን 2! - አብዱልጀሊል ሸህ ዓሊ ካሳ
የመጀመሪያ ዲግሪውን ከሀረማያ ዩኒቨርስቲ ወስዷል። ሁለተኛ ዲግሪውን ባህር ማዶ ተሻግሮ በጣሊያን ሰርቷል። ኪነት-ያገነነው አፄ፤ ተምኔታዊት ደሴት እና እስልምና በኢትዮጵያ ከቅድመ ክርስቶስ እስከ ዛሬ የሚሉ ዘመን ተሻጋሪ መፅሐፍትን ለማህበረሰቡ በማበርከት ጉልህ አስተዋፅዖ አበርክተዋል።
ከዚህ ባሻገር በተለያዩ የሚዲያ ፕላትፎርሞች ላይ ሕዝበ ሙስሊሙን በማንቃት ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ እና አሁናዊ መፍትሔ ጥልቅ እይታቸውን ያጋሩናል።
በሰዓቱ እንገኝ ... ታሪክን ከማወቅ ባሻገር ታሪክ እየሰሩ ካሉ ምሁራን ትላንታችንን እንወቅ፤ ዛሬያችንን እንረዳ፤ ስለነጋችን እናልም። የትላንቶቹ የሰሩትን እውቅና በመስጠት ዛሬን በመስራት ልናልፍ ቃልኪዳን አለንና ቃላችንን እንሞላ ዘንድ ከሚያሰባስበን መድረክ እንክተም።
ሁሉም ይገኝ ... ከሀይስኩል እስከ ኮሌጅ ... ከመድረሳ እስከ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ይገኝ ... የተማሪ ወላጅም ይገኝ ... ወላጅ ያልሆነም ይገኝ ... ሁሉም ይገኝ! ስለጋራ አጀንዳችን በጋራ ተሰባስበን በጋራ እንምከር!!!
ዝግጁ?!
@aaumsu
ከፓናሊስቶቻችን ! - 1
በሕግ ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር ናቸው። በሕገ-መንግስታዊ ሕጎች ዙሪያ አሉ ከሚባሉ ምሁራን ነው። በወሎ ዩኒቨርስቲ ሕግን እያስተማሩ ከመሆናቸው ባሻገር በፕሪቶሪያ ዩኒቨርስቲ እጩ የሕግ ዶክተር ናቸው። በ Ethiopian Civil Society Organizations Council ፖሊሲ ዳይሬክተር በመሆን እያገለገሉ ነው።
ፕሮፌሰር ዘላለም እሸቱ ...
በተለያየ መድረክ በተለይም በሴኩላሪዝም እና መሠል ርዕሶች ዙሪያ ጥልቅ የሕግ እውነታዎችን በማቅረብ ይታወቃሉ። "የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!" - በሚል ርዕስ በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ ያዘጋጀነው የፓናል ውይይት ላይ ከፓናሊስቶች መካከል ሲሆኑ መሠረት የሚሆኑንን ምልከታዎች ያጋሩናል።
ለመገኘት፣ ለመማር፣ ለመጠየቅ ዝግጁ ናችሁ? ደግሞም እርሳቸው ብቻ አይደሉም። ሌሎች ምሁራንም ተጋብዘዋል። የምናሳውቅ ይሆናል።
የሀይስኩል ተማሪዎች ዝግጁ?
የAAU እንቁዎች ዝግጁ?!
የኮሌጅ ተማሪዎች ዝግጁ?!!
ያኡመተ-ሙሐመድ ዝግጁ?!!!
እንሰባሰብ፣ ድምፃችንን እናዋህድ፤ ስለአንድ አላማ በአንድነት እንሰለፍ፤ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ታሪክ እናድርግ!!!
@aaumsu
ክቡራን የ2018 ዓ.ም የAAU ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች፤ ቀደም ሲል ያሳወቅናችሁ የልዩ የምረቃ ሪቫን ምዝገባ አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ቀጥሎ የሚገኝ መሆኑን እያበሰርን፣ ካባችሁን በባዶ አንገት ከመልበስ ይልቅ ከሪቫኑ ጋር አብሮ የተዘጋጀውን ውብ ባይንደር (Binder) ጨምረው ማዘዝ እንደሚችሉ እናስታውሳለን።
ምዝገባው ከመጠናቀቁ በፊት ዕድሉን በመጠቀም ስምዎን፣ ካምፓስዎን እና ስልክ ቁጥርዎን ለቴሌግራም ቦታችን @Niqab_issueBot በመላክ በፍጥነት ይመዝገቡ። ሌላ ቦታ በመሄድ ሳይንገላቱ የራሳችንን መለያ የያዘውን ጥራት ያለው ሪቫንና ባይንደር በአንድ ላይ በመረጡት ካምፓስ ድረስ እናቀርባለን።
የዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁን በታላቅ ድል ለምትደመድሙት ተመራቂዎቻችን በሙሉ አላህ መልካም የምረቃ ዕለት እንዲያደርግላችሁ እንመኛለን።
@aaumsu
ታሪካዊው መድረክ ጥቂት ቀናት ቀርተውታል!
ቅስቀሳው ቀጥሏል፤ ዝግጅቱም ደምቋል! በመጪው እሁድ ሰኔ 07/2018 ዓ.ል በጦር ኃይሎች ረያን መስጂድ የሚካሄደው ታላቅ የፓናል ውይይት እንደተጠበቀ ነው። ይህ መድረክ የሙስሊም ተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብቶች የሚከበሩበትን፣ እንደ ኒቃብና ሒጃብ ያሉ የእምነትና የማንነት መገለጫዎች ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች በሕጋዊ መንገድ የሚመከቱበትንና ዘላቂ መፍትሔ የሚቀመጥበትን አቅጣጫ የሚያሳይ ነው። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ (ትራንስፖርት በተዘጋጀላቸው ካምፓሶች) ጀምሮ በከተማዋ የምትገኙ የከፍተኛ ትምህርት፣ የኮሌጅና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በሙሉ የዚህ ታሪክ አካል እንድትሆኑ ጥሪያችን የፀና ነው። እምነታችን፣ መብታችንና ምርጫችን ይከበር ዘንድ፣ ሰኔ 7 ከጧቱ 2፡30 ጀምሮ ልባችንና አቅጣጫችን ወደ ረያን መስጂድ ይሁን። ሁላችንም ለአንድ ዓላማ በአንድነት እንሰባሰብ።
ዝግጁ ናችሁ?!👍🫡
@aaumsu
እምነቷ ነው
መብቷ ነው
ምርጫዋ ነው ... ኒቃብ !
የሴራ ጉንጉን ጎንጉነው ክብሯን ሊነኩ የሚሞክሩ አካላትን ተው ብሎ እጃቸውን መሰብሰብ የሁሉም ሀላፊነት ነው። የመንግስትን መዋቅር ተጠቅመው ሕዝብ የሰጣቸውን ሀላፊነት በመተላለፍ መብቷን የሚረግጥ መመሪያ በማውጣት በደል የፈፀሙ አካላትን ተጠያቂ ማድረግ የሁሉም ሀላፊነት ነው።
ኒቃብ ምርጫዋ ነው ... መብቷ ነው ... እምነቷ ነው። ሊነካ ሊደፈር አይችልም። ይህንን ተላልፎ መምጣት እስልምና እና ሙስሊሞችን መዳፈር ነው።
ለዚህም ሲባል ሁሉም ግንዛቤው ይኖረው ዘንድ ስለ ሁላችን በሁላችን የሆነን መድረክ አሰናድተናል።
እሁድ ሰኔ 7 ልባችንን ከአንድ ቦታ ይሁን ... አቅጣጫችን ወደ ረያን መስጂድ ይሁን ... በአንድነት ስለአንድ አላማ እንሰባሰብ ... አላህ ብሎ መፍትሔውን የሚያመጣው ትውልድ አካል እንሆናለን!!!
ዝግጁ ?!
@aaumsu
Waltajjiin Guddaan Gaheera!
Mirgoota Barattootni Muslimaa Itiyoophiyaa Dhaabbilee Barnoota Ol'aanaa Keessatti qaban!
Mirgoonni keenya kan heera mootummaa akka barataa Muslimaatti qabnu hayyoota affeeramaniin gadi fageenyaan ni xiinxalama. Yuunivarsiitii Finfinneerraa kaasee, kaleessas ta'e har'a qajeelfama adda addaa baasuun ykn dhuunfaan Hiijaaba dhowwuun barattoota Muslimaa barumsarraa kan gufachiisan, fedhiifi dhiibbaa dhaabbileefi dhuunfaawwanii akkasumas furmaanni waaraan dhimma kanaa panalistootaan (panelists) ni ibsama.
"Gaaffiin mirga barattoota Muslimaa itti gaafatamummaa dhaloota keenyaati" jechuun waadaa seenne ni haaromsina; hojiileen mana keenya kan gara fuulduraas ifa ni ta'u.Barattoonni kaampaasii hundumaa (Geejibni mijateera) qaama sagantaa seena-qabeessa kanaa akka taataniif affeeramtaniittu. Barattoonni Mana Barumsa Sadarkaa 2ffaa (High School) fi Kolleejjii Finfinnee keessa jirtan dhaloota seenaa kana hojjetu keessatti qooda akka fudhattaniif kabajaan waamamtaniittu. Dhimma dhimma keenya hunda ta'e kanarratti walitti qabamuun keenya dirqama; carraa gaariidhas! odeeffannoowwan Sagantichaa: Bakka: Masjiida Rayyaan (Kan xoorhayilochitti argamu) Guyyaa: Dilbata dhufu, Waxabajjii 07 / 2018 A.L Sa'aatii: Ganama sa'aatii 2:30 irraa kaasee Qopheessaan: Gamtaa Barattoota Muslimaa Yuunivarsiitii Finfinneeti. Hiriyoota, maatii, obboloota dhiiraafi dhalaaf dabarsuun (share gochuun) dirqama keenya!
ታላቁ መድረክ ደረሰ .... የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያላቸው መብቶች!
እንደ ሙስሊም ተማሪ ስላሉን ሕገ-መንግስታዊ መብቶች በተጋባዥ ምሁራን በጥልቀት ይዳሰሳል። ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ ድሮም ዛሬም መመሪያ በማውጣትም ሆነ እንደ ግል ሒጃብን በመከልከል ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ስለሚያሰናክሉ ተቋማት እና ግለሰቦች ፍላጎት እና አንደምታ ብሎም ዘላቂ መፍትሔ በፓናሊስቶች ይብራራል። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የእኛ ትውልድ ሀላፊነት ነው ብለን የገባነውን ቃል እናድሳለን፤ ቀጣይ የቤት ስራዎቻችንም ግልፅ ይደረጋሉ።
የሁሉም ካምፓስ ተማሪዎች (ትራንስፖርት ተመቻችቷል) የዚህ ታሪካዊ ፕሮግራም አካል ትሆኑ ዘንድ ተጋብዛችሗል። አዲስ አበባ ውስጥ ያላችሁ ሀይስኩል እና ኮሌጅ ተማሪዎች የዚህ ታሪክ አካል ትሆኑ ዘንድ በክብር ተጠርታችሗል። ሁላችንም የሁላችንም አጀንዳ በሆነው ጉዳይ ዙሪያ እንሰባሰብ ዘንድ ግድ ሆኗል። መታደልም ነው!
ቦታ፦ ጦርሓይሎች በሚገኘው ረያን መስጂድ
ቀን፦ በመጪው እሁድ ሰኔ 07 / 2018 ዓ.ል
ሰዓት፦ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ
አዘጋጁ፦ የእናንተው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ነው። ለጓደኞቻችን፣ ለቤተሰቦቻችን፣ ለእህት ወንድሞቻችን ማሰራጨት ግዴታ ነው።
@aaumsu
የምስራች ለ2018 ዓ.ም የAAU ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ! 🎓✨
ከ6 ኪሎ፣ 5 ኪሎ፣ 4 ኪሎ እንዲሁም በሁሉም ካምፓሶች የምትገኙ የፊታችን ተመራቂዎች፤ ለዚህ ታላቅ የውጤት ቀን ያበቃችሁን አላህ (ሱ.ወ) እጅግ የላቀ ምስጋና ይድረሰው። አልሐምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን!
የመጀመሪያውን የዩኒቨርሲቲ ጉዟችሁን አስታውሳችሁ “መቼ ይሆን የምመረቀው?” ስትሉ የነበራችሁበት የትናንት ድካም አልፎ፣ አሁን የድል ምልክት የሆነውን የካባ መለኪያ ሰዓት በአላህ ፈቃድ ደርሷል።
የምረቃ ቀን በህይወት ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው የትዝታ ማህደር ሲሆን፣ የምረቃ ሪቫን ደግሞ ለዕለቱ ፎቶዎች ልዩ ድምቀትና ውበት የሚሰጥ ዋናው አካል ነው። በመሆኑም፣ ሪቫን ሌላ ቦታ ሄደው ለማዘዝ ከመቸኮልዎ በፊት ጥቂት ሰከንዶችን ይውሰዱና ይህንን መልዕክት ያንብቡ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት (AAUMSU)፣ ሁላችንም የምንኮራበትን፣ እሴቶቻችንን እና አንድነታችንን በኩራት የምንገልጽበትን ልዩ የምረቃ ሪቫን በታላቅ ጥራት አዘጋጅቶላችኋል።
ሌላ ቦታ ሄዶ መጨናነቅ እና መጉላላት ቀርቷል፤ የራሳችንን መለያ ይዘን ውብ በሆነ መንገድ ደስታችንን እናከብራለን! 😎🎉
ሪቫኑን ለማዘዝ @Niqab_issueBot በዚህ ላይ ይዘዙን
@aaumsu
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
