ru
Feedback
AAU - Muslim Students Union

AAU - Muslim Students Union

Открыть в Telegram
7 138
Подписчики
+324 часа
+2417 дней
+65130 день
Архив постов
🔵 የሚገርም ነው ነገሩ እንዲህ ነው ✴️ ​በአንድ ቀበሮ ጭራ ላይ ከባድ ድንጋይ ወድቆ ጭራውን ቆረጠው። ✨ ​ሌላ ቀበሮ አየውና፦ “ጭራህን ለምን ቆረጥከው?” ብሎ ጠየቀው። ✨ ​እርሱም፦ “በአየር ላይ እንደምበር ያህል ይሰማኛል፤ ምንኛ ታላቅ ደስታ መሰለህ!” አለው። 🔴 ​ይህንን ሲሰማ (ሁለተኛውም) ጭራውን እንዲቆርጥ አደረገው! ​ነገር ግን ብርቱ ሕመም በተሰማውና እንደተባለውም ምንም ዓይነት ደስታ ባላገኘ ጊዜ፦ “ለምን ዋሸህብኝ?” ሲል ጠየቀው። ✨​የመጀመሪያው ቀበሮ እንዲህ ሲል መለሰ፦
“ለሌሎቹ ቀበሮዎች ስለ ሕመምህ ከነገርካቸው ጭራቸውን አይቆርጡም፤ በእኛም ላይ ያፌዙብናል።”
⚫️ ​በመሆኑም ያገኙትን ቀበሮ ሁሉ ስለሚያገኙት (የሐሰት) ደስታ መናገራቸውን ቀጠሉ፤ ይህም በመሆኑ አብዛኞቹ ቀበሮዎች ጭራ አልባ እስኪሆኑ ድረስ ሆነ! ​ከዚያ በኋላ ጭራ ያለው ቀበሮ ባዩ ቁጥር ያፌዙበትና ይንቁት ጀመር!
(ብልሽት (ፈሳድ) በሰፈነ ጊዜ፣ ሰዎች ደጋግ ሰዎችን በበጎነታቸውና በደግነታቸው ማነወሪያ ያደርጓቸዋል! መሃይማንና ሞኞቹም መሳለቂያ ያደርጓቸዋል።)
🔵 ​ኢማም ሹረይሕ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ብለዋል፦
“በሰዎች ላይ አንድ ዘመን በእርግጥ ይመጣል፤ ዛሬ አመጸኛ (ፋጂር) በአመጽነቱና በክፋቱ እንደሚነቀፈው ሁሉ፣ አማኝም በእምነቱ የሚነቀፍበት፤ እንዲያውም አንድን ሰው ለማጣጣል ሲባል ‘አንተ እኮ አማኝና አሊም ደረሳ ነህ’ እስኪባለው ድረስ።”
🔷​ብልሹ ማኅበረሰብ ለሚያስተካክሉና ለሚገሥጹ  ሰዎች የሚለጥፍላቸው መጥፎ ነገር በታጣ ጊዜ፣ በእነርሱ ውስጥ ባለው እጅግ ውብና መልካም በሆነው ነገር ያነውራቸዋል... ✴️(​የሉጥ ሕዝቦች):- የሉጥን ቤተሰቦች ከመንደራችሁ አስውጡ፤ እነሱ ንጽሕናቸውን የሚጠብቁ ሰዎች ናቸው አሉ  ንፅህናቸውን በመጠበቃቸው ብቻ በአካባቢው ባይተዋር ተደረጉ 🔴 ​ዛሬም ወደ እርቃንነት (መገላለጥ) መጣራትና መሸፈኛን(ኒቃብን)ና ጥንቁቅነትን (ዒፋን) ወደ መጣል ከሚደረገው ጥሪ ጋር እየሆነ ያለው ነገር በትክክል ይህንን ነው። ⚫️ ​ነገሩማ አማኝ ሴትን በመሸፈኗና በጥንቁቅነቷ ወደ ማስወለቅና መውቀስ ደረጃ ይደርሳል፤ ሒጃቧንና ጠንካራ መሸፈኛዋን አጥብቃ ስትይዝ ባዩዋት ጊዜ በኋላቀርነት፣ በመሀይምነት፣ በትዕቢትና በስነ-ልቦና መዛባት ይፈርጇታል። ✴️ እንዲሁም ብልሁ፣ ጥንቁቁና አማኙ ወንድ በጥንቃቄው፣ በብልህነቱ፣ በእምነቱና አላህን በመፍራቱ ይወቀሳል። ​በዚያን ጊዜ “(ዲኑን አጥብቆ የያዘ ሰው ልክ የጋለ ፍም እንደጨበጠ ነው)” የሚለውን ሐዲሥ እውነተኛ ትርጉም ትረዳለህ፤ ✨ ምክንያቱም ከዚህች የስቃይ ምድር በኋላ ስፋቷ እንደ ሰማያትና ምድር የሆነች፣ ለአላህ እሱን ለሚፈሩት የተዘጋጀች ጀነት እንዳለች ያውቃልና። 📝 ​ወንድሞቼ  እና እህቶቼ ሆይ ✴️​ሐራም  የሆነ ነገር ሰዎች ሁሉ ቢፈጽሙትም እንኳ ዘላለም ሐራም ሆኖ ይቀጥላል፤ ✴️​ሒጃብ ሴቶች ሁሉ ቢያወልቁትም እንኳ ግዴታ  ሆኖ ይቀጥላል፤ ✴️​ሞት በሕይወት ያሉ ሁሉ ቢረሱትም እንኳ እውነት ሆኖ ይቀጥላል፤ ✴️ በመጨረሻም የተውበት በር አንድ ባሪያ ወደ ወንጀል ሺህ ጊዜ ቢመለስም እንኳ ክፍት ሆኖ ይቀጥላል። ​✨ አላህ ሆይ! ጥራት ይገባህ፣ ክብርህ ምንኛ ታላቅ ነህ © @aaumsu

ነፍሷን አሸንፋ እርቃኗን ከመሆን: ራሷን አብቅታ ለመትረፍ ለወገን:: መማርን ፈልጋ ልታለማ አገሯን: በእውቀት አለንጋ አባራ ጅህልናን: ለሃገር ግንባታ ለማስቀመጥ ጡቧን:: ተፍ ተፍ ስትል ለመሻት እውቀትን: ከሐገር ለማጥፋት ችግር ድህነትን:: የሰው ቀዬ ሳትደርስ ሳትጋፋ ሌላን: መራቆትን ጠልታ በመያዟ እምነቷን:: የእህቴን ክብር የዛች የጥብቋን: በ'ምባ እየተሞላች ገፈፏት ሑርማዋን::                          ⭐️⭐️⭐️ « አላ ሹለት የዱን » እህቴን የነካች: የንፅህናን ልክ በቅጥ ያልተረዳች: በጥላቻ ሰክራ ድንበር የዘለለች: የእህቴን ካባ ክብሯን የደፈረች:: ያቺ እጅ ትረገም ሐቅን የረገጠች: ኒቃብን አውልቃ እርቃን ያነገሰች:: የእህቴን ካባ ክብሯን የደፈረች: ራቁት አስፈትና ለባሽ ያባረረች: ፍትህን በመጣስ ሚዛን ያጓደለች::         ⭐️⭐️⭐️ ሁሉ ሲሰለጥን ሗላ የዘገዩ : በክፋት ጥላቻ ተነክረው የቆዩ: ቀለም መንካት እንጂ መማርን ያላዩ:: በ'ድሜ ቢሆን እንጂ ከልጅ ያልተለዩ: ከሽበት በስተቀር ክፋ ደግ ያልለዩ:: በየ ሴክተሩ ላይ ተሰግስገው ያሉ: ስንት ሰዎች አሉ አድገው ያልበሰሉ:: የተቀመጡበት ከስር ያለው ወንበር: ከነሱ ይሻላል በግልጋሎት ግብር::            ⭐️⭐️⭐️ ምን ይሆን ክሳችሁ ከቶ ምን አጠፋች?! ራሴን ጠብቄ እማራለሁ ባለች: ለ'ምነቷ ዘብ ሆና ፀንታ ስለቆመች:: ጨርቃቸውን ጥለው ሲቆዝሙ ሌሎች: ክብሯን ችላ ብላ ልብሷን ስላልጣለች:: የቱ ነው ጥፋቷ መብቷን በጠየቀች?: የራሷን ነው እንጂ የሰው መብት አልነካች:: ከጥላቻ በቀር ምክንያት ካላችሁ: አይዟችሁ ንገሩኝ በሉ እስኪ ልስማችሁ: ንገሩን ሰበቡን ድምፅ ከፍ አርጋችሁ:: የክልከላው ምክንያት ከተዋጠላችሁ: ኑ እስኪ ተናገሩት ካላሳፈራችሁ::            ⭐️⭐️⭐️ የኔው ነው ጥፋቱ የኔው ነው ስህተቱ: ይሰማኝ ይመስል ሙታን መጣራቱ:: መንቃት ያልፈለገን አውቆ የተኛን ሰው: እሳት ቢሆን እንጂ ውሃ ላያነቃው:: ያፄዎቹን ትርክት ጠጥቶ የሰከረን: ወደ ፊቱን ትቶ ሗላ ላይ የቀረን:: እውነታውን ገፍቶ መረዳት ዘመኑን: በጨለማው ዘመን ሰምጦ የቀረውን:: ቅን መሆንን ትቶ ጥላቻን ያዘለን: ጭቆናን እንደ ድል ስኬት የቆጠረን:: ምን ብዬ ልንገረው እንዴትስ ላስረዳው?! የጥላቻ ቆፈን ሐቅን ከጋረደው:: የሰው ልጅ ወቃሹ የገዛ ህሊናው: እሱ የሌለውን ሰው ብለህ አትጥራው::              ይህን ለመረዳት ካልሆነህ ትምርትህ: ጥላቻን ካስቀደምክ አመክንዮን ትተህ: ጥቅሙ ምኑ ላይ ነው ቀለም የመንካትህ:: ፕሮፌሰር : ዶክተር : ምሁራን መባልህ: Master , phD , degree መሸከምህ:: @aaumsu

"መጅሊስ በሂጃብ ጉዳይ ከ Retroactive( እሳት አጥፊነት) ነፃ የሚሆነው መች ነው?" - (ጠበቃ ሙስጠፋ ሺፋ እንደፃፈው) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሸሪዓ ፍርድ ቤትን አ
"መጅሊስ በሂጃብ ጉዳይ ከ Retroactive( እሳት አጥፊነት) ነፃ የሚሆነው መች ነው?" - (ጠበቃ ሙስጠፋ ሺፋ እንደፃፈው) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሸሪዓ ፍርድ ቤትን አዋጅ ለማሻሻል ከመንግሰት ጋር በመቀናጀት አንድ እምርታ እንዳስመዘገበው ሁላ ስለ ሂጃብ ኢ ህገ መንግስታዊ ብሎም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲፈፀም በተለይ የፈተና ወቅትን እየጠበቁ ባልተፃፈ ህግ የሙስሊም ተማሪዎችን ስነ ልቦና ለመጉዳት ሆን ተብሎ በጥቂት የመንግስት ተሿሚዎች ስልጣንን አላግባብ በመጠቀም በአንደኛ ደረጃ፣ በሁለተኛ ደረጃና በከፍተኛ የትምህርት ተቋም እየተፈፀመ ያለውን በደል መጅሊስ ልክ ድርጊቱ ሲፈፀም መግለጫ ከማውጣትና ድርጊቱ ወደ ተፈፀመበት ስፍራ አቅንቶ ለዛሬ ይሁን ዓይነት ሽንገላ ተነጋግረናል ተወያይተናል ይባልና ጉዳዩ ችላ እንደተባለ ከሆነ ጊዜ ቆይታ በኋላ አሁንም ሲያገረሽ መጅሊስ retroactive ( እሳት ማጥፋቱ) ይቀጥላል። ግን እስከ መቼ? ሒጃብ ሃይማኖታዊ ነው። ይህን ሃይማኖታዊ መብት ከኢፌዲሪ ህገ መንግስት አንቀፅ 27(1) አኳያ እንዲከበርና እንዲጠበቅ ዘንድ በደንብና በመመሪያ ጥሰት ፈፃሚዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ሃይማኖታዊ መብትን ብሎም ህገ መንግስታዊ ጥበቃ የተሰጠውን መብት በዘለቄታነት ተከብሮ እንዲዘልቅ መጅሊስ ስር ነቀል ለውጥ እንዲመጣ ዘንድ ጥሰት ሲፈፀም ለጊዜያዊነት ማስታገሻ እየወሰዱ ከመዝለቅ ይልቅ ስር ነቀል ለውጥ ለማምጣት ህግ እንዲከበር አበክሮ ካልሰራ ትላንትም፣ዛሬም ነገም ስለ ሂጃብ ክብር እየተደፋፈነ እንግልቱ ወደ ትውልድ መቀባበሉ ይቀጥላል። መጅሊስ በአዋጅም ሆነ በህገ መጅሊሱ የህዝበ ሙስሊሙን ሃይማኖታዊ መብት ማስከበርና ማስጠበቅ አበይት ተግባሩ ነው። @MohammadamminKassaw

"እምነቴን ልተው? ወይስ ትምህርቴን?" - አቡ አብደላህ እንደፃፈው ይህ ዛሬ ብዙ የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሚጠየቁት ከባድ ጥያቄ ሆኗል። ኒቃብ ለብሳ መማር የፈለገች ተማሪ ከትምህርት ክፍል ውጭ ስት
"እምነቴን ልተው? ወይስ ትምህርቴን?" - አቡ አብደላህ እንደፃፈው ይህ ዛሬ ብዙ የሙስሊም ሴት ተማሪዎች የሚጠየቁት ከባድ ጥያቄ ሆኗል። ኒቃብ ለብሳ መማር የፈለገች ተማሪ ከትምህርት ክፍል ውጭ ስትቀር፣ ፈተና እንዳትፈተን ስትከለከል፣ የሚጎዳው አንድ ግለሰብ ብቻ አይደለም፤ የሀገራችን ፍትሕ፣ እኩልነት እና የሕግ የበላይነትም ጭምር ነው። እኛ የምንጠይቀው ልዩ መብት አይደለም። ሕገ መንግሥቱ የሚያረጋግጠው የእምነት ነፃነት እና የትምህርት መብት በአንድነት እንዲከበሩ ብቻ ነው። የደኅንነት ወይም የማንነት ማረጋገጫ ካስፈለገ፣ ያንን የሴት ሠራተኛ በሚያረጋግጥበት ሥርዓት መፈጸም ይቻላል። ነገር ግን በኒቃብ ምክንያት ትምህርትን መከልከል ተገቢ መፍትሔ አይሆንም። ለመንግሥት ያለን ጥሪ፦ የሁሉንም ዜጎች መብት በእኩልነት የሚያስከብር፣ የእምነት ነፃነትንና የትምህርት መብትን የሚያጣጥም ግልጽ መመሪያ እንዲወጣ እንጠይቃለን። ለመጅሊስ ያለን ጥሪ፦ ይህ የብዙ ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን የሚመለከት ጉዳይ ነው። ከመንግሥት፣ ከትምህርት ተቋማት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ሕጋዊ፣ ሰላማዊ እና ዘላቂ መፍትሔ እንዲገኝ የሚጠበቅበትን ሚና እንዲወጣ እንጠይቃለን። የሙስሊም ሴት ተማሪ ኒቃብ የትምህርቷ ጠላት አይደለም። እምነትም ሆነ ትምህርት ሁለቱም መብቶች ናቸው፤ አንዱ ሌላውን ሊያስቀር አይገባም። #ኒቃብ_ወንጀል_አይደለም #የትምህርት_መብት #የእምነት_ነፃነት #ፍትሕ_ለሁሉም

"ክብሯን አስወለቋት!" የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ኒቃቡን ካላወለቃችሁ ተብለው ማውለቅ ጀመሩ። በአደባባይ ክብራቸውን እንዲያወልቁ ተደረጉ። እስካሁን ባለው መፍትሔ ተብሎ የተሰጠው ማስክ ለብሰው መግባትን ነው። ኒቃብም ማስክም ፊትን ይሸፍናሉ። ኒቃቡን አስወልቀው ማስክ ማስለበስን ለምን ፈለጉ? ማስክ አስለብሰው ኒቃቡን ማስወለቅ ለምን ፈለጉ?! ጥላቻ! ለኢስላማዊ እሴት ያለ ጥላቻ!! ሌላ ምንም ምክንያት የለም። አሁንም ቢሆን ተማሪዎች ክብራቸውን በአደባባይ ሳይጥሉ፤ ከእነ ኒቃባቸው እንዲፈተኑ መጅሊስ እና የሚመለከተው የመንግስት አካል ይስራ። አሁንም ቢሆን ይህንን ውንብድና የፈፀሙ አካላት ተጠያቂ እንዲደረጉ መንግስት እና መጅሊስ ይስሩ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !

ዛሬም ኒቃባቸውን በአደባባይ አውልቀው እንዲገቡ ተገደዋል! በትላንትናው እለት የ12ተኛ ክፍል ኢንትራንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በአብርሆት ቤተመፅሐፍት እየተፈተኑ ባለበት ከ20 በላይ ሙስሊም ተማሪዎችን "ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትገቡም!" - ተብለው ጓደኞቻቸው ውስጥ እየተፈተኑ እና በትምህርት ሚኒስቴሩ ሚንስትር ብርሃኑ ነጋ እየተጎበኙ ለ3 ሰዓታት ያክል ከውጪ እንዲሆኑ ተደርጎ ነበር። የሗላ ሗላ እንዲገቡ ቢደረግም ኒቃባቸውን አውልቀው እና ጥለው በማስክ ነበር። መፍትሔ እንደሚመጣ የተገለፀ ቢሆንም በዛሬው እለትም በተመሳሳይ ኒቃባቸውን በአደባባይ እያወለቁ እንዲገቡ ነው የተደረጉት። ይህ ግልፅ የሆነ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው። ይህ ግልፅ የሆነ የሀይማኖት መብት ጥሰት ነው። ይህ ግልፅ የሆነ የነፃነት መብት ጥሰት ነው። ኒቃብን መልበስ መብት ነው። መብት ስለሆነም ለብሳው ስትማር ነበር። አሁን ላይ እየተፈፀመ ያለው ውንብድና ተማሪዎችን የስነ-ልቦና መቃወስ ውስጥ እየከተታቸው ነው። ተማሪዎችም አስቸኳይ መፍትሔ እንዲመጣላቸው እየጠየቁ ነው። መጅሊስ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ይስራ። መንግስት ተጠያቂ መደረግ ያለባቸውን አካላት ተጠያቂ ያድርግ። ዘላቂ መፍትሔም ይምጣ!!! @MohammadamminKassaw

Manneen barnootaa ol’aanaa biyya keenyaayeeeee? Har’a keessatti “kaleessa keenya” nu agarsiiftaniiga? “Nurra” waa beektu seen
Manneen barnootaa ol’aanaa biyya keenyaayeeeee? Har’a keessatti “kaleessa keenya” nu agarsiiftaniiga? “Nurra” waa beektu seenee Ilmaan keenya isinitti erganneem isin garuu Amaanaa Minilikii fii Tafarii mokonnin eegaa jirtumoo? Dhukkuba kaleessaa yoom fayyitu? Sababa tureef Kaanserii ta’ee laata? Gochi dabaa ilmaan keenyarratti raawwatamu waan nulaaffisu isinitti hin fakkaatin!!! Akkatti as geenye beyna nus. Ustaaz Raayyaa Abbaamacca

ይህ ምስል፣ ልብን በሀዘንና በቁጭት የሚሰብር የታሪክ ጠባሳ ነው! (በኡስታዝ ነስሩ ኸዲር) መሬት ላይ ተጥሎ የሚታየው ተራ ጨርቅ አይደለም፤ የአንዲት እህታችን ክብር፣ ማንነት እና የእምነት መብት እ
ይህ ምስል፣ ልብን በሀዘንና በቁጭት የሚሰብር የታሪክ ጠባሳ ነው! (በኡስታዝ ነስሩ ኸዲር) መሬት ላይ ተጥሎ የሚታየው ተራ ጨርቅ አይደለም፤ የአንዲት እህታችን ክብር፣ ማንነት እና የእምነት መብት እንጂ! ተማሪዎች ነገ ሀገር ለመረከብ በሚፈተኑበት አዳራሽ ደጃፍ ላይ እምነታቸውን በግድ እንዲያወልቁ መገደዳቸው እጅግ አሳዛኝ ሥርዓት አልበኝነት ነው። ሂጃብ ለሙስሊም ሴት ልጅ ውጫዊ ጌጥ ሳይሆን፣ የማንነቷ አካልና የእሴታችን መገለጫ ነው። ​ይህ ድርጊት በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ላይ ሲፈጸም፣ የሚመለከታቸው የመፍትሄ አካላት እስካሁን ድረስ ግልጽና የማያሻማ እርምጃ አለመውሰዳቸውና በዝምታ ማለፋቸው ተጠያቂነትን ያጠፋ የተቋማት ዳተኝነት ነው። ትምህርት ቤት የነፃነትና የእኩልነት ማዕከል መሆን ሲገባው፣ የተማሪዎችን ስነ-ልቦና የሚሰብር አግላይ መድረክ ሊሆን አይገባም። ይህንን በደል ዝም ብሎ ማየት አብሮነትን ማፍረስ በመሆኑ፣ የሚመለከተው አካል አስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግና ጥፋተኞችን ተጠያቂ እንዲያደርግ በጽኑ እንጠይቃለን።

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የቀድሞ ፕሬዝዳንት የተላለፈ የስንብት መልዕክት! بِسۡمِ اللَّهِ الرَّحۡمَٰنِ الرَّحِيمِ إلى جميع الطلاب المسلمين المتخرجين من جامعة أديس أبابا — فالحمد لله الذي أوصلكم إلى هذا اليوم الذي طالما انتظرتموه. بعد كل الصعود والهبوط، والتعب، ولحظات الشك، والارتفاعات، والتضحيات الكثيرة، منّ الله عليكم بهذا الإنجاز العظيم. وعلى هذه النعمة الجليلة، هو وحده يستحق عميق شكركم وثنائكم. الحمد لله!! وكما هي طبيعة هذه الدنيا، تجمع الحياة الناس في لحظات، وتفرقهم في أخرى. وقد جمعنا الكثير معاً من خلال أنشطة الجماعة المختلفة، وقد حظيت شخصياً بشرف التعلم الكثيرمنكم جميعاً  وعلى ذلك، الحمد لله، إنني ممتن حقاً.   وأودّ أن أتقدم  التهاني إلى الأخ أنور أندارجي، والأخ محمد محمد بشير، والأخ عمران كامل، والأخ عمر عبد القهار، والأخ عبد لله   محمد فجزاكم الله خيراً جميعاً على تفانيكم وصبركم والدور الذي أديتموه طوال فترة دراستكم في هذ  الجامعة ,الوصول إلى هذا اليوم ليس بالأمر الهين، وقد استحققتموه عن جدارة وأخصّ بالذكر القلبي الأخ زيد صادق ثباتك والطريقة الهادئة والمستمرة التي أعطيت بها نفسك لهذه الجماعة لن تُنسى.   كنت أحد أولئك الإخوة الذين وجودهم يُحسّن الأمور دون الحاجة إلى الإعلان عن ذلك. بارك الله فيك وجزاك خيراً عظيماً على ما قدمته. وإلى الأخ عرفات محمد فإن تفانيكم في عمل جماعة الجامعي، سواء كان ظاهراً أو خفياً، فتقبّل الله كل جهد بذلتموه في سبيله، وليعوّضكم خيراً منه أضعافاً مضاعفة. وفي الحقيقة، القائمة أطول من أن تُحصى، وكل من بذل جهداً في سبيل الله من إخوة وأخوات سواء ذُكر اسمه أم لم يُذكر، قاد من الأمام أم عمل في الخفاء  فإن الله لم يغفل عن عمله ولن يضيع أجره. وإلى كل أخ وأخت خدم في قطاعات الدعوة، والقراءة، والأكاديمية، والاجتماعية في الجماعة  والاتحاد أولئك الذين سهروا ولا بد من إفراد ذكر خاص من القلب لأولئك الأخوات والإخوة الذين وقفوا إلى جانبهن , الذين ناضلوا بلا كلل وبشجاعة في قضية النقاب. في وقت لم يكن فيه الثبات أمراً يسيراً، ثبتّن. وفي وقت كان التمسك بموقفكن يكلّف الكثير، تمسكتن به على أي حال  في سبيل الله، وصوناً لكرامتكن، ومن أجل كل أخت مسلمة جاءت بعدكن. واجهتن ضغطاً مؤسسياً ومقاومة وصعوبات، غير أنكن لم تترددن. ما حملتموه لم يكن معركة شخصية فحسب — بل كان مسألة مبدأ وإيمان وعدالة. وسيتذكر التاريخ موقفكن، والأهم من ذلك أن الله شهد كل لحظة منه. فليجزيكن بأعلى الجزاء على كل صعوبة تحملتموها، وكل دمعة ذرفتموها، وكل خطوة خطوتموها في سبيله. جزاكم الله خيرا  عسى أن يجمعنا الله وإياكم في الفردوس الأعلى                                                                          الحمد لله — وألف مبروك للجميع. مبارك عليكم التخرج أيها الخريجون. الفصل القادم يبدأ الآن احملوا دينكم معكم إليه. أخوكم مهفوظ نغاش @aaumsu

📢📢📢የዘገየ መልዕክት ውድ የ2026 አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምሩቃን..... ከብዙ ድካም፤ ዱዓና ጥረት ቡሃላ አላህ አግርቶላቹህ እናንተም ቤተሰቦቻቹህም በጉጉት ለሚጠብቁትና ለሚኮሩበት ለዚህ ስኬት እንኳን አበቃቹህ! ምስጋና ለአላህ የተገባ ይሁን! ይድረስ~ 📌ለአላህ ብዬ ምወድህና ማከብርህ፤ ታላቄ፤ ሃሚለል ቁርአን፤ ድምጸ ውቡ ~ ሙስዓብ ኢብራሂም ከ 4ኪሎ IS 📌የህብረቱ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ማህፉዝ ነጋሽ፤ 📌የህብረቱ የቀድሞ ምክትል ፕሬዝዳንት ~ የማከብርህ... ህብረታችንን ከመረጥንህ ጊዜ አንስቶ በቅንነትና በጫና ስታገለግል የነበርከውና ለእህቶችህ ኒቃብ ብዙ መስዋእትነትን የከፈልከው ባለ ውብ ስነምግባሩ አብዱልሃሚድ ከ6ኪሎ ህግ፤ 📌የህብረቱ የቀድሞ ጸሃፊና ጽኑ ባለ መልካም ስነምግባሩ ወንድማችን ዘይድ ሳዲቅ ከ4ኪሎ Mathimathics፤ 📌በህብረቱ የቀድሞ የ6ኪሎጀመዓ ም/አሚር አቡበከር ኢድሪስ ከ6ኪሎ ማርኬቲንግ፤ 📌በህብረቱ የልደታ ካምፓስ የቀድሞ አሚርና የስራ ባልደረባዬ ሙህሲኑ አረፋት ሙሀመድ ከልደታ Urban፤ 📌በህብረቱ የቀድሞ የሰፈረሰላም የቀድሞ አሚር ባለጥልቅ እውቀቱ፤ ዝምተኛው አብዱራህማን ከሰፈረሰላም Radiology፤ ሊሎችም በተለያየ አጋጣሚ ያገኘኋቹ ውድ ወንድሞቼ ሙሀመድ (ከሰፈረሰላም ~ Radiology)፤ ሰሚር ሙሰማ (ኮሜርስ ~ Logistics) ፤ የFBE የቀድሞ የተማሪዎች ህብረት ም/ፕሬዝዳንትና የ6ኪሎ ጀመዓ ሶሻል ሴክተር አባል ኢስሃቅ አምሳሉ (FBE ~ Management)፤ ሙእሚን ጀማል(4k ~ IS)፤ አብዱረሂም ነስሬ (FBE ~ Management)፤ አማን ከድር (FBE ~ Management)፤ ገና ዱሬሳ (FBE ~ PADM)፤ አብዱልሃሚድ ሳዲቅ(FBE ~ PADM)፤ የወርቂቾ ልጅ[ስምህን ረሳሁት😅](FBE ~ Management)፤ አባስ አህመድ (5k ~ Civil) ፤ አብዲ ታዬ (5k ~ Civil)፤ የቀድሞ የስራ ባልደረባዬ አብዱልሙንዒም (5k ~ Software)፤ ሰልማን አሊ(5k ~ Software)፤ አንዋር (5k ~ Electrical)፤ ኡስታዝ ፉአድ ፈድሉ (4k)፤ ሙህዪዲን (FBE ~ Management)፤ አሚር (commerce ~ Marketing)፤ ሰልማን (commerce ~ Marketing)፤ አብደላ አህመድ (Commerce ~ BAIS)፤ ጋሊብ (FBE ~ Economics)፤ በሺር(FBE ~ Economics)፤ የባቲው ሰዒድ ሙሀመድ (6k ~ PSIR) ፤ አመለሸጋው አንዋር (commerce ~ Economics)፤ ፈውዛን (4k ~ CS)፤ አብዲ (4k ~ CS)፤ መርዋን (5k ~ Software)፤ ኡሳማ (4k ~ IS)፤ አሚር መኑር (4k ~ IS)፤ አይመን (6k ~ Chinese) እንዲሁም በስም ያልጠራኋቹህ መላው የ6ኪሎ፤ 4ኪሎ፤ ሰፈረሰላምና ልደታ ሙስሊም ተመራቂዎች በሙሉ እንኳን ለዚህ አበቃቹህ። ደስታቹ ደስ ብሎኛል አልሀምዱሊላህ ለነጃት፤ ረውዳ፤ ሃናን፤ ኢክራም ሙሀመድ፤ ፈይሩዛ፤ ራህማ ና መላው የ2026 ሙስሊም ሴት ምሩቆች እንኳን ደስ አላቹ። አላህ በስኬት ላይ ስኬትን ይጨምርላቹ ዘንድ ዱዓዬ ነው። ከናንተ ብዙ እንጠብቃለንና በርቱልን! ውዱ ወንድማቹህ ከ6ኪሎ

"መመሪያው መማር ማስተማሩን የሚረብሹ እና ስነ-ምግባርን ያልተከተሉ ብሎ እንደሚያስቀጡ ከገለፀ ቡሃላ ከእነዚህ መካከል በአንቀፅ 1.3 እና 2.3 ላይ 'ፊትን በሙሉ የሚሸፍን (ኒቃብ) መልበስ አይፈቀ
"መመሪያው መማር ማስተማሩን የሚረብሹ እና ስነ-ምግባርን ያልተከተሉ ብሎ እንደሚያስቀጡ ከገለፀ ቡሃላ ከእነዚህ መካከል በአንቀፅ 1.3 እና 2.3 ላይ 'ፊትን በሙሉ የሚሸፍን (ኒቃብ) መልበስ አይፈቀድም ይላል።" - የሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሙስሊም ተማሪዎች የኮሌጁ ሙስሊም ተማሪዎች ይህ መመሪያ ኒቃብን ስነ-ምግባርን ያልተከተለ ብሎ ማስቀመጡ እምነትን እና ማንነትን የሚያንቋሽሽ ነው በማለት ገልፀዋል። ይህንንም ተከትሎ በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ የተለያዬ ክልከላ እና እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ አስቀምጠዋል። መፍትሔ ይመጣ ዘንድም ለኮሌጁ፤ ለአዲስ አበባ እና ፌደራል መጅሊስ ደቤዳቤ ያስገቡ ቢሆንም እስካሁን ድረስ መፍትሔ እንዳልመጣ በመግለፅ መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ባከበረ መልኩ ይስተካከል ዘንድ እና ይህንን ያደረጉ አካላት በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ይሰራ ዘንድ ጠይቀዋል።

ልዩነቱን ተመልከቱ አንዱ ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በወራቤ ዩኒቨርስቲ ነው። ሁለቱም ለኢንትራንስ ተማሪዎችን እያስፈተኑ ሲሆን ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ያለው በትምህርት ሚኒ
ልዩነቱን ተመልከቱ አንዱ ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በወራቤ ዩኒቨርስቲ ነው። ሁለቱም ለኢንትራንስ ተማሪዎችን እያስፈተኑ ሲሆን ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ያለው በትምህርት ሚኒስቴሩ ብርሃኑ ነጋ ኒቃባቸውን ገፍፎ ከመሬት ሲጥል፤ በወራቤ ያለው ደግሞ ክብራቸውን ጠብቆ ስርዓቱን በተከተለ መልኩ ፈትሾ አስፈትኗቸዋል።

ይህ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ አደራችን ነው ብለን ተቀብለናል። በአላህ ፈቃድ ፍትሐዊ መልስ መጥቶ መብቶቻችን እስኪከበሩ ድረስ ጥያቄ አለን ከማለት አናርፍም፤ አንፈራምም። መረጃዎች ይደርሷችሁ ዘንድ የህብረቱን ቻናል @aaumsu ያሰራጩ።

ከአራት ቀን በፊት ነበር "ኒቃቧን እንደለበሰች ትማራለች!" - የሚል ፅሁፍ ያለበትን ሪቫን የለበሱ 12 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪዎች በምርቃታቸው ቀን ከእስር ቤት እንዲውሉ የተደረገው። ዛሬ ደግሞ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎች "ኒቃብ ስለለበሳችሁ ልትገቡ አትችሉም!" - ተብለው ጓደኞቻቸው እየተፈተኑ ባለበት ከውጪ እንዲቀመጡ ተደረገ። What are we waiting for? ምን እስኪደርስ ነው የሚጠበቀው? የክብራችን ዋጋ ምን ያክል ነው? የእስልምናችን ዋጋ ምን ያክል ነው? @aaumsu

ማስክም ኒቃብም ፊትን የሚሸፍኑ ሆነው ሳለ ኒቃባቸውን አስወልቀው በማስክ አስገቧቸው። እንዳሉት ለደህንነት ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ማስኩም ፊትን ስለሚሸፍን መለበስ አልነበረበትም። ሆኖም ግን ምክንያታቸው ሙ
ማስክም ኒቃብም ፊትን የሚሸፍኑ ሆነው ሳለ ኒቃባቸውን አስወልቀው በማስክ አስገቧቸው። እንዳሉት ለደህንነት ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ማስኩም ፊትን ስለሚሸፍን መለበስ አልነበረበትም። ሆኖም ግን ምክንያታቸው ሙስሊም ጠልነት ስለሆነ ፍላጎታቸው ኒቃቡን በማስወለቅ ማዋረድ፣ መጨቆን፣ ከእምነቷ ማራቅ ነው፤ አደረጉትም። መብቷን ማስጠበቅ የነበረበት መጅሊስም ከቦታው ተገኝቶ ማስክ ገዝቶ ሰጣት።

ክብራችንን ነው የገፈፉት መብታችንን ነው የጣሉት ነፃነታችንን ነው በማስክ የቀየሩት ጨርቅ ነው ብለው ከወሰዱ ስህተት ነው። ሱና ነው ብሎ ያብራራም ካለ ውርደት ነው። ይህ እንደ ሀገር፤ እንደ ኢትዮጵ
ክብራችንን ነው የገፈፉት መብታችንን ነው የጣሉት ነፃነታችንን ነው በማስክ የቀየሩት ጨርቅ ነው ብለው ከወሰዱ ስህተት ነው። ሱና ነው ብሎ ያብራራም ካለ ውርደት ነው። ይህ እንደ ሀገር፤ እንደ ኢትዮጵያዊ፤ እንደ ዜጋ መብታችን የሆነ ነገር ነው። የክብራችን መገለጫ፤ የሐይማኖት መብታችን ዋስትና ነው። ሆኖም ግን ገፈፏቸው ሆኖም ግን አስወለቋቸው ሆኖም ግን ከመሬት ጣሉት ይህ በእኔ እና በአንተ ዘመን እየሆነ ያለ ነው!

ኒቃባቸውን በዚህ መልኩ ሰብስበው ከመለሱ ቡሃላ ማስከ አስለብሰው ነው ያስገቧቸው። ይህ ነው ጊዜያዊ መፍትሔ? ይህ ነው መፍትሔው?! ይህ እኮ ውርደት ነው ወገን!!! @MohammadamminKassaw
+1
ኒቃባቸውን በዚህ መልኩ ሰብስበው ከመለሱ ቡሃላ ማስከ አስለብሰው ነው ያስገቧቸው። ይህ ነው ጊዜያዊ መፍትሔ? ይህ ነው መፍትሔው?! ይህ እኮ ውርደት ነው ወገን!!! @MohammadamminKassaw

መጅሊስ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ለማስከበር ቁርጠኝነት ካለው የሚከተሉትን ነገሮች ያድርግ፦   ፨ የመብት ጥሰት እየፈፀሙ ያሉ አካላትን በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ያድርግ   ፨ ለሙስሊም ተማሪዎች መብት እውቅና የሚሰጥ መመሪያ ይወጣ ዘንድ በቁርጠኝነት ይስራ @aaumsu

መንግስት ከሙስሊሙ ማህበረሰብ የመብት ጥያቄ ጋር ችግር ከሌለበት እና ችግሩ የብርሃኑ ነጋ ብቻ ከሆነ የሚከተሉትን ነገር ያድርግ፦ 1ኛ፦ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጥሰት እንዲፈፀም እያደረገ ያለውን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከሀላፊነቱ ያንሳ፤ በሕግ አግባብም ተጠያቂ እንዲሆን ይስራ 2ኛ፦ ለሙስሊም ተማሪዎች ሕገ- መንግስታዊ መብቶች እውቅና የሚሰጥን መመሪያ ያውጣ

የሙስሊም ተማሪዎች መብቶች ማስከበር ለእነሱ የሚደረግ ውለታ አይደሉም። ከአላህ ለሁላችንም በቦታችን ልክ የተሰጠ አደራ፣ ህጋዊ ኃላፊነት እና የማህበረሰብ ግዴታ ናቸው። ሙስሊም ተማሪዎችን መደገፍ በጎ አድራጎት (ሰደቃ) አይደለም፤ አማናን (አደራን) መወጣት ነው። @aaumsu