Amigonian High School (9-12)2015
Відкрити в Telegram
1 298
Підписники
Немає даних24 години
Немає даних7 днів
Немає даних30 днів
Архів дописів
Repost from Ethiopian Digital Library
የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና (የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና)
በአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ሪፎርም መሠረት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ወደ ሙሉ ትግበራ መግባቱ ይታወሣል፡፡
በዚህም መሠረት ደረጃ ትምህርት የሚሰጡ የትምህርት አይነቶች ተለይተው የመማር ማስተማር ሂደቱ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዞ በ2016 ዓም በሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የሚሰጡ የትምህርት አይነቶችን መወሰን በማስፈለጉ በሁለቱም ዘርፎች ዕድስት፣ ስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሆኑ እንደሚከተለው ተወስኗል፡፡
✅የተፈጥሮ ሣይንስ
👉 እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ከሚስትራ፣ ባዮሎጂ፣ ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ
✅የማህበራዊ ሣይንስ
👉 እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ጂኦግራ፣ ፊታሪክ፣ ኢኮኖሚክስ፣ ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ
ከላይ በተጠቀሰው መሠረት የ2016 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ዝግጅት
👉1. የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ከ12ኛ ክፍል ብቻ ፈተናው የሚዘጋጅ፣ ሌሎች የትምህርት አይነቶች ከ9ኛ እስከ 11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ-ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሆኑን
👉2. ሰኮላስቲክ አኘቲቲውድ ቴስት ወደፊት ጥናት ተጠንቶ እስከሚለይ ድረስ በነበረው አሠራር መሠረት ውጤት ተደምሮ የሚገለጽ መሆኑን
👉3. የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያውቁት እንዲደረግ እናሳስባለን።
ትምህርት ሚኒስቴር
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
