uk
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 739
Підписники
-124 години
+17 днів
-730 день
Архів дописів
Repost from N/a
photo content
+4

Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የግዢና ፋይናንስ ስራ ሂደት አዲስ በተገነባው ቢሮው በዛሬው እለት ስራውን ጀምሯል:: ኮሌጁ በሪፎርም ስራዎች እየሰራባቸው ከሚገኙ ስራዎች ውስጥ የስራ ቦታን ለሰራተኛው ምቹ የማድረግ ስራ የሚገኝበት ሲሆን ዛሬ ተመርቆ ስራ የጀመረው የኮሌጁ የግዢና ፋይናንስ ስራ ሂደት ቢሮም የዚህ ማሳያ ነው:: ይህ የስራ ክፍሎችን የማዘመና ምቹ የማድረግ ስራ በሌሎች የስራ ክፍሎችም ጭምር ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ወደተቋሙ የሚመጡ ተገልጋዮችን ምቹ በሆነና በተቀላጠፈ መንገድ አገልግሎት ለመስጠት እንዲቻል ታቅዶ እየተሰራ የሚገኝ ተግባር ነው:: ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 26/2016 ዓ.ም

Repost from N/a
photo content
+8

Repost from N/a
" እያመረትን እናሰለጥናለን እያሰለጠንን እናመርታለን " በሚል አዲስ ዕሳቤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ስር የሚገኙ ሁለቱን የመንግስት ኮሌጆች ከስልጠና በተጨማሪ አምራችነታቸውን የሚያጠናክር የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በዛሬው ዕለት ተካሄደ። " እያመረትን እናሰለጥናለን እያሰለጠንን እናመርታለን " ስንል ምን ማለታችን ነው? ማሰልጠንና ማምረት ፣ማምረትና ማሰልጠን በአንድ ቦታ ማለትም በድሬዳዋ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆቻችን በተመሳሳይ ወቅት በማከናወን የማምረቻና የማሰልጠኛ መሣሪያዎች፣ አምራችና አሰልጣኝ ባለሙያ ፣ቦታና ጊዜ ተቀናጅተው የሚገኙበት ሲሆን በዚህም ቁሳዊና ሰብዓዊ ሃብቶችን በማቀናጀት እሴት በመጨመር ሃብት ማፍራት ምንም የሚባክን ጊዜና ሃብት እንዳይኖር በማድረግ ድርብ ኃላፊነትን በማቀናጀት ምርት በማምረት/አገልግሎት በማቅረብ ገቢ ማግኘት የሚያስችል ነው፡፡ በዚህም መርሃ ግብር ላይ የየድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው፤ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የአስተዳደሩና የቢሮው ከፍተኛ አመራሮች፤ የኮሌጅ ዲኖች፤ አሰልጣኝ መምህራን እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የተገኙ ሲሆን ሰነዶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ጥቅምት 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from N/a

photo content
+2