uk
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 740
Підписники
+124 години
+37 днів
-530 день
Архів дописів
#አሁን #Happening_Now 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር የመዝጊያ ፕሮግራም
+5
#አሁን #Happening_Now 4ኛው ሀገር ዓቀፍ የክህሎት ውድድር የመዝጊያ ፕሮግራም

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ  "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሦስተኛ ዙር ትግበራ በሁለት ተከታታይ ዙሮች የህይወት ክህሎትና የስራ አፈላለግ ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ 1200 ሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር በድምቀት ተካሄደ፡፡ በዚህም የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ላይ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በቀጣይ በስራ ላይ ለሚኖራቸው ስልጠና እንዲጠቀሙበት በማሳሰብ የሚመጡ እና የሚገጥሟቸን ፈተናዎች በጥንካሬ በማለፍ ለራሳቸውና ለሃገራቸው የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በሁለት ዙሮች ለ12 ቀናት የህይወት ክህሎትና የስራ አፈላለግ ስልጠና በኮሌጆቹ ውስጥ ሲሰጣቸው የቆየ ሲሆን ይህንንም ሲያጠናቅቁ በመረጡት የሙያ ዘርፍ በአስተዳደሩ በሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንደስትሪዎች ላይ የኪስ ገንዘብ እየታሰበላቸው በተግባር እየሰሩ እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ እንደሚሆን ገልጸው በስልጠና ቆይታቸውም በኮሌጆቹ የህጻናት ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅቶላቸዋል በዚህም የልጅ እናት የሆኑ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ስልጠናውን ሳይስተጓጎሉ እንዲወስዱ መቻሉን በማስታወስ ለዜጎች ሁሉን ተደራሽ የሚያደርግ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች በመሰራት ላይ ለመሆናቸው ይህ መርሃግብር ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በአጠቃላይ በሁለት ዙር በሁለቱም ኮሌጆች ሰልጥነው ያጠናቀቁ ሰልጣኞች ብዛት አንድ ሺህ ሁለት መቶ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይ ቀናትም ሰልጣኞቹን ከኢንዱስትሪዎች ጋር የማስተሳሰር ስራ የሚጠናቀቅ መሆኑን አስታውቀው ሰልጣኞቹን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በማሰልጠንና ሁኔታዎችን በማመቻቸት የተሳተፉ አካላትን ሁሉ አመስግነዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 1/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሶስተኛ ዙር ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የህይወት ክህሎት እና የስራ አፈላለግ ስልጠና ማጠቃለያ መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሄደ።

photo content
+9

photo content
+9

የሽሬ ግብርና ቴ/ሙ/ት/ስልጠና ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራር አባላትን የያዘ ልዑካን ቡድን ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት ካሄደ፡፡ ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ እያሳየ በሚገኘው ከፍተኛ አፈፃፀም ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ኮሌጆች ለልምድ ልውውጥ ወደ ተቋማችን እየመጡ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው እለትም በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሚገኘው የአክሱም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋማችን የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርጏል:: ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የአፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከተ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ የለውጥ ስራዎችም በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረገው ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃ መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች መደነቃቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ሞዴል ተደርጎ መወሰድ የሚችልበት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ሀሳባቸውን ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኟቸውን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡበት ኮሌጅ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ የፋይዳ ዲጂታል ብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ መርሀግብር አካሄደ። ሚያዚያ 30/2017 ዓ.ም እንደ ሀገር የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማስቻልና የዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ እውን ከማድረግ አኳያ ሁሉንም ዜጋ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ ቁልፍ ተግባር ተደርጎ በንቅናቄ እየተሰራ ይገኛል:: በዛሬው እለትም በኮሌጁ በተዘጋጀው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ መርሃ-ግብር ላይ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም ሰልጣኝ ተማሪዎች በቦታው በመገኘት ምዝገባቸውን ማከናወንም ችለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ

photo content
+9

photo content
+9

#ዜና | የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አድራ ፕሮጀክት የ 5000 ዋት ሶላር ፒቪ ኢኒስታሌሽን እና ኮሚሽኒንግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ ። #Dire tv አማርኛ ሚያዚያ 28/2017 በድሬዳዋ አስተዳደር በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በአድራ ኢትዮጵያ በቅንጅት እየተሰራ ያለ የኤሌትሪክ ሀይል የሚሰራ በአይነቱ ለየት ያለ ሶፍት ዌር የተገጠመለትን የኮሌጁን የኤሌክትሪክ ዲፖርትመንት ሙሉ ለሙሉ በሶላር ሀይል ኢንዲጠቀሙ የሚያደርግ ፕሮጀክት ከጀርመን ሀገር በመጡ የሶላር ዘዴዎች የተሰራ 5000 ዋት ሶላር ፒቪ ዝርጋታ በትብብር በመስራት በይፋ የርክክብና የምረቃ መርሀ ግብር ተካሂዷል ። የድሬዳዋ አስተዳደር የስራና ክሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸዉ በጸሀይ ሀይል የሚሰራ የሀይል ምንጭን መጠቀም ውስጥ የታዳሽ ሀይልን የመጠቀም አዲስ ልምድና አዲስ አቅምን የፈጠረ መሆኑን ገልጸው በተጨባጭ ያለዉን አስተዳደሩ የሚፈልገዉን ቴክኖሎጂ የሞላ የስራ እድልን መፍጠር ላይ ከዚህ በላይ መስራት ይገባናል ብለዋል ።ድርጅቱ ላደረገው ድጋፍም በቢሯቸውና በአስተዳደሩ ስም አመስግነዋል። የአድራ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ዳሬክተር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በበኩላቸው ወጣቶች በታዳሽ ሀይል በሶላር ሀይል መሳቢያ ተከላ ሥራ ሰልጥነዉ ህዝባቸዉና ሀገራቸዉን እንዲያገለግሉ ብሎም የራሳቸውን ህይወት እንዲለዉጡ አላማ ይዞ እየሰራ ያለ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀዉ ወጣቶችን የክህሎት ባለቤት በማድረግ ወጣቱ ከስራ ፈጠራ ወደ ሀብት ፈጠራ እንዲገባ የሚያነሳሳ ፕሮጀክት ነዉ ሲሉ ተናግረዋል ። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁ እንደ አስተዳደር ከያዝነዉ ድሬዳዋን የዘመነች ከተማ የማድረግ ግንባታ ላይ ትልቅ ሚና የሚጫወት ፕሮጀክት ነዉ ብለዋል ። አድራ ኢትዮጵያ ፕሮጀክቱ ሲጀመር ለ120 ሰልጣኞች የስራ እድል ለመፍጠር የታሰበ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ከ46 በላይ ሰልጣኞችን አሰልጥኖ በማስመረቅ ለሁለተኛ ዙር ምዕራፍ እንዲሁ አሰልጥኖ ለማስመረቅ በዝግጅት ላይ ይገኛል ። አድራ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ላለፉት አርባ ሁለት አመታት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በተለይ የነብስ አድንና ዜጎችን ህይወት መለወጥ ላይ ትኩረት አድርጎ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲሰራ የቆየ አሁንም እየሰራ ያለ ድርጅት ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በአጫጭር ስልጠናዎችና በሶላር ፒቪ ሲስተም መስመር ዝርጋታና ጥገና ተማሪዎችንንና መምህራንን የማሰልጠንና የማብቃት ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ከመድረኩ ተገልጿል። ሰላም ይኄይስ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የውይይት መድረክ አካሄዱ። "የመሃሉ ዘመን!" በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እና ሠራተኞች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ የተወያዩ ሲሆን ውይይቱም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ባለፉት ተከታታይ 7 አመታት ለውጡን ለማፅናት በተደረጉ ጥረቶች፣ የተገኙ ውጤቶች፣ ያጋጠሙ ውስጣዊ፣ ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ተግዳሮቶችና የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲሁም አሁናዊ ሀገራዊ ሁኔታና የቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ ሆኗል። በውይይቱም የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት የቢሮው ሰራተኞችና አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጠራ ግንዛቤ መያዛቸው እንደሀገር ሊገጥሙ የሚችሉ ፈተናዎችን በሚገባ ለመቀልበስ እንዲሁም የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን በማድረግ ሂደት የማይዝልና የማይታክት አቅም የሚፈጥር ይሆናል ብለዋል። በመድረኩ "የመሃሉ ዘመን!" በሚል መሪ ቃል ለውይይት መነሻነት የሚሆን ሰነድ በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጎበታል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

4ኛው ሀገር ዓቀፍ ክህሎት ቴክኖሎጂ እና ጥናትና ምርምር ውድድር ዛሬ በዲጂታል ተወዳዳሪነት ቀን የተለያዩ የክህሎት እና የቴክኖሎጂ ውድድሮች በመካሄድ ላይ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደርም በአሰልጣኝ በሰልጣኝ እና በኢንተርፕራይዞች ተወክሎ ኢትዮጵያን አሸናፊ ለማድረግ በመወዳደር ላይ ይገኛሉ። ከሚካሄዱ ውድድሮች ጎን ለጎን የቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽኖች እና ባዛር በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ግቢ እየተካሄደ ይገኛል። "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 28/2017 ዓ.ም አዲስ አበባ

photo content
+9

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa) - Статистика та аналітика Telegram каналу @eipc2001