uk
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Відкрити в Telegram

Показати більше
1 740
Підписники
+124 години
+37 днів
-530 день
Архів дописів
የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት መነሻ አድርገው የሚሰጡ የሙያ ስልጠናዎች የሚስተዋለውን የሰለጠነ የሰው ሀይል እጥረት መቅረፍ እንደሚያስችሉ ተገለፀ:: ሚያዚያ 25/2017 ዓ.ም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አማካኝነት በኢንዱስትሪው የሙያ ፍላጎትን አስመልክቶ በተዘጋጀው የዳሰሳ ጥናት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክት "በቀጣይ እንደ ተቋም በሚኖረን ትግበራና ፕሮጀክቱም ትኩረት ከሚሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ አንደኛው የኢንዱስትሪውን ፍላጎት ምንነትን ተገንዝቦ ስልጠናዎችን በዛ አግባብ መስጠት በመሆኑ ይህን የፍላጎት ደሰሳ እዲዘጋጅ እድርገናል" ያሉ ሲሆን አክለውም በቀጣይ እንደ ተቋም በምናዘጋጀው የ10 አመት እስራቴጂክ እቅድ ላይ መሰል ጥናቶች እንደ ግብዓት የምናካትት ይሆናልም ብለዋል:: በኢንዱስትሪዎች ላይ የፍላጎት ዳሰሳ ከተደረገባቸው ነጥቦች አንፃር የተገኙ ውጤቶች፣ የተለዩ ክፍተቶችን በአጭር ጊዜና በረጅም ጊዜ ለመሙላት በሚያችል መልኩ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ መዘጋጀቱን የገለፁት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም ይህን ጥናት እንደ መነሻ መሆኑን እና በቀጣይም የትኩረት ማዕከል በሆኑት ዘርፎች ላይ በልዩነትና በጥልቀት መሰል ጥናቶችን በማካሄድ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወን በእቅድ መያዙን ገልፀው በዚህ የፍላጎት ዳሰሳ ላይ ለተሳተፉ በሙሉ በኮሌጁ ስም ላቅ ያለ ምስጋናም አቅርበዋል:: በእለቱ የተዘጋጀው የኢንዱስትሪዎች የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሰነድ በአሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ እና እሰልጣኝ መ/ር ነዋይ ይልማ አማካኝነት በመድረኩ ተሳታፊ ለነበሩ ባለድርሻ አካላት የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሰነድም በኢንዱስትሪዎች ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎች ካላቸው የትምህርት ዝግጅት አንስቶ ከሚሰሩት ስራ አኳያ ያላቸው ተዛማችነት በዝርዝር የዳሰሰ ሲሆን በርካታ መሰል የተለዩ ክፍተቶችም በቀረበው ሰነድ ላይ ተመላክተዋል:: በመድረኩ በቀረበው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናትን መነሻ በምድረግም ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ገንቢ የሆነ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ለሰነዱ ተጨማሪ ግብአቶችም የተገኙበት መድረክ ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

photo content
+9

በስራና ክህሎት ቢሮ ደረጃ በተዘጋጀው የእውቅና መርሃ-ግብር ላይ ተጨማሪ ምስሎች📸📸

ለ4ኛው አገር ዓቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ስራዎች እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ለተሳተፉና ላለፉ ተወዳዳሪዎች የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራ ክህሎት ቢሮ የውድድርና የተነሳሽነት ስሜትን በመፍጠር በክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማቱ ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን እና አሰልጣኞችን ባለሙያዎችን ለማፍራት በማለም የ2017 ዓ.ም ከተማ አቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ስራዎች እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች ማካሄዱ ይታወሳል፤ በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ የዕውቅና ፕሮግራም ላይም የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት በዋናነት በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር በሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በተለይም ከኢንዱስተሪዎችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር በመስራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍን የላቀ ሚና ለማጎልበት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ እና በዚህም አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑንና ይህም መርሃግብር አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ከተጣለበት ከፍተኛ ኃላፊነት አንዱ በሙያ ክህሎቱ የበለጸገ የሰው ሀይል ማፍራትና ቴክኖሎጂን የመቅዳት፣  የማሻሻል እና የማሸጋገር ስራ  ዋነኛው መሆኑን ገልጸው፡፡ በሙያ ክህሎታቸው የበቁ ቴክኖሎጂስቶችና ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ለሚሰሩ አሰልጣኞች፤ ሰልጣኞች፤ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች እንዲሁም ለ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ መምህራንና ተማሪዎች ውድድሮችን በማዘጋጀት ማትጋቱ አስፈላጊነቱ ስለታመነበት ቢሮው ይህን ኃላፊነት በመውሰድ ውድድሮችን በማዘጋጀት ዕውቅናና ሽልማት መርሃግብር ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ መርሃ ግብር በሁሉም ውድድሮች ለተሳተፉና ውጤት ላስመዘገቡ የሰርተፍኬትና የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን በቀጣይ ድሬዳዋን ወክለው በፌደራል ደረጃ የሚወዳደሩ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለ4ኛው አገር ዓቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ስራዎች እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ለተሳተፉና ላለፉ ተወዳዳሪዎች የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራ ክህሎት ቢሮ የውድድርና የተነሳሽነት ስሜትን በመፍጠር በክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማቱ ዘርፍ ብቁና ተወዳዳሪ ሰልጣኞችን እና አሰልጣኞችን ባለሙያዎችን ለማፍራት በማለም የ2017 ዓ.ም ከተማ አቀፍ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ ስራዎች እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድሮች ማካሄዱ ይታወሳል፤ በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ የዕውቅና ፕሮግራም ላይም የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደገለጹት፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት በዋናነት በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር በሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በተለይም ከኢንዱስተሪዎችና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በትብብር በመስራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍን የላቀ ሚና ለማጎልበት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ እና በዚህም አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑንና ይህም መርሃግብር አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ከተጣለበት ከፍተኛ ኃላፊነት አንዱ በሙያ ክህሎቱ የበለጸገ የሰው ሀይል ማፍራትና ቴክኖሎጂን የመቅዳት፣  የማሻሻል እና የማሸጋገር ስራ  ዋነኛው መሆኑን ገልጸው፡፡ በሙያ ክህሎታቸው የበቁ ቴክኖሎጂስቶችና ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ለሚሰሩ አሰልጣኞች፤ ሰልጣኞች፤ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች እንዲሁም ለ1ኛ እና 2ኛ ደረጃ መምህራንና ተማሪዎች ውድድሮችን በማዘጋጀት ማትጋቱ አስፈላጊነቱ ስለታመነበት ቢሮው ይህን ኃላፊነት በመውሰድ ውድድሮችን በማዘጋጀት ዕውቅናና ሽልማት መርሃግብር ማዘጋጀቱን ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ መርሃ ግብር በሁሉም ውድድሮች ለተሳተፉና ውጤት ላስመዘገቡ የሰርተፍኬትና የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን በቀጣይ ድሬዳዋን ወክለው በፌደራል ደረጃ የሚወዳደሩ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት  ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+9

የአክሱም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራር አባላትን የያዘ ልዑካን ቡድን ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ልምድ ልውውጥ ጉብኝት ካሄደ፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ እያሳየ በሚገኘው ከፍተኛ አፈፃፀም ጋር ተያይዞ በሀገሪቱ የሚገኙ በርካታ ኮሌጆች ለልምድ ልውውጥ ወደ ተቋማችን እየመጡ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው እለትም በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሚገኘው የአክሱም ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋማችን የልምድ ልውውጥ ጉብኝት አድርጏል:: ቡድኑ በኮሌጃችን በነበረው የልምድ ልውውጥ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የአፈፃፀም ሂደት በዝርዝር የተመለከተ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በተለያዩ ተግባራት እያከናወናቸው የሚገኙ የለውጥ ስራዎችም በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አማካኝነት ሰፋ ያለ ገልፃ ተደርጎላቸዋል:: ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ ባደረገው ምልከታና የተደረገላቸው ገለፃ መነሻ በማድረግ በተካሄደው የጋራ ውይይት ወቅትም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ እያከናወናቸው በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የስራ እንቅስቃሴዎች መደነቃቸውን ገልፀው በተለይም ኮሌጁ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ በአጭር ጊዜ እያሳየ ያለው የላቀ አፈፃፀም ለሌሎች አቻ ተቋማትም ሞዴል ተደርጎ መወሰድ የሚችልበት ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ሀሳባቸውን ገልፀዋል:: በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎች እንዲሁም ዎርክ ሾፖችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን እዚህ በኮሌጁ ያገኟቸውን በርካታ ልምዶችንም ቀምረው በመጡበት ኮሌጅ ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩም ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሚያዚያ 20/2017 ዓ.ም

የስራ ማስታወቂያ ለድሬዳዋ ነዋሪዎች በሙሉ የኢትዮጲያ አየር መንገድ አዲስ የስራ ማስታወቂያ ያወጣ ሲሆን በኤሌክትሮኒክስ በሜካኒካል ፣ በኢንዱስትሪያል ኢንጂነሪንግ እና ተያያዥ የትምህርት መስኮች የተመረቁትን ለመቅጠር ይፈልጋል ። በመሆኑም እድሜያቸው ከ 18 እስከ 25 እንዲሁም ቁመት ሜትር ከ ስልሳ የሆናቹ ከሚያዚያ 20 አንስቶ እስከ ሚያዚያ 24 2017 ዓ.ም ድረስ አስፈላጊውን የትምህርት ማስረጃ በመያዝ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በአካል በመገኘት መመዝገብ ይኖርባቸዋል ። አስታውሱ የምዝገባው ቀን አጭር ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ !

#እንኳን_አደረሳችሁ!! በቅድሚያ ለኮሌጃችን ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና እንዲ
+1
#እንኳን_አደረሳችሁ!! በቅድሚያ ለኮሌጃችን ማህበረሰብ እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና እንዲሁም የመተሳሰብ ይሆንላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቴን አገልፆለሁ፡፡ #መልካም_የፋሲካ_በዓል!! አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጁ ዲን                   

photo content
+9

photo content
+9

የEASE ፕሮጀክት የሩብ አመት አፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣይ ሩብ አመት እቅድ ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት የተከናወኑ ያለፉት 3ወራት የትግበራ አፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣዩን 3ወራት እቅድ ለኮሌጁ ኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ በዛሬው እለት አቅርቦ በመድረኩ ውይይት ተደርጎበታል:: መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደገልፁት ፕሮጀክቱ በየሩብ አመቱ ሪፖርቱን ሲያቀርብ በዋነኛነት የደረሰበትን አፈፃፀም ደረጃ ለባለድርሻ አካላት ግልፅ ከማድረግም በተጨማሪ ለቀጣይ ትግበራዎች ግብዓት የሚሆኑ ምክረ-ሃሳቦችን ከመድረኩ ለማግኘት በማሰብ ጭምር መሆኑንም ገልፀዋል:: የፕሮጀክቱን ያለፈው ሩብ አመት አፈፃፀም ሪፖርት በEASE ፕሮጀክት ዋና ኮርድኔተር ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው አፈፃፀም ሪፖርትም በሩብ አመቱ ሊሰሩ የታቀዱ በርካታ ተግባራት መከናወናቸው ተገልፇል:: በዚህም.... የፕሮጀክቱን አዲስ ቢሮ ከማደራጀት አንስቶ -የGender & Inclucsive guidline ማዘጋጀት -የአሰልጣኞችን የውጭ ስልጠና የማመቻቸት -የDigitalization ስራዎች የማስፋፋት -ከተለያዩ የፌደራል ተቋማት እና ከ14 አጎራባች ቴክኒክና ሙያዎች ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ውል የመፈራረም -የተልያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች -የHigh school ተማሪዎች ላይ ግንዛቤ የመፍጠር ስራዎች በሩብ አመቱ ከተከናወኑት ተግባራቶች ውስጥ እንደሚጠቀሱም ተገልፇል:: መድረኩ ቀጥሎም በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 3ወራት በኮሌጁ የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ ለተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው የፕሮጀክቱ አፈፃፀምና የቀጣይ ትግበራ እቅድን መነሻ በማድረግ ለፕሮጀክቱ ውጤታማነት የሚረዱ ምክረ ሃሳቦችን በስፋት አንስተው ውይይት ተደርጎበታል:: በመጨረሻም በEASE ፕሮጀክት የትኩረት ዘርፎች ተብለው በተለዩት ዲፓርትመንትቶች ላይ ጊዜው የደረሰበትን የስልጠና ማቴሪያሎች ለማሟላት በዲፓርትመንቶቹ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንን በማቀናጀት እየተዘጋጀ ሚገኘው የማቴሪያል ልይታ(Specification) ለኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርዱ የቀረበ ሲሆን የቦርዱ አባላትም ካላቸው ልምድ አኳያ በማቴሪያል ዝርዝሩ ላይ ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን እንዲሁም ማስተካከያ ሚያስፈልጋቸውን ጉዳዮች ምክረ-ሀሳብ እንዲሰጡበት የተደረገ ሲሆን የማቴሪያል ዝርዝሩን ሚያዘጋጁት መምህራንም ከመመድረኩ የተሰጠውን ግብረ-መልስ በማካተት በቀጣይ በሚኖረው መድረክ የሚያቀርቡም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሚያዚያ 4/2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content
+9

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት የስርዓተ-ፆታ ትግበራ መመሪያን ለማዘጋጀት የተሰራው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ:: የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ ላለፉት ወራት ለዚህ ተግባር በተዋቀሩ ባለሙያዎች ሲዘጋጅ የቆየ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዛሬው እለትም ለኮሌጁ ማኔጅመት ቀርቦ ውይይት ተደርግበታል:: የEASE ፕሮጀክት በቀጣይ አመታት በሚኖረው ትግበራ በHard Skills ላይ የሴት ሰልጣኞችን ቁጥር በተቻለ መጠን ለማሳደግ ትኩረት እድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ይህንን የዳሰሳ ጥናት በከፍተኛ ተነሳሽነት ያዘጋጁ ባለሙያዎችን አመስግነው በቀጣይም የስርዓተ-ፆታ መመሪያው ተዘጋጅቶ በአጭር ጊዜ ወደ ትግበራ እንዲገባ ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል:: ፕሮጀክቱ በዚህ የትግበራ ማእቀፍ በዋነኛነት የሴት ሰልጣኝ ተማሪዎችን እንዲሁም የኮሌጁ ሴት ሰራተኞችን ተጠቃሚ ለማድረግ የምንሰራበት ነው ያሉት ደግሞ የEASE ፕሮጀክት ዋና ኮርድኔተር ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ ይህ ትግበራ በትክክል ግብ እንዲመታ ከማድረግ አኳያም የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱን የጉዳዩ ባለቤት በሆኑት ሴት አሰልጣኝ መምህራን እና ሴት አመራሮች እንዲዘጋጅ እድርገናልም ብለዋል:: በEASE ፕሮጀክት በቀጣይ 5አመት ውስጥ በስርዓተ-ፆታ ላይ ለሚከናወኑ ተግባራት መነሻ የሚሆን መመሪያ ለማዘጋጀት የተሰራው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በወ/ሮ ራሄል እሸቱ እንዲሁም በኢንጂነር ህይወት እሸቱ አማካኝነት ለመድረኩ ተሳታፊዎች የቀረበ ሲሆን በHard Skills ላይ የሴት ሰልጣኞችን ውስነት መነሻ በማድረግ በተዘጋጀው በዚህ ጥናትም በዋነኛነት የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት ሴት ሰልጣኞች የተሳተፉበት ሲሆን በተጨማሪም ዲፓርትመንት ተጠሪዎች፣ ሴት አሰልጣኝ መምህራን፣ የኮሌጁ ዲኖች እንዲሁም እንዱስትሪዎችንም በጥናቱ ተሳታፊ እንደነበሩ የተገለፀ ሲሆን በዘርፉ ለሚስተዋለው ችግር መንስኤ ናቸው ያሏቸው ጉዳዩችም ለጥናቱ በግብአትነት ተካተውበታል:: በመድረኩ በቀረቡት የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቶች መነሻነት ከተሳታፊዎች በርከት ያሉ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት የተካሄደ ሲሆን ጥናቱንም ለማዳበር ተጨማሪ ግብአቶች የተገኘበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ሚያዚያ 3/2017 ዓ.ም

photo content
+9