Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
Відкрити в Telegram
Показати більше
1 739
Підписники
-124 години
+17 днів
-730 день
Архів дописів
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠና አጠናቃቂ ለሆኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች የኢንተርፕሩንርሺፕ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል::
ስልጠና በዋናነት ሰልጣኝ ተማሪዎች መደበኛ ስልጠናቸውን አጠናቀው ሲወጡ ስራ ፈጣሪነትን ተላብሰው እንዲወጡና በሚፈጥሩትም ስራ ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ከመጥቀም ባሻገር ለሀገር ኢኮኖሚ እንዲተርፉ የሚያስችላቸው የንግድ ስራ ክህሎት ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል::
የኢንተርፕሩነርሺፕ ስልጠናውን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI)ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን ስልጠናው በቀጣዮቹ ቀናትም ቀጥሎ የሚሰጥም ይሆናል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ህዳር 14/2017 ዓ.ም
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተከናወነው የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ዙሪያ
ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀም በፕሮጀክቱ ተወካይ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ስልጠና ላይ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ጭምር በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በዚህም በመጀመርያ ዙር የፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በቀጣይ ለሚሰጠው ስልጠና እንቅፋት እንዳይሆኑ ከወዲሁ ለማስተካከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመምከር የመፍትሄ አቅጣጫዋችን ማስቀመጥ ተችሏል።
መድረኩ ቀጥሎም እንደ አገር አዲስ የሆነው የሶላር ቴክኒሺያን እና ኤክስፐርት የስራ መዘርዝር 'JOB BOX ' ሰነድ ከሲቪል ሰርቪስ በመጣ ባለሙያ የቀረበ ሲሆን ሰነዱንም የሚመለከታቸው ተቋማት ሁኔታውን በደንብ ገምግመው ግብረመልስ ተሰቶበታል።
በቀጣይም የተሰራው የJOB BOX ሰነድ እንዲፀድቅና የሶላር ፒቪ ተጠቃሚ ተቋማት የሶላር ኤክስፐርት/ ቴክኒሺያን በመቅጠር የሶላር ዘርፍ ላይ ያለውን ከፍተኛ ክፍተት መሙላት እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን ይህም በADRA ፕሮጀክት የሰለጠኑ ባለሞያዋችም ከሚከፈትላቸው የስራ እድልም ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደላድል ይፈጥራልም ተብሏል።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 13/2017 ዓ.ም
በአስተዳደሩ በሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒኮች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደቶች አዘጋጅነት ለጥቃቅን ፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስለሚሰጠው የኢ/ኤ/ቴ/ሽ አገልግሎት ድጋፍ ላይ ያተኮረ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተካሄደ::
የውይይት መድረኩን የሁለቱ ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የኢ/ኤ/ቴ/ሽ አገልግሎት ስራ ሂደት ም/ ዲኖች በጋራ የመሩት ሲሆን በመድረኩም የ2016 ዓ.ም የኢ/ኤ/ቴ/ሽ አገልግሎት አፈፃፀም ላይ እንዲሁም የ2017 ዓ.ም በተሰራ የዳሰሳ ጥናት እና በቀጣይ ስለሚደረግላቸው ድጋፍ እንዲሁም የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የሙያ ብቃት ምዘናን በተመለከተ አጠቃላይ ገለጻ በስራ ሂደቱ ባለሙያዎች የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ተችሏል፡፡
በመጨረሻም የ2016 ዓ.ም አፈፃፀምን መነሻ በማድረግና የተለዩ ችግሮችን በመለየት በ2017 በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንዲቻል ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባ በመግለፅ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል::
የኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ህዳር 10/2017 ዓ.ም
"ሀገራዊ መግባባት
ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት!"
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች 19ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ።
በዓሉ በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን፣ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን አውስተው፣ ሀገራዊ መግባባትን ለማጽናት ሕገ መንግሥቱን መሠረት በማድረግ ጥያቄዎችን በሰላማዊ አግባብ የሚያስተናግድ ሥርዓት መገንባትና የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ከዳር ደርሶ አንድነታችንን እንዲያጠናክር ቀዳሚ የመንግሥት ትኩረት እንደሆነ ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 6/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
የISO 9001:2015 QMS የጥራት ሥራ አመራር ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሸላሚ::
የድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001:2015 የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ባለቤት ሆነ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ከሚገኙት የመንግስት ኮሌጆች አንዱ የሆነው የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የትምህርት ስርዓት የጥራት ማረጋገጫ እና የብቃት መመዘኛ ISO 9001:2015 QMS አለም አቀፍ ሰርተፊኬት አገኘ።
በሰርተፊኬት ርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ የተገኙት የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ እንዲሁም የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ሀርቢ ቡህ በድሬዳዋ 233 አነስተኛ ፣ 70 መካከለኛ እና 36 ከፍተኛ የኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች እንደተመዘገበ ጠቁመው የምስራቋ የኢንደስትሪ ኮሪደር እንደመሆኗ መጠን በኮሌጁ የሰለጠኑ ባለሙያዎችና ከፍተኛ የሰው ሃይል እንደሚያስፈልጋት አረጋግጠዋል።
ጥራት ያለው የሰው ሃይል ለማፍራት ፤ ጥራት ባለው የትምህርት ስርዓት እና ምዘና ማለፍ ይገባል ሲሉ በመክፈቻ ንግግራቸው ወቅት የገለፁት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ በብቃት የሰለጠነ የሰው ሃይልን በማፍራት ለኢንደስትሪው ማበርከት ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል።
በመድረኩ ላይ በእንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ነቢሃ መሀመድ እንደገለፁት በሀገር አቀፍ ደረጃ እድሉን ካገኙ 20 ትቋማት መካከል 5ቱ እራሳቸውን በጥራት ደረጃ ማሳለፍ መቻላቸውንና ከእነዚህም መካከል የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንዱ መሆኑን አስታውቀዋል።
አክለውም ይህ የጥራት ማረጋገጫ ከምስራቅ ኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሚያደርገው ገልፀው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ተፈላጊ ባለሙያዎችን በማሰልጠን የስራ እድልን ከመፍጠር በዘለለ ትልልቅ ድርጅቶችንና ኩባንያዎችን የሚያንቀሳቅሱ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል።
የጥራት ማረጋገጫ ሰርተፊኬቱን ለኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ያስረከቡት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ መዓዛ አበራ ተቋማቸው በሀገሪቱ 9 የተደራጁ የጥራት ላቦራቶሪዎችን በማደራጀት እየፈተሸ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በግብርና ፣ በምግብ ስርዓት ፣ በኢንደስትሪ ምርት እና በትምህርት ስልጠና የብቃት ደረጃዎችን የመለካት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልፀው በአጠቃላይም 50 ሚሊየን ዶላር በመመደብ የጥራት ደረጃዎችን ለማሻሻልና ለመፈተሽ እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በመርሃግብሩ ማጠቃለያም ለኮሌጁ የትምህርት ስርዓትና የጥራት ደረጃ አስተዋፅኦ ላበረከቱ መምህራን የእውቅና እና ማበረታቻ ሽልማት ተበርክቷል።
©️ Diretv ህዳር 3/2017
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዘንድሮ አዲስ ለማሰልጠን የተቀበላቸውን ሰልጣኞች በአስተዳደሩ የሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችን አስጎበኘ::
ኮሌጁ ያዘጋጀው የጉብኝት መርሃ-ግብር በእስተዳደሩ ከሚገኙ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በመተባበር የተከናወነ ሲሆን በዚህም ሰልጣኝ ተማሪዎች ጉብኝታቸውን በኮካኮላ፣ናሽናል ሲሚንት፣ሬድዋ ሞተርስ እና ኒውዌቭ ፋብሪካዎች ላይ ተዘዋውረው እዲጎበኙ ማድረግ ተችሏል::
ሰልጣኝ ተማሪዎቹ በኢንዱስትሪ ጉብኝት ቆይታቸው በኮሌጁ ለመሰልጠን ከመረጡት የሙያ ዘርፍ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ፉብሪካዎች ላይ ተመድበው የጎበኙ ሲሆን ይህም በኮሌጁ ቆይታቸው ስለሚሰለጥኑት የሙያ ዘርፍ የተሻለ ግንዛቤ እንዲያገኙም አስችሏቸዋል::
ይህን መሰል መርሃ-ግብር ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጁ ስልጠናቸውን ካጠናቀቁ በኃላ ያሏቸውን የስራ እድሎች ምን እንደሚመስሉ ከውዲሁ እንዲረዱና በቴ.ሙ.ስ ዘርፍ በሚኖራቸው ቆይታ መነቃቃትን እንዲፈጥርላቸው ታስቦ የተዘጋጀ የጉብኝት መርሃ-ግብር ነው::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
