Wolayta sodo university
Відкрити в Telegram
Info about wolayta sodo university Photos ,new music ,vine and different thing about the Campus@@@@@@@@@@@@@@ For junior and senior students.@veva1
Показати більше2 421
Підписники
+624 години
+57 днів
+530 день
Архів дописів
#ማስታወቂያ!!
ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች በሙሉ።
ጉዳዩ፦አዲሱ የሰው ሀይል አደረጃጀት መወቅር በድልድል አፈጻጸም መመሪያ መሠረት የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ምርጫን ይመለከታል፡፡
አዲሱ የፌዲራል መንግስት መወቅራዊ አደረጃጀት ለውጥ ምክንያት በድልድል አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 859/2014 ክፍል አራት አንቀጽ 29 መሠረት የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ አባላት በቁጥር ዐ2 ከሠራተኞች የሚመረጥ ስለሆነ በቀን 21/01/2016 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ሁሉም ሠራተኞች በዋናው ካምፓስ በመመረቂያ አደራሽ በተጠቀሰው ቀን በሰዓት በመገኘት ከሰራተኞች በቁጥር ዐ2 የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ እንድትመርጡ እናሳውቃለን።
#ማሳሰቢያ፦ በመድረኩ የድልድል ኮሚቴው የእስከ አሁን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና ቀጣይ የስራ አቅጣጫ ቀርቦ ውይይት ስለሚደረግ በዕለቱ ሁሉም የአስተዳደር ሰራተኛ በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኝ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር በጥብቅ ያሳስባል።
ከሰው ሀብት አስተዳደር ልማት ዳይሬክቶሬት
መስከረም 18/2016 ዓ/ም
@wsu19be
የዩኒቨርሲቲው መማክርት ጉባኤ/ሴኔት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔዎችን አስተላለፈ።
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲው መማክርት ጉባኤ/ሴኔት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመምከር ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
__
በ2016 በጀት ዓመት የሚተገበሩ የማህበረሰብ ጉድኝትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ፕሮጀክቶችን እንዲሁም የ2016 ትምህርት ዘመን አካዳሚክ ካሌንደርን ገምግሞ ማጽደቅ የሚሉ አጀንዳዎች ላይ መማክርቱ በስፋት መክሯል።
በጉባኤው በወቅታዊና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ የመረጃ ልውውጥ የተካሄደ ሲሆን፤ በአጀንዳነት በተያዙ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት በመወያየትም መማክርቱ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
መማክርት ጉባኤው በቅርቡ ከትምህርት ሚኒስቴር የተላከ ኢንስፔክሽን ቲም ያካሄደውን የቅሬታ አቤቱታ መረጃን የማጣራት ተግባር በተመለከተም ከልዑኩ በተሰጠ ግብረ መልስ ላይ በስፋት ተወያይቷል።
ኢንስፔክሽን ቲም አባላቱ ለአንድ ሳምንት መረጃዎችን የማጣራት ስራ ሲያከናውኑ እንደቆዩ በመድረኩ የተገለጸ ሲሆን፤ የቅሬታ አቤቱታው በአብዛኛው ሀሰተኛና ተጨባጭነት የሌለው መሆኑ ተመላክቷል።
በአሉባልታና በሀሰተኛ መረጃ ተቋም ፈጽሞ እንደማይመራ እንዲሁም በተቀነባበረ የሀሰት መረጃ ተቋም ለማፍረስ የሚደረግ ማንኛውም አካሄድ ተቀባይነት እንደሌለው በመድረኩ ተገልጿል።
በጥብቅ ዲሲፕሊን፣ ህግን እና የአሰራር ስርዓትን በመከተል ተግባራትን ማከናወን ተገቢ መሆኑን በመገምገም በቀጣይ ጊዜ ማንኛውም ፕሮጀክት የፋይናንስ አስተዳደር ስርዓትን በመከተል በጥንቃቄ እንዲመራም መማክርት ጉባኤው አቅጣጫ አስቀምጧል።
የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን መንግስት እንደ ሀገር ያስቀመጠውን የትኩረት አቅጣጫ መሰረት በማድረግ የኤሌክትሮኒክ ዲጂታል ግዥ ስርዓት በፍጥነት እንዲተገበርም መማክርቱ ውሳኔ አስተላልፏል።
የ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና አተገባበርን በተመለከተ "የአዝማሚያ ትንተና ጥናት" በማካሄድ ድክመትና ጥንካሬን እንዲሁም ያጋጠሙ ዋና ዋና ችግሮችን በመለየት በጥልቀት መገምገም እና በቀጣይ የበለጠ ለመስራት ከወዲሁ መዘጋጀት ተገቢ መሆኑን መማክርቱ አቅጣጫ አስቀምጧል።
መማክርት ጉባኤው በ2016 በጀት ዓመት እንዲተገበሩ የታቀዱ የምርምር፣ ማህበረሰብ ጉድኝት እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዝርዝር ፕሮጀክቶችን በጥልቀት በመገምገም አጽድቋል።
በበጀት ዓመቱ 130 የምርምር፣ 05 የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም 60 ያህል የማህበረሰብ አገልግሎት ፕሮጀክቶች የሚተገበር መሆኑ እና ፕሮጀክቶቹን ለማስፈጸም 61,500,000 ብር የተመደበ መሆኑ በቀረበው ሰነድ ተገልጻል።
ከተመደበው ጥቅል በጀት ውስጥ 37,500,000 ብር ለምርምር ፕሮጀክቶች እንዲሁም 24,000,000 ለማህበረሰብ ጉድኝት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚውል መሆኑ ተመላክታል።
በመጨረሻም መማክርት ጉባኤው የ2016 ትምህርት ዘመን አካዳሚክ ካሌንደርን በጥልቀት በመገምገም እና የማሻሻያ ሀሳቦችን በማካተት ያጸደቀ ሲሆን፤ በውሳኔው መሰረት መስከረም 21 እና 22/ 2016 ዓ.ም የነባር መደበኛ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው የሚገቡ መሆኑ ተጠቁሟል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ታከለ ታደሰ የ2016 በጀት ዓመት አካዳሚክ ካላንደር እንዲሁም የምርምር፣ ማህበረሰብ ጉድኝት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ፕሮጀክቶች ጥራት ባለው አግባብ እንዲተገበር እጅ ለእጅ ተያይዞ በትብብር መስራት ተገቢ ነው ሲሉ መልእክት አስተላልፈዋል።
➭ «ዕውቀትን በተግባር!!»
@wsu19be
(ሃምሌ 26/2015 ዓ.ም ትምህርት ሚኒስቴር)የ ‘UAE’(የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ) ስኮላርሽፕ አግኝታችሁ የዩኒቨርሲቲ ምደባ ያላገኛችሁ ቀሪ 73 ተማሪዎች ምደባችሁ የታወቀ በመሆኑ የተመደባችሁበትን ዩኒቨርስቲ እና ከየዩነቨርሰቲዉ የምታገኙትን ሰዉ(Contact person) የኢሜል አድራሻ የተቀመጠ ስለሆነ በአድራሻዉ እየተጻጻፋችሁ የምትጠየቁትን እንድታሟሉ እንጠይቃለን፡፡
የተመደባችሁበትን ዩኒቨርሲቲ ዝርዝር [http://rb.gy/pzdd4](https://l.facebook.com/l.php?u=http%3A%2F%2Frb.gy%2Fpzdd4%3Ffbclid%3DIwAR1abctIZFWRPHgf10gRDmw61UAI_oZRJG7GpRDtS2ivSOOxfNb5ZKMU1Mo&h=AT1cfLogKy8TAm3AVXPS28a-zi6k_aWvfX1v5ommEnDOY0TDgVdtuA1_2xcysjOwaG3ObFZgsmr_NyE2U9yO7wmKV0gv0GvkhTvRBXyWLZl4MBTr66KIlIWU2ZTAEf2raEDC&__tn__=-UK-R&c[0]=AT3etRFk7ooIJBGNc1U6SujSc0jjXVSemdbeGcdjTAAgnuX0bgMGrJPeTwtcJmnHKWGaHN2-Qd7RhYosttUJpGJMRiai5h8FP71z1NjtbOjrYtHp_gC8WwnDi-_OLGWvEd10qTXev1KDuQ5rsWPePm77SwNU7_jExduJSVSGICRj39k2ok4PHv84yUK5ctFYM_pdAVqUFNEF) ማየት ትችላላችሁ።
@wsu19be
# **በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2015 ዓ.ም የክረምት ትምህርት መርሃ ግብር** **እንደማይኖር ተገለጸ
___________________________**
ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
የ2015 ዓ.ም የክረምት ትምህርት ፕሮግራምን ይመለከታል::
ትምህርት ሚኒስቴር በተለያዩ ምክንያቶች ላለፉት ዓመታት የተዛነፈውን የትምህርት ካላንደር ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ለማስተካከል እየሰራ ይገኛል::
በመሆኑም በቀረው አንድ ወር ብቻ ትምህርትን ማስቀጠል የማይቻል በመሆኑና ጊዜውን ለማራዘም ደግሞ እንዲስተካከል እየተሰራ ያለውን የትምህርት ካላንደር መልሶ የሚያዛባ በመሆኑ የ2015 ዓ.ም የክረምት ትምህርት የማይኖር መሆኑን እናሳውቃለን::
@wsu19be
Repost from WOLAITA SODO UNIVERSITY STUDENTS UNION
Compliant Form(ቅሬታ ማቅረቢያ ቅጽ)
Dear remedial students use the following link or form to submit your compilients on remedial exam result. https://forms.office.com/pages/designpagev2.aspx?lang=en-US&origin=OfficeDotCom&route=OfficeHome&sessionid=79ad3247-c28b-4f2e-a320-7da07699369e&subpage=design&id=xX4ArEPgTUq_OTQQxNzfvCv_xwtCvf5MojcV4zhA0uNUNzBJM0FTQ1NOSDFPNDJWSTBHM1hCU1FDTS4u&analysis=false
🔷ማስታወቂያ!!
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም በሚከተሉት የዶክትሬት እና የማስተርስ ዲግሪ ትምህርት መስኮች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል👇
@wsu19be
ሰላም ጤና ይስጥልኝ እንዴት አላችሁ ?
ሰላምታዬ በዬአላችሁበት ይድረስ እያልሁ
የተመራቁ ተማሪዎችን ለexit ፈተና በተመለከተ የሚወሰዱ ጥንቃቄዎች እንድታደርሷቸው አደራ እላለሁ
1/ ስትፈተኑ flag(ቀይ) ያበራችሁትን ወደ normal ሳትመልሱ እንዳትልኩት ፣ ብትልኩት አይታረምም
2/ ምርጫ ስትመርጡ መልስ ከቀየራችሁ clear ሚለውን መንካት አለባችሁ ምክንያቱም clear የሚለውን ካልነካችሁ ኮምፒውተሩ save ሚያደርገው መጀመሪያ ያጠቆርኸውን/ሽውን ነው
3/ ሰርታችሁ ስጨርሱ send ማለት ግዴታ መሆኑን አትርሱ
4/ send/ submit answer ካላችሁ በኃላ እንደገና መመለስ(ማስተካከል) እንደማይቻል አውቃችሁ ርግጠኛ ስትሆኑ መላክ እንዳለባችሁ መግለፅ እዎዳለሁ።
ላልሰሙት አድርሱ!!!
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@wsu19be
#ማስታወቂያ‼
💢ለዩኒቨርሲቲያች የሣምንቱ መጨረሻ ተማሪዎች በሙሉ!!
ጉዳዩ፦ ከሰኔ 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ትምህርት የማይኖር መሆኑን ስለማሳወቅ።
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከቀን 23/10/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች የሙከራ ፈተና (mock exam) የሚሰጥበት መርሃ-ግብር እንዲሁም ከሰኔ 26/2015 ዓ.ም ጀምሮ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተማሪዎች እና የመውጫ ፈተና ሀገር አቀፍ የምዘና መርሃ ግብር በተከታታይ ይካሄዳል።
በመሆኑም በዩኒቨርሲቲያችን በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራም የሣምንቱ መጨረሻ ተማሪዎች ከሰኔ 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ትምህርት የማይኖር መሆኑን እየገለጽን፤ መማር ማስተማር የሚጀመርበትን ጊዜ ወደፊት በማስታወቂያ የምናሳውቅ መሆኑን እናሳስባለን።
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር‼
@wsu19be
ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ እንኳን ለ1444ኛው የዒድ አል አድሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ዒድ ሙባረክ!
መልካም የዒድ አል አድሃ በዓል!
@wsu19be
#ማስታወቂያ
አስቸኳይ መልዕክት ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባለቤቶችና አመራሮች በሙሉ
ባሉበት
ጉዳዩ፡- አስቸኳይ መልዕክት ማስተላለፍን ይመለከታል
የመጀመሪያ ድግሪ የመውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለመስጠት ዝግጅት መደረጉ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ተቋማት ለተማሪዎቻቸው በቂ መረጃ ያላደረሱ፣ የትና መቼ እንደሚፈተኑ ያላሳወቁ፣ተማሪዎቻቸው ከሚፈተኑባቸው የመንግስት ተቋማት ሥራ ኃላፊዎች ጋር ያልተወያዩ … ወዘተ ጉድለት እንዳለባቸው ከክትትላችን ለማወቅ ችለናል፡፡
ስለሆነም እነኚህ ክፍተቶች በአጭር ጊዜ እንዲታረሙ እያልን ተማሪዎች መረጃ ባለማግኘት ለሚደርስባቸው እንግልትና ለሚከሰተው ችግር ኃላፊነቱ የተቋማቱ መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
ለማንኛውም ድጋፍና ማብራሪያ የሚከተሉት ባለሙያዎችና ኃላፊዎች እንድታገኙ ይሁን፡፡
ስም ስልክ ቁጥር
1. ጡሪ ጭምዴሳ 0911-78-04-97
2. ታምራት ከበደ 0913-56-67-17
3. ብሩክ አሰፋ 0913-30-77-30
4. አዲስ አለማየሁ 0913-71-57-72
5. ፈሲል ፀጋዬ 0911-33-56-83
@wsu19be
#ExitExam
ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ምን አሉ ?
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸው ምን አሉ ?
- የፈተናው አይነት " የምርጫ ጥያቄ " መሆኑን ገልፀዋል።
- የፈተናው ጥያቄ ብዛት በተመለከተ ጊዜው ሲደርስ እንደሚገለፅ፤ የጥየቄው ብዛት ግን ከ50 በላይ እንደሆነ ፤ በአብዛኛው ፕሮግራም 100 ጥያቄ እንደሚኖር አሳውቀዋል።
- በአብዛኛው ፕሮግራም 100 ጥያቄ ነው ፈተናው ፤ በተወሰኑ መስኮች ምርጫውን ለመሙላት ብዙ ሂሳብ ስለሚሰሩ የጥያቄ ቁጥሩ ከ100 ሊያንስ ይችላል።
- ተማሪዎች ፈተናውን እንደተፈተኑ ውጤታቸውን ወዲያው መላክ የሚያስችል ቴክኖሎጂ ቢሮርም የመጀመሪያ ቀን የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤት ቢገለፅ ሌሎች ላይ ከሚያሳድረው ጫና አንፃር ወይም ፈተናው ቀለል / ከባድ ነው ብሎ እንዳይዘናጋ / እንዳይጨነቅ ወዲያው አይገለፅም። የፈተናው ውጤት የሚገለፀው የመጨረሻው ፈተና ከተሰጠ ከአንድ ቀን በኃላ ነው።
- ውጤት አልፏል ወድቋል ብቻ ሳይሆን ተማሪው ያመጣው ውጤት ይገለፃል።
- የጤና ተማሪዎች ፈተና ሰኔ 30 ይጀምራል እስከ ሐምሌ 8 ድረስ ይዘልቃል። የጤና ተማሪዎች ቀድመው የሚፈተኑበት ምክንያት ቀኑን ሙሉ ፈተናውን ስለሚወስዱ ነው። ጥዋት ላይ ከሙያቸው ጋር የተያያዘውን ይፈታናሉ ፤ ከሰዓት ላይ የመውጫውን ፈተና ይወስዳሉ / በተቃራኒው / ።
- ፈተናው በከፍተኛ ጥንቃቄ ነው የተዘጋጀው ፤ በውስን ኃላፊዎች ብቻ እንዲታወቅ ተደርጓል፤ ስለማይታተም፣ እጅም ስለሌለበት ደህንነቱ አያሰጋንም።
- ፈተናውን ከመስጫው ሰከንድ በፊት ማየት የሚችል ሰው አይኖርም። ፈተናው ካለቀበት ሰከንድ በኃላ መስራት የሚችል ሰው አይኖርም። ይህ በማዕከል ነው ቁጥጥር የሚደረገው።
- የማለፊያው ነጥብ 50 % እና በላይ ሲሆን ይህን ያላለፉ (ኮርስ ያልጨረሱ) ከ5 / ከ6 ወር በኃላ ጥር እና የካቲት ላይ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና መውሰድ ይችለሉ። በዚህም ከለተሳካ ከቀጣይ አመት ተፈታኞች ጋር መውሰድ ይቻላል። በዓመት ሁለት ጊዜ ለመስጠት ታቅዷል።
- አብዛኛው ተማሪ በመጀመሪያው ዙር ያልፋል የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል፤ ካልሆነ ግን በሁለተኛው ዙር ተፈትኖ ያልፋል። ሁለቴ ተፈትኖ ማለፍ ያልቻለ እስከሚያልፍ / 50 % እና ከዚያ በላይ ማምጣቱ እስኪረጋገጥ ፈተናውን መውሰድ ይችላል።
- ፈተናው ተማሪዎች አልተሳካላቸውም ብሎ የማሸማቀቅ ዓለማ ስለሌለው እስኪያልፉ ድረስ መፈተን ይችላሉ።
- ምናልባት ያላለፉ ተማሪዎች ዳግም ፈተና ለመውሰድ መጀመሪያ ሲማሩበት ወደነበረበት ተቋም መሄድ አይጠበቅባቸውም ፤ ባሉበት አካባቢ ባሉ ተቋማት ፈተናውን እንደሚወስዱ የሚደረግበት ሁኔታ ይኖራል።
- ከ50 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች በምረቃ ፕሮግራም ላይ ይሳተፋሉ ? ትምህርት ሚኒስቴር የምረቃ ፕሮግራም በተመለከተ በፖሊሲው ላይ እንደማይፅፍ ገልፀዋል። ጉዳዩ የተቋማት ነው ብለዋል። ሚኒስቴሩ በፖሊሲ የሚያስገድደው ግን የመውጫ ፈተናው የስርዓተ ትምህርቱ አካል ስለሆነ ይህን ያላለፈ ዲግሪ/ጊዜያዊ ጭምር፣ ትራንስክሪብት አይሰጠውም። የምረቃ ፕሮግራም ከማዕከል አይመራም ይህ የተቋማቱ ጉዳይ ነው። እኛ የምንከታተለው ፈተናውን ሳያልፉ ዲግሪ እንዳይሰጣቸው ነው።
- የምረቃ ጉዳይ እና በዕለቱ በምረቃ ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎች ጉዳይ የሴኔት ነው ትምህርት ሚኒስቴር አይመለከተውም። ነገር ግን የመውጫ ፈተናው እየተሰጠ/ ሳይሰጥ በፊት ምረቃ ማድረግ በፍፁም አይቻልም።
- የመውጫ ፈተና ያላለፈ ተማሪ በፍፁም ዲግሪ፣ ቴምፖራሪ ዲግሪ፣ ሰርተፊኬት እንደማይሰጠው አስገንዝበዋል።
@tikvahethiopia
@wsu19be
አትመረቅም ከማለታችሁ በፊት የሚቀድሙ ነጥቦች‼️
( ለሚመለከተው አካል ይድረስ ሁላችሁም ወደተለያዩ ግሩፖች ሼር አድርጉ)
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራት በማለት ተመራቂ ተማሪዎች Exit Exam እንዲወስዱ ተባለ።
ትምህርት ጥራት ተማሪውን ሳታስተምር ፈተና በመፈተን ከወደቅክ አትመረቅም በማለት ይመጣል ወይ?? የትምህርት ጥራት የሚጀመረው ከታች እንጂ ከላይ ነው??
🪭Exit Exam በጣም አሪፍ ሆኖ ሳለ ግን ከዛ የሚቀድሙ ብዙ ነገሮች ነበሩ።
1ኛ--በአብዛኛው ግቢዎች የ #Facility እጥረት አለ። አንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች እንደውም የለም ማለት ይቻላል። #Workshop እጥረቶች ያላቸው ዩኒቨርስቲዎች ብዙ ናቸው።
2ኛ-- የተማሪዎች የምግብ ባጀት እስካሁን ድረስ ለ አንድ ተማሪ በቀን 15 ብር ነው። ግቢዎች በራሳቸው ብጨምሩም እንኳን አብዛኛው ተማሪ ከምግብ ጥራት ማነስ የተነሳ ለተለያዩ በሽታዎች ተዳርጓል ። ( በተለይ ለጨጓራ ህመም😭)
3ኛ--እስካሁን የ Internship ክፍያ ለ አራት ወር 7,800 ብር ነው። አንድ ተማሪ በዚህ ብር አንድ ወር እራሱ በትክክል መስራት አይችሉም።
4ኛ-- የዩኒቨርስቲ #Lecture ደሞዛቸው ዝቅተኛ ስለሆነ ለማስተማር ስመጡ እንኳን በትክክል አያስተምሩም። ተነሳሽነት የላቸውም ፣ በፕሮጀክተር በአንድ ቀን ሁለት እና ከዛ ከዛ በላይ አስተምሮ የሚወጣም አለ። እነ የቱ ይቀድም ነበር???
5ኛ -- በዚህ አመት ተመራቂ የሆኑ ተማሪዎች Exit Exam እንዳለ ያወቁት በዚህ አመት ነው። በዛ ላይ Exit Exam ፈተናው ከ 1ኛ አመት--5ኛ አመት የተማሩትን ያካትታል።
እንኳን 5ት አመት ወደኋለ ተመልሶ ማስታወስ ይቅርና አንድ ሳምንት የተማረውን እንኳን ለማስታወስ በደንብ ከተነበበ ብቻ ነው።
Practical ባሌለበት የትምህርት ስርዓት Exit Exam ፈተኖ ካላለፍክ አትመረቅም ማለት አይከብድም ወይ??
ማንም ብሆን ከ ባቹ (ከጓደኞቹ ) ጋር ነው ደስታውን ማሳለፍ የሚፈልገው። በዛ ላይ ወላጆቹ ፣ ዘመዶቹ ልጃችን ዘንድሮ ይመረቃል ብለው እየጠበቁ ያንተ ምርቃት የለም ስትለው አይከብድህም ወይ???
Part 2 ይቀጥላል ......ለ ብርሃኑ ነጋ አድርሱለት። #Share #Share
ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
👉 @wsu19be
Share share🙏🙏
ለተጨማሪ መረጃ@wsu19be
የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች ከየትኛውም ባች በላይ ከባድ ጫና የደረሰባቸው ባቾች ናቸው።
⚠️ 2011 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሲታረም ስህተት ተሰራባቸው። ትምህርት ሚኒስቴር ምንም እንኳን በማሽኑ የመልስ ቁልፍ "Answer key" ተቀያይሮ መግባት ቢያሳስብብም ስህተቱን አምኖ ተቀበለ።
⚠️ የ12ኛ ክፍል ማለፊያም ከ400 ነጥብ እንዲያዝ ተወሰነ።
⚠️ እጅግ በጣም ብዙ የሚጠበቁ ተማሪዎች ነጥብ ሳይመጣላቸው ቀሩ።
⚠️ ልክ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ ደግሞ የ3 ዓመት ትምህርት ቀርቷል። ኮመን (ፍሬሽማን) ኮርስ ትወስዳላችሁ። ከእዚህ ወዲያም አንድ ዓመት ተጨምሮባችኋል ተባሉ።
⚠️ ትምህርት እንደጀመሩ በየካምፓሱ የብሔር ግጭት ተቀሰቀሰ። እጅግ ብዙ ተማሪዎች ሕይወታቸው በአሰቃቂ ሁኔታ አለፈ።
⚠️ ይሃም አልፎ ትምህርት ሲጀመር የCOVID-19 ወረርሽኝ ተነስቶ ትምህርት ከአንድ ዓመት በላይ ተቋረጠ።
⚠️ ትምህርቱ ሲቀጥልም የባከነ ጊዜ ለማካካስ በሚል አንድ ሴሚስተር በ45 ቀን እንዲያልቅ ሆኖ በሩጫ ተማሩ።
⚠️ ሊመረቁ 3 ሴሚስተር ሲቀራቸው ማለትም 3ኛ ዓመት 2ኛ ሴሚስተር ላይ ሲደርሱም ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ከምርቃት በፊት የመውጫ ፈተና መውሰድ የግድ ነው ተባሉ።
⚠️ አሁን ደግሞ የመውጫ ፈተናውን ያላለፈ ተማሪ ለምርቃት አይቀመጥም የሚል ውሳኔ ተላለፈ።
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ይቀላቀሉን
@wsu19be
ሰላም እንዴት ናችሁ ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሠላማዊ ሰልፍ ቀኑን ከቅዳሜ ወደ ነገ 2:00 ጀምሮ ተቀይሯል ።ምክንያቱም ግቢው መረጃዎችን አጣርቶ ስለደረሠበት ለቅዳሜ አጠቃላይ የግቢ ስብሰባ አለ በማለት ተማሪዎችን በስብሰባው አማካኝነት ሰላማዊ ሰልፉን ማደናቀፍ ስለፈለገ ቀኑን በመቀየር ቅፅበታዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ወስነናል ።
ስለዚህ ወደ ሰልፉ ስንወጣ
1. ላይበራሪው ይዘጋል ቢከፈት እንኳን አንድም ተማረመ እውስጥ እንደይገኝ
2.በየ ዶርሙ ማን እደ ወጣ እና ማን ተለይቶ ከሰላማዊ ሰልፉ እንደሚቀር የሚከታተል እራሱን የቻለ መድበናል
3.ከ fbe ወደ ሜን ካምፓስ እስከ ሁለት ስሀት ሣትበዙ ሶስት አራት እየሆናችሁ ትገባላችሁ
4 .ሁለተኛ እና ሦስተኛ አመት ስለሆንሁ አልወጣም ማለት አይቻልም እንዳልወጣህ መረጃው ቢገኝ ሀላፊነቱን እራስህ ትወስዳለህ
5.በተለይ ሴት ተማሪዎች ስሀት ጠብቃችሁ የማትወጡ ከሆነ ከውስጥ እዶርም ገብተን ቢሆን እናወጣሻለን ውጭ ሁልሽም
6.ማንኛውም ተማሪ የመሣተፍ ሀላፊነት አለበት ተጨማሪ ነገር ካለ እናሳውቃችኋለን።
ሌላው ይህን በየ ግሩፑ ፎርዋርድ አድርጉት ካሁኑ ስሀት ጀምራችሁ።
@wsu19be
በዚህ ውጥረት ውስጥ የመውጫ ፈተና መውሰድ ለተማሪዎች የመኖር ህልውናን እንደማጣት ስለሆነ ሁላችንም በያለንበት ልንቃወመው ይገባል። ሁሉም ተማሪ አንድ በመሆን አንፈተንም የሚለውን ድምፅ ካሰማ እና አንፈተንም ካለ እፈትናለሁ የሚለው የሚለው አካል ማን እንደሚፈትን የምናየው ይሆናል። ግዜው አሁን ነው ጩኸታችንን እናሰማ።
@wsu19be
