uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 697 підписників, посідаючи 8 049 місце в категорії Технології та додатки та 2 173 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 697 підписників.

За останніми даними від 02 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 141, а за останні 24 години на 0, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 28.59%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.37% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 487 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 569 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 03 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 697
Підписники
Немає даних24 години
+147 днів
+14130 днів
Архів дописів
ተቋርጦ የቆየው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዳግም ኤሌክትሪክ መስጠት ጀምሯል ........///........ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ልዩ ስሙ መቃ በተባለ አካባቢ በስርቆት እና ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የአዘዞ-ሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዳግም ኤሌክትሪክ መስጠት መጀመሩን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት በስድስት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት እና ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ዝናብ ምክንያት በአካባቢው ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት የኃይል መቋረጡን በጊዜያዊነት በ87 የእንጨት ምሰሶዎች በመተካት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። በሸኽዲ ከተማና በዙሪያው በሚገኙ ከተሞች ላለፉት 20 ቀናት ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት መልሶ ለማገናኘት የሪጅኑ ጥገና ሠራተኞች ርብርብ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ነው የገለፁት። እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት በተከናወነው ጥገና ምክንያት ከሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በሙሉ የኃይል አቅርቦት ዳግም ማግኘት ጀምረዋል፡፡ ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል ከቀኑ 9:25 ሰዓት ላይ ዳግም ማገናኘት ተችሏል ያሉት አቶ በላይነህ በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ሠራተኞች በሙሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

ጣቢያው በሁለተኛ ዲግሪ ያሠለጠናቸውን ሠራተኞች አስመረቀ ....///..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከጅማ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር  በኤሌክትሪካል  ፓወር ምህንድስና በሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 20 ሠራተኞች ዛሬ አስመርቋል። በዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው የተመረቁት አንድ ሴት እና 19 ወንድ  ሠራተኞች መሆናቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ ገልጸዋል። ሠራተኞቹ ከመደበኛ ሥራቸውን ጎን ለጎን በሚሰሩበት የሙያ ዘርፍ እውቀታቸውን በማሳደግ ራሳቸውን እና ተቋማቸውን እንዲለውጡ ታስቦ የትምህርት ዕድሉ መመቻቸቱን አስታውቀዋል። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው የዛሬ ተመራቂዎችን ጨምሮ ለሦስተኛ ጊዜ ሠራተኞቹን አስተምሮ ማስመረቁን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በቀጣይም ከዩኒቨርስቲው ጋር በመተባበር ለጣቢያው ሠራተኞች የሚሰጠው የትምህርት ዕድል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ሠራተኞች በትምህርት ቆይታቸው ከዩኒቨርሲቲው ያገኟቸውን አዳዲስ እውቀቶች ተጠቅመው ተቋማቸውን አንድ እርምጃ ለማራመድ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። ተመራቂ ተማሪዎች በበኩላቸው የተቋሙን ችግር የሚፈቱ ጥናቶችን ጨምሮ በሥራ ቦታ ላይ የሚያጋጥሙ የእውቀት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያግዙ ትምህርቶችን እንዳገኙ ገልጸዋል። ተመራቂዎቹ ከሥራቸው ጎን ለጎን ትምህርታውን ተከታትለው እንዲመረቁ ጣቢያው እና ተቋሙ ላደረጉላቸው ድጋፎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ሠራተኞቹ በዩኒቨርስቲ ያገኙትን እውቀት ካላቸው ልምድ ጋር አጣምረው  ተግባራዊ በማድረግ የጣቢያውን ምርታማነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ነን ብለዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በጣቢያው የተተከለው ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለአገልግሎት ዝግጁ ተደርጓል .........///....... በአዳማ ቁጥር ሁለት የማከፋፈያ ጣቢያ የተተከለው ተጨማሪ ትራንስፎርመር ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት በአዳማ የሚስተዋለው የኢንዱስትሪና የከተማ መስፋፋት የኃይል ፍላጎት እንዲጨምር አድርጓል። ማከፋፈያ ጣቢያው እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ማስተናገድ የማይችልበት ደረጃ ላይ በመድረሱ የአቅም ማሳደግ ሥራ መስራት እንዳስፈለገ ተናግረዋል። ጣቢያው በ132/15 ኪሎ ቮልት አገልግሎት የሚሰጡ ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮች እንደነበሩት ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል። ለአዳማ ኢንደስትሪ ፓርክ በ33 ኪሎ ቮልት አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ተጨማሪ ትራንስፎርመር መተከሉን ገልፀዋል። በሪጅኑ በራስ አቅም የተከናወነው የትራንስፎርመ ማስቀመጥ ሥራ የጣቢያውን አቅም በ50 በመቶ ከማሳደግ ባለፈ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ያለ ተፈጥሮ ወንዝና ግድብ ከውሃ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሙከራ፤ .....///..... አንድ አሜሪካዊ ያለ ተፈጥሯዊ ወንዝ ወይም ግድብ የሚሰራ “ዝግ-ሉፕ” የተሰኘ የውሃ ኃይል ማመንጫን ሙከራ አድርጓል፡፡ ማመንጫው ተፈጥሯዊ ወንዝ ወይም ግድብ የሌለው ሲሆን የመሬት ስበትን፣ ከፍታን እና ጥቅም ላይ የዋለ ውሃን በመጠቀም በደረቃማና ግድብ በሌላቸው አካባቢዎች ጭምር የማያቋርጥ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ነው። ይህ ግኝት ከአሁን ቀደም የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ ያልነበሩ አካባቢዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ተብሏል። ማመንጫው በቀን ውስጥ የፀሐይ ኃይልን ወይም የንፋስ ኃይልን በመጠቀም ውሃን ወደ ከፍተኛ ከፍታ ማጠራቀሚያ ቦታ በመውሰድ የሚሰራ ሲሆን ከፍተኛ ፍላጎት በሚኖርበት ወይም ፀሐይ በምትጠልቅበት ስዓት ደግሞ ውሃውን ወደ ታች በተርባይኖች በመልቀቅ እንደ ውሃ ኃይል ማመንጫዎች ኤሌክትሪክ ያመነጫል። ከዚያም ውሃው በታችኛው የተፋሰስ ቦታ ላይ ተሰብስቦ በፓምፖች አማካኝነት እንደገና ጥቅም ላይ እንዲውል የሚያስችል ሲሆን ኃይልን እንደ ባትሪ ማከማቸት እና ለግሪድ ፍላጎቶች ወዲያውኑ ምላሽ ለመስጠትም የሚረዳ ነው ተብሏል። ይህ ግኝት ብዙውን ጊዜ የጎርፍ አደጋን ከሚያስከትሉ፣ ነዋሪዎችን እና የዱር እንስሳትን ከሚያፈናቅሉ ግድቦች በተቃራኒ የአካባቢ ተጽዕኖ የሌለው፣ የተፈጥሮ ወንዞችን አቅጣጫ የማያስቀይር፣ በዓሳን ሀብት የተሰማሩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን የማይጎዳ እና ግዙፍ የግንባታ ሥራዎችን የማይፈልግ ነው። በተጨማሪም ማመንጫው በረሃን ጨምሮ ጥቅም ላይ ባልዋለ መሬት እና አነስተኛ የነዋሪ ቁጥር ባላቸው ቦታዎች በመገንባት በአካባቢው ያለውን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት ያስችላል። ያለ ተፈጥሮ ወንዝና ግድብ ከውሃ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ሙከራው በአሜሪካ በአሪዞና እና ኔቫዳ ግዛቶች ተሞክሮ ከ80 በመቶ በላይ ውጤታማ በመሆን ከሊቲየም ባትሪዎች እኩል አቅም እንዳለው ተረጋግጧል። ግኝቱ ግዙፍ የኃይል መሰረተ ልማት ግንባታ ሳይፈልግ እና ጥቅም ላይ የዋለ ውሃን በመጠቀም ታዳሽ ኢነርጅን ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ማከፋፈያ ጣቢያዉ የአካባቢዉን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ እየሰራ ነዉ ………///…….. የቱለፋ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢዉ ለተሰማሩ ኢንዱስትሪዎች እና ለነዋሪዎች የኃይል ፍላጎት ተደራሸ ለማደረግ እየሰራ መሆኑን የጣቢያዉ ኃላፊ አስታወቁ። የጣቢያው ኃላፊ አቶ አዲሱ ከፍአለ ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዉ በአካባቢዉ ያለዉን የኢንቨስትመንት ፍሰት መሰረት አድርጎ በ2012 ዓ.ም ወደ ሥራ መግባቱን ገልፀዋል። ጣቢያዉ በ132 ኪሎ ቮልት የተቀበለውን ኃይል 50 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል የመሸከም አቅም ባለው ትራንስፎርመር አማካኝንት ለቡልጋ ከተማ፣ አሌልቱ፣ ጨፌ ዶንሳ፣ ሰንዳፋ እና ሸኖ ከተሞችና አካባቢያቸው ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ አቶ አዲሱ ተናግረዋል።  እንደ ኃላፊው ገለፃ ጣቢያው በአካባቢው ያለውን የኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎት መሰረት አድርጎ የተቋቋመ በመሆኑ በቡልጋ ከተማ መስተዳድር እና አካባቢዉ የተሰማሩ 59 ፋብሪካዎችን የኃይል ተጠቃሚ ማደረግ ችሏል። በሌላ በኩል ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያዉ በደብረ ብርሃን ቁጥር ሁለት እና ለገጣፎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል ላይ በመገኘቱ የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥም በቅንጀት በመስራት ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መቻሉንም አክለዋል። በአካባቢዉ የሚስተዋለውን የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ የማከፋፈያ ጣቢያ ለመገንባት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ተንቀሳቃሸ ማከፋፈያ ጣቢያው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል …..…///…..… የገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በቅርቡ ወደ ሥራ ያስገባዉ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለደንበኞች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩን የጣቢያዉ ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊዋ ወ/ሮ አበበች ሸዋለም እንደገለፁት ጣቢያው በ230 ኪሎ ቮልት ከፊንጫ፣ ጌዶ 1 እና 2፣ ሰበታ፣ ሱሉልታ እና ሸጎሌ በስድስት ገቢ መስመሮች ኃይል ያገኛል፡፡ ጣቢያዉ በሁለት ባለ 50 እና ሁለት ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል ፓወር ትራንስፎርመሮች ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀዋል። እየጨመረ የመጣውን የደንበኞች የኃይል ፍላጎት ለማሟላት በቅርቡ ወደ ሥራ የገባው ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በ15 ኪሎ ቮልት በገፈርሳ ዙሪያ ለሚገኙት አካባቢዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ኃላፊዋ ተናገረዋል። እንደ ኃላፊዋ ገለፃ ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያው በዙሪያው ያሉ ግለሰብ የኃይል ተጠቃሚ እና የንግድ ቤት ደንበኞችን ጨምሮ በዙሪያው የሚገኙ ከ400 በላይ ትንንሽና ትልልቅ አምራች ኢንደስትሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ተጨማሪ አቅም ፈጥሯል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በአካባቢዉ ለተሰማሩ የኢንቨስትመት ዘርፎች በበቂ ሁኔታ ኃይል እየቀረበ ነዉ .....…///…..… በቡራዩ ከተማ እና አካባቢው የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎትን ያገናዘበ በቂ አቅርቦት መኖሩን የከተማው ምክትል ከንቲባ አስታወቁ። ምክትል ከንቲባው አቶ ሽብሩ ዓለሙ እንደተናገሩት በቡራዩ ከተማ እና አካባቢዉ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ከተሰማሩ 356 ባለሀብቶች መካከል 276ቱ ወደ ምርት የገቡ ሲሆን 86ቱ ሥራ ለመጀመር በሂደት ላይ ናቸዉ፡፡  የኃይል አቅርቦት ለኢንዱስትሪ መስፋፋት የማይተካ ሚና እንዳለው የጠቀሱት ምክትል ከንቲባው አቶ ሽብሩ ከተማዋ ለኢንደስትሪ ተመራጭ በመሆኗ ተጨማሪ የኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልጋት ጠቁመዋል። 60 ዓመታት ያስቆጠረው የገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅሙን በማሳደግ ያከናወናቸዉ ተግባራት እያደገ የመጣዉን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ አስችሎታል ብለዋል።  በቡራዩ ከተማ እና አካባቢዉ ለሚገኙ ከ270 በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት ተደራሽ በማድረግ ለበርካታ የአካባቢዉ  ነዋሪዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ምክትል ከንቲባው አመልክተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ስለ ገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጥቂት እውነታዎች 📌     በ1954 ዓ.ም. ግንባታዉ ተጀምሮ በ1958 ዓ.ም አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ 📌     ከፊንጫ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ230 ኪሎ ቮልት መስመር ኃይል ተቀብሎ ለአስኮ እና አካባቢዉ እንዲሁም ለአዲስ ዓለም እና ፍቼ ከተሞች ኤሌክትሪከ በማቅረብ ነው ሥራ የጀመረው፡፡ 📌     በማዕከላዊ 1 ሪጅን ከሚገኙት 21 ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል አንጋፋ ጣቢያ ነው፡፡ 📌     በአሁኑ ወቅት በ230 ኪሎ ቮልት ከፊንጫ፣ ጌዶ 1 እና 2 ፣ ሰበታ፣ ሱሉልታ እና ሽጎሌ ኃይል ተቀብሎ በ132 ኪሎ ቮልት 4 ወጪ መስመር፣ በ15 ኪሎ ቮልት 20 ወጪ መስመር፣ በ45 ኪሎ ቮልት አንድ ወጪ መስመር እንዲሁም በ66 ኪሎ ቮልት አንድ ወጪ መስመር በአጠቃላይ በ26 ወጪ መስመሮች ኃይል እየሰጠ ይገኛል። 📌     ጣቢያው ከአንድ ማመንጫ ጣቢያ ኃይል በመቀበል በአንድ አዉቶ ትራንስፎርመር እና አንድ ፓወር ትራንስፎርመር ኃይል ሲያከፋፍል ቆይቷል፤ በአሁኑ ወቅት አቅሙን በማሳድግ  500 ሜጋ ቮልት አምፔር ኃይል የመሸከም አቅም ፈጥሯል፡፡ 📌     ትራንስፎርመሮቹ  በ230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀበለዉ በ132 ኪሎ ቮልት ኃይል ሊሰጡ የሚችሉ 4 አዉቶ ትራንስፎርመሮች እንዲሁም በ132 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን የሚያስተናግዱ 4 ፓወር ትራንስፎርመሮች ናቸው፡፡ 📌     የሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን እና ጥገና ኃላፊ አቶ ጌትነት ተስፋዬ ጣቢያው የደንበኞቹን የኃይል ፍላጎትን ለማሟላት ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን እያሳደገ መምጣቱን ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን መፈተሽ ያስፈልጋሉ ……..///…….. ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለመፍጠር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን መፈተሸ እንደሚገባ የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዎን ጤሞቲዎስ (ዶ/ር) ገለጹ። አፍሪ-ራን በተሰኘው እና ምክንያታዊ የናይል ወንዝ አጠቃቀም እና ቀጣናዊ ውህደት በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት ምክክሩ በአካባቢው ትብብርን ለማጠናከር ጥሩ እርምጃ መሆኑን አንስተዋል። ለዘላቂ የኢንዱስትሪ ልማት፣ ለሥራ ፈጠራ እና ለአየር ንብረት ለውጥ መቋቋም አስተማማኝ እና ፍትሃዊ የኃይል አቅርቦት መሰረት ሆኖ ማገልገል አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ይህንን ለማሳካት የጋራ መሰረተ ልማት፣ የተጣጣሙ ፖሊሲዎች እና ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ንግድ የአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳን እቅዶች ለማሳካት ወሳኝ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአፍሪካ ሚሊየኖች የኤሌክትሪክ አገልግሎት የማያገኙ በመሆናቸው ቤቶች ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ፣ ኢኮኖሚን ለማነቃቃት እና ወጣቶችን ወደ ሥራ ለማሰማራት የጋራ ፍላጎትን ማሰባሰብ ያስፈልጋል ሲሉ ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋትና  ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለማጠናከር አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮች እንደሚያስፈልጉ ገልጸዋል። አፍሪራን ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም መርህ የናይል ወንዝ ውሃ አጠቃቀም ገዢ መርህ በማድረግ በናይል ወንዝ ፍትሐዊነት ማረጋገጥ እንዲቻል ዓላማ ይዞ የተቋቋመ ዓመታዊ ቀጣናዊ ኮንፈረንስ  ሲሆን ዘንድሮ በዋናነት ትኩረቱን የመንግሰትና የግል ሴክተር ትብብር የፋይናንስ ምንጮች ላይ አድርጎ መክሯል። "ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ለአካታችና ዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል የተካሄደው ኮንፈረንስ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ምሁራን እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 11 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

esti check afirgew