ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 572 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 384,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 572 名订阅者。

根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 0,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.89%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.48% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 026 次浏览,首日通常累积 2 408 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 572
订阅者
-224 小时
-37
无数据30
帖子存档
photo content
+4

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ አካላት በቁጥጥር ሥር ውለዋል ……///…. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኮምቦልቻ 2 ወደ ኮምቦልቻ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን በደቡብ ወሎ ዞን የቃሉ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የተፈፀመው ስርቆት ለአንድ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ መውደቅና በኮምቦልቻ፣ በደሴ አቀስታ እና ዓለም ከተሞች እና አካባቢያቸው ለመብራት መቋረጥ ምክንያት ሆኖ ነነበር፡፡ በስርቆቱ የተሳተፉ አራት ግለሰቦችን ማለትም ሁለቱ በስርቆቱ በቀጥታ የተሳተፉ፣ አንድ ገዥ እና ቀሪው የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያካሄደ እንደሚገኝ የገለፀው ፖሊስ ፅ/ቤቱ ምርመራውን በፍጥነት በማጠናቀቅ ለፍርድ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም አስታውቋል፡፡ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ስርቆት የወንጀል ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን በመረዳት በመሰል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካልት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም ፖሊስ አሳስቧል፡፡ በቀጣይም በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀም ስርቆትን ለመከላከል ከማህበረሰቡና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራ ገልጿል፡፡ የኢነርጂ አዋጅ 810/2006 አንቀጽ 26 በኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ ወይም ማከፋፈያ ተቋማት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም ሰው ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ወይም እስከ 50 ሺህ ብር በሚደርስ ገንዘብ ወይም በሁለቱም እንደሚቀጣ ይደነግጋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የህፃናት ማቆያ ማዕከሉ የሠራተኞችን ጫና እያቃለለ ነው ……….///……….. የአዋሽ ሁለት እና ሶስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የህፃናት ማቆያ ማዕከል በመከፈቱ በሥራ ላይ የሚገጥማቸውን ጫና እያቃለለ መሆኑን የጣቢያው ሠራተኞች ተናገሩ፡፡ በማዕከሉ ልጆቻቸውን በማቆየት ተጠቃሚ የሆኑ የጣቢያው ሰራተኞች እንደተናገሩት ጣቢያው ከሰኞ እስከ አርብ  ልጆቻቸውን ተቀብሎ በመንከባከቡ የሥራ ጊዜያቸውን ለሥራ ለማዋል አስችሏቸዋል፡፡ ማዕከሉ በጣቢያው ውስጥ መከፈቱ ልጆቻቸውን ያለስጋት እንዲቆዩ እና በቅርበት እንዲንከባከቡ ማስቻሉን ተናግረዋል፡፡ በጣቢያው የንብረት አስተዳደርና አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ኮከቤ ተመስገን በበኩላቸው ሁሉም የጣቢያው ሠራተኞች በእውቀት፣ በቁሳቁስ እና በጉልበታቸው በማገዝ ሥራ እንዲጀምር ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡ ማዕከሉ ለጊዜው ስድስት ህፃናት ተቀብሎ በአንድ ተንከባካቢ ሰራተኛ ስራውን መጀመሩን አስረድተዋል፡፡ 💡"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

ሪጅኑ ለኦዲት ግኝቶች ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዳለበት ተገለፀ፤ ….///…. ሪጅኑ ለኦዲት ግኝቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ለተቋማዊ ለውጡ ስኬት የበኩሉን ሚና ሊወጣ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውስጥ ኦዲት ዘርፍ አሳሰበ፡፡ ዘርፉ ከምስራቅ ሪጅን አንድ ለተውጣጡ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች በተቋማዊ ለውጡ እና በውስጥ ኦዲት ሥራዎች ዙሪያ በድሬድዋ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጋ ተረፈ እንደገለጹት ስልጠናው ሪጅኑ ሥራውን ግልፅነትንና ተጠያቂነትን ባሰፈነ መልኩ በማከናወን ተቋሙ እየተገበረ ያለውን ተቋማዊ ለውጥ ለማሳካት የሚችሉበትን ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡ የውስጥ ኦዲት ሥራ የተቋሙን የመልካም አስተዳደር፣ የሥራ ቅልጥፍናና የፋይናንስ ጤንነት እንዲሁም የቁጥጥር ሥርዓቱን በመገምገምና በማሻሻል ተቋማዊ ስኬትን ለማምጣት እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ ኦዲትን ከፋይናንሽያል ምርመራ ጋር ብቻ የማያያዝ አመለካከት መኖሩን የጠቆሙት አቶ መርጋ ዘርፉ ይሄን አመለካከት ለማስተካከል ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ተግባራትን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ ሪጅኑ የሚያከናውኗቸው ሥራዎች በተቋሙ የተቀመጡ ፖሊሲዎችና ደንቦችን የተከተለ እና ከብክነት የፀዱ መሆናቸውን በማረጋገጥ እንዲሁም ለኦዲት ግኝቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት በኩል ሚናውን ሊወጣ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ የውስጥ ቁጥጥርን በማጠናከር፣ የስጋት አስተዳደርን በማሻሻል፣ የሕግና ደንብ ተገዢነትን በማረጋገጥ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ማስፈን ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ የውስጥ ኦዲት ሥራውን በተሳካ ሁኔታ ለማከናወን ሁሉም በእኔነት ስሜት እንዲሰራ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ፕሮጀክቱ ከመተግበሩ በፊት ጥናት መካሄዱ ተቀባይነቱ እንዲጎላ አድርጎታል ………///……… የአርባ ምንጭ 2ኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅእኖ ጥናት መከናወኑ ፕሮጀክቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረጉ ተገለፀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የካሳ ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ ኢዘዲን ሸምሱ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ሥነ ምህዳርና በማህበረሰቡ ላይ ሊፈጥር የሚችለው አወንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ እና ተፅዕኖዎችን እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል ከዞን እስከ ቀበሌ ካሉ የመስተዳድር አካላት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ ግንባታው የሚካሄድበት ቦታ ለ140 ግለሰቦች ለቤት መስሪያነት በመመራቱና በውስጡም ስምንት መቃብሮች መኖራቸው በጥናቱ ስለተለየ ከዞን መስተዳደር፣  ቤት እንዲሰሩ ከተመሩ ግለሰቦች እና ከሟች ቤተሰቦች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የማስተላለፊያ መስመሩ ለማህበራዊ አገልግሎት በተሰጠ ቦታና በዞኑ አስተዳደር ህንፃ ላይ እንደሚያልፍ በጥናቱ በመረጋገጡ የሚዘረጋበት ቦታ እንዲቀየር መደረጉንም አቶ ኢዘዲን ጠቅሰዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ የተካሄደው ጥናት በኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ማረጋገጫ ተሰጥቶት እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ወደ ትግበራ መገባቱንም ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ ጥናትና ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ሳይደረግ ወደ ሥራ ቢገባ ኖሮ በማህበረሰቡ ተቀባይነት ላያገኝ ይችል ነበር ያሉት አስተባባሪው ይህም በግንባታ ሥራው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ አማካሪ ባዮሰን ፓወር ኩባንያ የአርባ ምንጭ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች እንዲሁም የጤናና የሥራ ላይ ደህንነት ባለሙያ አቶ ቤካን ዳምጠው በበኩላቸው ሥራ ተቋራጩ አካባቢውን የማይበክሉ ማሽነሪዎች እንዲጠቀም እና ለፕሮጀክቱ ግንባታ የዋሉ የተለያዩ ተረፈ ምርቶች በአግባቡ እንዲወገዱ ክትትል እየተደረገ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠ https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+2

ለተቋረጠው ኃይል ጊዜያዊ መፍትሄ ተሰጥቷል .........///....... ትናንት በስርቆት ምክንያት የወደቀው የኮምቦልቻ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር  የብረት ምሰሶ በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶ መተካቱን  በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት በኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው ዝርፊያ የወደቀውን የብረት ታወር በእንጨት ምሰሶ ሲተካ የተፈታታውን ታወር ደግሞ በማጥበቅና የጎደሉ አካሎችን በማሟላት አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጓል። ለጊዜው በተከናወነው ጥገና  በኮምቦልቻ ከተማና አካባቢው፣ በደሴ ከተማና አካባቢው፣ በአቀስታ ከተማና አካባቢው እንዲሁም በዓለም ከተማና አካባቢው የተቋረጠው ኃይል ማምሻውን መመለሱን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 7 ቀን 2017 ዓ.ም

ፕሮጀክቱ ከመተግበሩ በፊት ጥናት መካሄዱ ተቀባይነቱ እንዲጎላ አድርጎታል ………///……… የአርባ ምንጭ 2ኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅእኖ ጥናት መከናወኑ ፕሮጀክቱ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረጉ ተገለፀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የካሳ ጉዳዮች አስተባባሪ አቶ ኢዘዲን ሸምሱ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ ግንባታ ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ሥነ ምህዳርና በማህበረሰቡ ላይ ሊፈጥር የሚችለው አወንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖ እና ተፅዕኖዎችን እንዴት ማስቀረት እንደሚቻል ከዞን እስከ ቀበሌ ካሉ የመስተዳድር አካላት እና ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ ግንባታው የሚካሄድበት ቦታ ለ140 ግለሰቦች ለቤት መስሪያነት በመመራቱና በውስጡም ስምንት መቃብሮች መኖራቸው በጥናቱ ስለተለየ ከዞን መስተዳደር፣  ቤት እንዲሰሩ ከተመሩ ግለሰቦች እና ከሟች ቤተሰቦች ጋር በመነጋገር መፍትሔ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የማስተላለፊያ መስመሩ ለማህበራዊ አገልግሎት በተሰጠ ቦታና በዞኑ አስተዳደር ህንፃ ላይ እንደሚያልፍ በጥናቱ በመረጋገጡ የሚዘረጋበት ቦታ እንዲቀየር መደረጉንም አቶ ኢዘዲን ጠቅሰዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ የተካሄደው ጥናት በኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ማረጋገጫ ተሰጥቶት እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ወደ ትግበራ መገባቱንም ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ ጥናትና ከማህበረሰቡ ጋር ውይይት ሳይደረግ ወደ ሥራ ቢገባ ኖሮ በማህበረሰቡ ተቀባይነት ላያገኝ ይችል ነበር ያሉት አስተባባሪው ይህም በግንባታ ሥራው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ አማካሪ ባዮሰን ፓወር ኩባንያ የአርባ ምንጭ 2ኛ ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች እንዲሁም የጤናና የሥራ ላይ ደህንነት ባለሙያ አቶ ቤካን ዳምጠው በበኩላቸው ሥራ ተቋራጩ አካባቢውን የማይበክሉ ማሽነሪዎች እንዲጠቀም እና ለፕሮጀክቱ ግንባታ የዋሉ የተለያዩ ተረፈ ምርቶች በአግባቡ እንዲወገዱ ክትትል እየተደረገ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠ https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ፕሮጀክቱ በጥናት ውጤቱ መሰረት እየተከናወነ ነው ……..///……… የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ውጤት መሰረት መከናወኑን በፕሮጀክቱ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያ አስታወቁ፡፡ ባለሙያው አቶ አዲሱ እጅጉ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ በሚከናወንበት ወቅትና ወደ ኦፕሬሽን ሲገባ በአካባቢና በማህበረሰቡ ላይ ሊኖር የሚችለውን አሉታዊና አዎንታዊ ተፅእኖ ለመለየትና መፍትሔ ለማስቀመጥ የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ተካሂዷል፡፡ ጥናቱ ፕሮጀክቱ በአካባቢው መልከዓ ምድር፣ በአየር ንብረት፣ በውሃ አካላት፣ በእፅዋት፣ በእንስሳትና ማህበረሰቡ ላይ ጉዳት ማድረሱንና አለማድረሱን ለማወቅ ትኩረት ያደረገ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡ በጥናቱ ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት መሳተፋቸው እና ጥናቱ በትክክለኛመረጃ ላይ ተመስርቶ መከናወኑ ፕሮጀክቱ ወደ ትግበራ ሲገባ በማህበረሰቡ ተቀባይነት እንዲኖረው ከማድረግ ባለፈ ከማህበረሰቡ ለሚነሱ ጥያቄዎች በጥናቱ መሰረት ምላሽ መሰጠቱን ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም መሬታቸው በፕሮጀክቱ ለተወሰደባቸው አካላት አስፈላጊውን የካሳ ክፍያ ለመፈፀም፣ ማህበረሰቡ በፕሮጀክቱ ላይ የባለቤትነት ስሜት እንዲኖረው እና ፕሮጀክቱን በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን ለማድረግ ማገዙንም አስረድተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ አሁን ለደረሰበት አፈፃፀም የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ ጉዳዮች ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ባለሙያው አመልክተዋል፡፡                                                                                                                     የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በአርሲ ዞን ሂጦሳ ወረዳ ከሚገኙ ቀበሌዎች አራቱን  ያካልላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠ https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠  https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት የተነሳ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል .........///....... ከኮምቦልቻ 2 ወደ ኮምቦልቻ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ ዛሬ ከረፋዱ 5:30 ሰዓት አካባቢ በአንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ አንድ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደገለፁት በኮምቦልቻ ከተማ አቅራቢያ በተፈፀመው ዝርፊያ አንድ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ሲወድቅ ሌላኛው ተፈታቶ ከመውደቁ በፊት ተደርሶበታል። በዚህ የተነሳ በኮምቦልቻ ከተማና አካባቢው፣ በደሴ ከተማና አካባቢው፣ በአቀስታ ከተማና አካባቢው እንዲሁም በዓለም ከተማና አካባቢው ኃይል መቋረጡን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። የኮምቦልቻ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ደሴ በ66 ኪሎ ቮልት፣ ወደ አቀስታ እና ዓለም ከተማ ማከፋፈያ ጣቢያዎች በ132  ኪሎ ቮልት እንዲሁም ለኮምቦልቻ ከተማ በ15 ኪሎ ቮልት ኃይል ሲሰጥ ነበር። የወደቀውን የብረት ምሰሶ መልሶ ለማቆምና የመውደቅ ስጋት ያጠላበት ሁለተኛውን ምሰሶ በሌሎች ድጋፎች መልሶ ለማቆም ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ ህብረተሰቡ ችግሩን ተገንዝቦ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ከባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስተር ጋሲማ ኒያሞ ሀንጋ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል። ኒያሞ ሀንጋ የታንዛኒያን ብሎም የቀጣናውን ኢነርጂ ዘርፍ በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ቋት በኩል ለማላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ባለራዕይና ቁርጠኛ መሪ ሲሉ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋቸዋል። በተሽከርካሪ ድንገተኛ አደጋ በደረሰባቸው ህልፈት በእጅጉ ማዘናቸውን ያስታወቁት ኢንጂነር አሸብር ለቤተሰቦቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸውና ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ኩባንያ መጸናናትን ተመኝተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

Condolence Message from the CEO of Ethiopian Electric Power (EEP) It is with profound sorrow that I extend my heartfelt condolences on the sudden and tragic passing of Mr. Gissima Nyamo-Hanga, Managing Director of TANESCO, who lost his life in a road accident. Mr. Nyamo-Hanga was a committed and visionary leader whose efforts significantly contributed to advancing the power sector in Tanzania and the regional power trade through the Eastern Africa Power Pool (EAPP). His passing is a significant loss to TANESCO and the broader energy community in EAPP. I express our deepest sympathies to his family, colleagues, and the TANESCO family on behalf of EEP and myself. May you find strength during this difficult time, and may his soul rest in eternal peace. Eng. Ashebir Balcha Chief Executive Officer, EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content