uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 554 підписників, посідаючи 8 397 місце в категорії Технології та додатки та 2 165 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 554 підписників.

За останніми даними від 21 червня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 10, а за останні 24 години на 1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 25.74%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 14.94% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 003 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 323 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 9.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 22 червня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 554
Підписники
+124 години
+87 днів
+1030 день
Архів дописів
#AdwaMuseum #GERD የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት የተለያየ አበርክቶ ለነበራቸው ተቋማትና ግለሰቦች የሰጠው የምስጋና እና እውቅና መርኃ ግብር በከፊል፤ 👇 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+9

photo content
+9

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት የተለያየ አበርክቶ ለነበራቸው ተቋማትና ግለሰቦች የሰጠው የምስጋና እና እውቅና መርኃ ግብር በከፊል፤ 👇 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

photo content
+9

photo content
+9

#AdwaMuseum የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ በአደዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ያዘጋጀው የምስጋና ፕሮግራም ድባብ ፤ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ባዘጋጀው የምስጋና መርኃ ግብር ላይ ለመታደም የተገኙ የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየምን ሲጎበኙ፤ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

"ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ብዙ መከራዎችን እና ፈተናዎችን አልፈን አንድነታችን ያጸናንበት ነው" - አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ........///....... ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ብዙ ፈተናዎችን በማለፍ  ወደ ብልጽግና የምናደርገው የጋራ ጉዞ ቃል ኪዳንናችን ያጸናንበት ነው ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ገለጹ። ሰብሳቢው አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁንና ለምርቃት መብቃቱን አስመልክቶ ተቋሙ ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ በግንባታው ሂደት አስተዋጽዖ ለነበራቸው በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ጠንካራ አመራርን፣ ሙያዊ አስተዳደርን፣ ከመንግሥት፣ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ከጠቅላላ የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ጽኑ ቁርጠኝነትን የጠየቀ መሆኑን ገልጸዋል። ግድቡ ኢትዮጵያዊያን ተባበርን ከሠራን ቀጣይ የልማትና የብልጽግና እጣ ፈንታችንን በራሳችን የምንወስን መሆናችንን ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡ የግድቡ ግንባታ ከሲቪልና ኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች ጀምሮ የሚመነጨውን ኃይል ወደ ብሔራዊ የኃይል ቋት እስከማስገባት ድረስ የገጠሙትን ውስብስብ ተግዳሮቶች ተሻግሮ ለምርቃት መብቃቱ ለኢትዮጵያዊያን ትልቅ የመቻል ማሳያ መሆኑንም ነው ያብራሩት። ኢትዮጵያውያን የማይጠናቀቅ የሚመስለውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከፕሮጀክት በላይ ደምቆ እንዲጠናቀቅ ማድረጋቸው አዲስ ጅማሮ እንጂ የመጨረሻ እንዳልሆነም ተናግረዋል። ከዚህ በፊት የነበሩ ትውልዶች ሁሉ አስበው  ያልቻሉትን እና አቅደው ያላሳኩትን ፕሮጀክት ማጠናቀቅ መቻሉን የጠቀሱት ዶ/ር አብርሃም ይህን ያሳካው ያሁኑ ትውልድ ዕድለኛ መሆኑን አስረድተዋል። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተባበረ ርዕይ እና ቆራጥነት በብሔራዊም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ አስደናቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ እንደምንችል ያሳየንበት ነው ሲሉ  ገልጸውታል። በምስጋና መርሃ ግብሩ ላይ  ለዚህ ታላቅ ስኬት የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉትን ጨምሮ በየደረጃው አስተዋጽኦ ላደረጉ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ አባላት፣ ልዩ ልዩ ተቋማት እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም  27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎በግድቡ ግንባታ ላይ አበርክቶ ለነበራቸው ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ተሰጠ ‎…....///…..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ  ወቅት የተለያየ አበርክቶ  ለነበራቸው ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና ሰጠ። መርሐ ግብሩ የተከናወነው  የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በስኬት  በመጠናቀቁ አስተዋጽዖ የነበራቸው አካላትን ለማመስገን ነው። የእውቅና ምስክር ወረቀቱንና የተዘጋጀውን ሜዳሊያ የሰጡት የዕለቱ የክብር እንግዳና የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድ ስብሳቢ አብርሃም በላይ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ናቸው። በዕውቅና መርሃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት፣ የፌዴሬሽን ም/ቤት እና  ሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮችን ጨምሮ እንዲሁም ለተለያዩ የሥራ ተቋራጮች፣ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅናና ተሰጥቷል። በተጨማሪም በግድቡ ዙሪያ የሚገኙ እና የታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በቅርበት በመደገፍ እና ትብብር በማድረግ በስኬት እንዲጠናቀቅ ምቹ ሁኔታ ለፈጠሩ  የአካባቢው የመስተዳድር አካላት እና ተቋማት እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ‎💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ‎ ‎📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ‎📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ‎📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ‎📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ‎📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ‎📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ‎📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ‎መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ግድቡ የትውልዱ የአንድነትና የአይበገሬነት ማሳያ እንዲሁም የማንሰራራት ዘመናችን ጅማሮ ትዕምርት ነው -ኢንጂነር አሸብር ባልቻ …..///……  የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የአንድነትና የአይበገሬነት ማሳያ እንዲሁም የማንሰራራት ዘመናችን ጅማሮ ትዕምርት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ ያዘጋጀው የምስጋና ፕሮግራም  የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ፣ ሠራተኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተካሂዷል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደገለጹት ዓለም ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ጨምሮ በቴክኖሎጂ ርቆ በሄደበት በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከ45 በመቶ በላይ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ አይደለም፡፡ ዓባይ ወንዝ ላይ ከ86 በመቶ በላይ ድርሻ ያላት ኢትዮጵያ በድህነቷና በዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች ምክንያት ድንበር ተሻጋሪ ወንዞቿን ተጠቅማ የኃይል አቅርቦቷን በማሟላት ከድህነትና ኋላ ቀርነት ለመላቀቅ ሳትችል መቆየቷን አስታውሰዋል፡፡ መንግስትም የተፈጥሮ ሀብታችንን በመጠቀም ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር ግድቡን በራስ አቅም ገንብቶ ማጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡ ‎የግድቡ ምርቃት ኢትዮጵያውያን በርካታ ችግሮች ቢኖሩብንም በትብብርና በሕብረት ከተነሳን የተፈጥሮ ሀብታችንን ተጠቅመን ከመልማትና የብርሃን ምንጭ ከመሆን የሚያግደን አንዳች ምድራዊ ኃይል አለመኖሩን በተግባር ለሁሉም ያሳየ ብሔራዊ ፕሮጀክት መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ትልልቅ ፕሮጀክቶችን መጀመር ብቻ ሳይሆን መጨረስ እንደምንችል ማሳየት የቻለ እንዲሁም ጨለማ እና ድህነትን ለማፍረስ የተሰነዘረ ሀገራዊ መዶሻ ነውም ብለዋል። የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ተቋሙ የግንባታውን ሂደቱን በመምራት፣ የኃይል ማመንጫ ተርባይኖችን በመትከል፣ ከግድቡ የመነጨውን ኃይል ከሀገሪቱ የኃይል ቋት ጋር በማስተሳሰር ኃላፊነቱን በብቃት ሲወጣ መቆየቱን አስታውሰዋል። ህዳሴ እንደ ሀገር የነበረውን ከ5 ሺህ ሜጋ ዋት ያልበለጠውን ኃይል የማምረት አቅም ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ እንዳደረሰው የጠቆሙት ኢንጂነር አሸብር ይህም ተቋሙ የኃይል ተደራሽነት ሽፋኑን አሁን ካለበት 54 በመቶ ወደ 78 በመቶ ለማሳደግ የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት እና በየዓመቱ በአማካይ በአስር በመቶ እያደገ የሚገኘውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስ እንደሚያስችለው ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል በመሆን የአፍሪካ አህጉርን በመሰረተ ልማት የማስተሳሰር አጀንዳ 2063 ዕቅድን ለማሳካት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ ወደ ሥራ መግባት ከፍተኛ ድርሻ ያበረክታል ብለዋል። የግድቡ መጠናቀቅ ኃይል ከማመንጨት ባሻገር ግብርናን በማዘመን፣ ቱሪዝምን በማስፋፋት፣ የአሳ ሀብትን በማሳደግ፣ ዲፒሎማሲያዊ አቅምንና ብሔራዊ አንድነትን በማጎልበት በኩል ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከፕሮጀክቱ በቀጣይ መሰል ትውልድ ተሻጋሪ ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች በራስ አቅም ገንብቶ መጨረስ የሚያስችል ዕውቀትና ልምድ የተገኘበትም መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡ የኢትዮጵያዊነትና የኢትዮጵያ ከፍታ ለሚታይበት እንዲሁም የትውልዱ ብሔራዊ ፕሮጀክት ለሆነው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ግድብ መጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት እንዲሁም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት በተቋሙ ሥም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የምስጋና ፕሮግራም በአደዋ መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ ነው ‎….///…. ‎የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያዘጋጀው የምስጋና ፕሮግራም በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ ነው፡፡ ‎ ‎በፕሮግራሙ ላይ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድና ሠራተኞች እንዲሁም የተለያዩ ተቋማት ተወካዮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ‎ ‎በመርሃ ግብሩ ላይ የግድቡን የግንባታ ሂደት የሚያሳይ ዶክመንተሪ የሚቀርብ ሲሆን በግድብ ግንባታው አስተዋጽኦ ለነበራቸው ግለሰቦችና ተቋማትም እውቅናና ሽልማት ይሰጣል፡፡ ‎ ‎ፕሮግራሙ በተመሳሳይ ዕለት በሁሉም የኃይል ማመንጫዎች፣ በሪጅኖች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችም በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም