ትዝብተ-በርናባስ🔎✍️
Відкрити в Telegram
ምድር እጅግ ሰፊ ናት፤ እኔ ወንድማችሁ በርናባስ ደግሞ ያሉኝ ሁለት ዐይኖች ብቻ! አባካችሁን ኑ...ና አጋጭተን (ዐይኖች አዋጥተን) እንይ!✍️ አሳብ አስተያየት ቢኖራችሁ፦ @barnica የግላችሁ ነው።
Показати більше1 414
Підписники
-124 години
-27 днів
Немає даних30 день
Архів дописів
1 414
ዘመዶቼ ለሳምንት የጠፋሁባችሁ ከላይ ባኖርሁላችሁ ልጥፍ (post) መሠረት ክፍ'ላገር ስለነበርሁ ነው። እንደው ወደዚህ ግድም አላመጣሁም እንጂ በሳምንቱ በቆይታዬ ለዚህም ሆነ ለሌሎች ምስባኮቼ የሚሆኑ ጥንቅሮችን ከትቤአለሁ። ትዝብቶች፣ ቁጭቶች፣ የነፍስያዬን ጩኸቶች የሚያትቱ ጽሑፎችን ክታቤ ላይ አስፍሬአለሁ።
ከቢሮዬ ተልዕኮ ጋር የሚገናኙ ሥራዎችን ከውኜአለሁ። የምወዳቸውን ጥቂት ሰዎችን አግኝቼ በሸነና ለማለት እድል አግኝቻለሁ። በንፁህ ፍቅራቸው ሁሌም እገረማለሁ። የቀጣዩ ዘመን ጉዞዬን አሰላለፍ በሚመለከት አዳዲስ ውጥኞችን ይዤ ተመልሻለሁ። እናንተስ እንዴት ናችሁ? ከእንግዲህ በሳምንት ስንት ቀናት ልጻፍ? ደግሞ ተናፍቃችኋል።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
ክፍ'ላገር ድሮ ቀረ!
---🔘----
ከበርናባስ በቀለ
ክፍ'ላገርን ክፍ'ላገር የሚያሰኘው ምንድነው? እኔ ሲመስለኝ የማኅበረሰብ ስብጥሩ፣ የባላገሩ ባህልና ወጉ፣ መሃል አገር በቀላሉ የማይገኙ ነገሮች easily access መደረግ መቻሉ ጥቂቶቹ ናቸው። በዚህ ወቅት ግን ክፍ'ላገሩ ወጉን የተወው ይመስላል፤ ባለፉት ሁለት ወራት በቃኘኋቸው ሦስት ከተሞች ያስተዋልሁት ይህንን ነው።
ከተሞች ተመሳሳይ ቅርጽና ዐውድ እየፈጠሩ ይገኛሉ። አንዱን ከተማ ከሌላኛው ለመለየት እስክትቸገሩ ምስስሎሹ ተቀራርቧል። ምናልባት የሉላቀፋዊነቱ (globalization) ተጽዕኖ /effect/ ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ፦ ዛሬ ያለሁባትን ከተማ ከአዲስ አበባ ከተማ የሚለየው እኔና ቤተሰቤ የምንኖረው አ/አ መሆኑ ብቻ ነው።
ያመሸንበት ሰፈር ደግሞ CMC ከኮንቬንሽን ሴንተር ወደ ፍየል ቤት ስትኼዱ ያለው መንገድ ቅርጹ አለ አይደል? በቃ እንደርሱ። እዚህ የሚወስደን ታክሲ ወደ ሪዞርቱ እየወሰድኋችሁ ነው ይለናል፣ እኛ በልባችን ወደ ፍየል ቤት (ሳፋሪ) እየኼድን ነበር። አቤት! ከሰሞኑ አመሻሹ ላይ ፍየል ቤት አካባቢ ያስተዋልሁት ወከባ! መንገዱን ስሻገር ፊልም ላይ እየተወንሁ ያለሁ ነበር የመሰለኝ።
በወከባ ከምትናጥ የጉድ ከተማ ስንመጣ በክፍላገሩ ነፋሻማ vibe ደግሞ ልባችን ለቀቅ ማለት አልነበረበትም? ልዩነት ሂንጅሩ። እዚያም ወከባ እዚህም ወከባ። የከተሞች ፎረምና ምክክር ላይ የምትቀመጡ ሰዎች የምትሰበሰቡት ከተሞቹን መንትያዎች (በሁሉ ነገር የሚመሳሰሉ) ስለማድረግ ነው እንዴ? ኧረ ከአንደኛው ጫፍ ወደ ሌላኛው ስንኼድ የቆየንበትን ጩኸትና ግርግር በመርሳት እንጽናና ዘንድ የድሮ እሴቶችን ተውልን።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
የጃር ውኃ ይቅርባችሁ!😥
-----------
ጓደኛዬና ቤተሰቡ (ባለቤቱና ልጆቹ) በጃር ውኃ ምክንያት ታመው ሆስፒታል ገብተዋል። በተለይ የመጀመሪያ ልጃቸው በከባድ የሐኪሞች ርብርብና እርዳታ ነው የተረፈው። ባለቤቱ ትላንትና ግሉኮስ ላይ እንደዋለች አሁን ደውሎ አሳወቀኝ።
እኛም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የጃር ውኃ ተጠቃሚዎች ነበርንና ከወራት በፊት ከሰማናቸው መረጃዎች ተነስተን የጃር ውኃ አቁመን ነበር። ግን ከቀናት በፊት ውኃ በጣም ባስፈለገን ሰዓት አስመጥተን ተጠቅመናል፣ ሁለቱን ቀናት ዝም ብሎ የሆድ ቁርጠት ነገር ራሴ ላይ አስተውዬ ለባለቤቴ ነገርኋትና ውኃውን አቆምን። ግን የመጣውን ጃር ተጠቅመን ጨርሰናል።
ከዚያም ውኃ ለሚያመጣልን ልጅ ኼጄ ይህን ጃር የሚሉትን ጉድ ግን ባታመጡት (ለሕዝቡ ብትናገሩ) አይሻልም? ብዬው እንደተመለስሁ አስታውሳለሁ። ስለ ወዳጄ ቤተሰብ የሰማሁት ግን አሁን ነው። እርዳታዬ አስፈልጎት በደወለልኝ ሰዓት ስልኬ ዝግ ስለመሆኑ አውርቶኝ ሳምንቱን ያለፉበትን ስቃይ አጫወተኝ።
የኼዱበት ሆስፒታል ሐኪሞቹም "የጃር ውኃ አትጠቀሙ ብለን ለሕዝቡ እየነገርን ነው ግን ሕዝቡ እየሰማ አይደለም። መንግሥት ስላላስቆመ ነው እኛም ጸጥ ያልነው እንጂ ችግሩን በይፋ መናገር እንችል ነበር!" ብለውናል አለኝ። በጣም አዝኛለሁ። ጃር የምትጠቀሙ እባካችሁን አቁሙ። ሌላስ ምን እናድርግ? በዚህ አቅጣጫ የሕግ መንገድ የምታውቁ ማኅበረሰቡን ለመታደግ ምን እናድርግ? ቢያንስ ግን መልእክቱን በማጋራት የጃር ውኃ ተጠቃሚዎችን እንታደግ!!!
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
እሑድም አይደል! እኔ እየተጓዝሁ ነው። ሚስቴና ልጄ ደግሞ ወደ ቤተ ክርስቲያን ኼደዋል። ሲመለሱ (ሳገኛቸው) የት ኼደው እንደነበር እጠይቃቸዋለሁ።
1 414
Repost from መጽሐፉ ይናገር | Official
ቤተ ክርስቲያንን ስታስቡ ጥንቅቅ ያለ ፕሮግራም ተካፍሎ ስለመመለስ፣ ከዐውድ ያላፈነገጠ ትምህርትና ስብከት ተካፍሎ ስለመምጣት አስባችሁ ከሆነ የነገረ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረታችሁ ችግር ገጥሞታል። ቤተ ክርስቲያን ፕሮግራም ተካፍሎ ለመመለስ የሚኬድበት ቦታ ሳይሆን ሕይወት ለመካፈል (ለመቀበልና ለመስጠት) የሚኬድበት ሕያው የሆነ የወንድሞች ኅብረት ነው።
ሕያውነቱ አንዱ ሰው በሌላው ውስጥ በመኖሩ የሚረጋገጥ ነው። ወደ ቅዱሳን ጉባኤ ኺዱ፤ በፍጹም አትቅሩ። ዛሬ ጠዋት በኼዳችሁበት ጉባኤ በስንት ወንድምና እህቶች ልብ ውስጥ በቋሚነት አላችሁ? ስንት ሰዎች actively በሕይወያችሁ ውስጥ መብትና ኃላፊነት አላቸው? እንደርሱ ካልሆነ የኼዳችሁት ወደ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን ወደ አንድ ቆንጆ ማኅበራዊ ክለብ ነው።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
1 414
ነገረ ቀልቀሎ
--🔘---
ከበርናባስ በቀለ
"አንተ ለምን ነገሮችን ሌጣቸውን አትረዳቸውም" ይሉኛል። ሌጣውን ያለ ነገር አለ? ያለ ዐውድ፣ ጊዜና ቦታ የሚነገር ድስኩር ኖሮ ያውቃል? ሲያልፍም የሰጡትን ብቻ የሚቀበል ቀልቀሎ ወይም ስልቻ ነው። ይህም የሆነው ቀልቀሎ ስለ ሰጡት ነገር reflect ለማድረግም ሆነ በሰጡት ነገር እሴት (value) መጨመር የሚያስችለው ስብዕና ስለሌለው ነው። ለሕላዌው የሚያስብለት ሌላ ነው። የሚገለገልበትም ሌላ አካል ነው። አያስብም፣ ማሰብ ስላለመቻሉም አይጨነቅም። አሳቢው ሌላ ነውና የሰጡትን ብቻ ይቀበላል። በእህል ጠቅጥቀው ያኖሩትና የሰጡትን በታማኝነት ሸክፎ ይይዛል። ይመቸው!
እኔ ግን ስብዕና አለኝ። በአምሳለ ስላሴ የተሠራሁ እንደመሆኔ አሳቢና ተመራማሪ አዕምሮ የተጎናጸፍሁ ፍጡር ነኝ። ስለዚህ የሰጡኝን ብቻ የምቀበል አይደለሁም። "ትውፊት፣ ታሪክ፣ ወግና ትርክት ይህን ይላልና ተቀበል" ሲሉኝ ቆዩኝ እስቲ እቀበለው ዘንድ በደንብ ልረዳው እላለሁ። ታዲያ ትርክትና ትውፊት ጠል አይደለሁም ግና ጠያቂ አዕምሮ ያለኝ አማኝ ነኝ። እጠይቃለሁ፣ አሰላስላለሁ፣ ደግሞም በደረስሁበት መረዳት መሠረት ኃላፊነት ወስጄ እወስናለሁ። ምክንያቱም ስልቻና ቀልቀሎ አይደለሁም!
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
"ሰው የገዛ ሕይወቱ ሸማኔ ነው፣ መዘወሪያው ደግሞ ሃሳብ ነው።" ይላሉ የሃሳብ ኃይል አወዳሾቹ። እነዚሁ አስቦ አደሮች "ሃሳብህን ከተቆጣጠርህ የሕይወትህን ፍጻሜ ትቆጣጠራለህ" ብለውም ያምናሉ። አንዲት ጉዳይ ቢጤ እያሰብሁ ነውና እስከ ምን ድረስ ላስብ የሚለውን እያሰብኩኝ ነው።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
የ'ኔ ተራራ! ⛰️
--🔘--
ከበርናባስ በቀለ
አንደኛ ለመሆን አልሠራም። ጎበዝ ለመባል አልፈጋም። ተጽዕኖ ለመፍጠርም አልባትልም። ምድሩን ለማስደመም ድንጋይ አልፈነቅልም። ትላንት በሳቁብኝ በተራዬ ልስቅባቸው ጠብ እርግፍ አልልም። ታዋቂ መሆንም አልፈልግም። ዘመናዊ ለመሆን አላንቧችርም። ከማን አንሼ በሚል ተምች ቢሂል ናላዬ አይዞርም። እጄ ላይ ያለው ነገር ወደ ሰዎች እንዲደርስ ብዬ አልሠራም። እግዚአብሔርንም ላገለግለው ብዬም ያላቅሜ ከመለኮት እሰጥ አገባ ውስጥ አልገባም።
መሆን የምፈለገው "ራሴን"፤ ማሸነፍም የምሻው ራሴን። ለመግዛትም ጦሜ ምጸልየው ራሴን። ተጽዕኖ መፍጠሩንም የምፈልገው በራሴው። ይህ ራሴ አመጸኛ ዓለም ነውና ትግሌ ከርሱ ጋር ነው። መንገዱ የክርስቶስ መስቀል እንደሆነ መጽሐፉ ነግሮኛልና (መድኀኒትነቱም የተፈተነ ነውና) ተስፋ አለኝ። ራሴን ካሸነፍሁ ዓለምን ማሸነፌ የት ይቀራል? ዓለም ምስቅልቅል ውስጥ ያለችው በራሳቸው በተሸነፉ ግን ሌሎችን ለማሸነፍ በሚጋደሉ ሰዎች መሆኑን መች አጣሁት። በቃ የኔ ተራራ! እኔው ራሴ ነኝ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
ሕያዊቷ ማኅበር-- ሕያውነት ከራቃት ዓለሙማ ተስፋ የለውም። እርሷ ለዓለም እውነተኛ ህሊና ናት። የርሷ ህሊና ከጎደፈ ዓለሙማ በጨለማ ይዋጣል።
1 414
Repost from መጽሐፉ ይናገር | Official
ክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር እቅፍ ወጥቶ ለቤዝዖቱ ሥራ መጣ፣ ከክርስቶስ ኢየሱስ ማንነትና ሥራ የድነት ወንጌል ወጣ፣ ከወንጌሉ ውስጥ መሲሓዊቷ ማኅበር (ቤተ ክርስቲያን) ወጣች፣ ከቤተ ክርስቲያን (በኩል) ሕያውነት ወደ ዓለሙ ይወጣል።
------------
Join Us! & Share!!!
@metsihafuyinager
------------
ወደ ውስጥ፦ @adfontess
1 414
በሥራዬ ጉዳይ ወጥቼ ቦሌ Morning Star አካባቢ ያለ ካፌ ውስጥ ነኝ። አጠገቤ አንድ ቆፍጠን ያለ ወጣት አለና ይደወልለታል። ስልኩን አንስቶ ወዳጁን "እ.. እየጠበኩህ ነው አትመጣም?" ይለዋል።
"እየመጣሁ ነው ግን አንተ መኪና ይዘሃል አይደል? የእኔን መኪና ትቼው ልምጣ?" ብሎ ይጠይቀዋል። አጠገቤ ያለው ጎረምሳ "የእኔ መኪና ፓርኪንግ ውስጥ ናት" ያንተን ይዘህ ና እና ሮጥ ብለን እንመለሳለን ይለዋል።
ከዚያም ያኛው ወዳጁ "የእኔ መኪና ላንተ አትሆንም፣ እባክህን ያንተን አውጣ ይለዋል" ኋላም ይኸኛው (አጠገቤ ያለው) ሰው "አንተ ምን ሆነህ ነው? እኔ በሳይክልም መኼድ እችላለሁ እኮ፣ ደግሞ vits እኮ ትልቅ መኪና ነው!" ይለዋል ያኛው እንደተሳቀቀ "እሺ" አለውና ይኸው እየጠበቀው ነው። ቦሌ የሆነ ተፋልሶማ አለ!
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
ካረጁ አይበጁ!
---🔘----
ከበርናባስ በቀለ
ዓለም ዋንጫዋን አስረክባለች። ሌጀንዶቹን እነ ክርስቲያኖንና ሊዮኔል ሜሲን ሸኝታ Yamalንና መሰሎቹን (አዲሱን ትውልድ) ማንቆለጳጰሱን ይዛዋለች። "እኔ የሚያስፈልገኝ አዲስ ትውልድና አሠራር ነው!" (ካረጁ ለእኔም አይበጁ!) የምትል ይመስላል። እርሷ መች ያልቅባትና!
ዓለምዬ (ዓለሚቱ) ጎበዝ ናት ማንን መቼ ተጠቅማ ውጥኗን ማሳካት እንደምትችል ታውቃለች። ለምን ሳር ምድሩ ያደነቀህ... ሰማይ ምድሩ ያጨበጨበልህ አትሆንም? ጊዜህ ሲያልፍ አለፈ ነው። "በእነ እንትና ዋጋ መክፈል የመጣ ለውጥ" እያለች ያለፈውን ዘመን legacy ስታዳንቅ አዳዲሶቿን አትቀርብርም። "አዳዲሶች አሉኝ እኮ" እያለች ቡቃያዎቿን ወደ ምድሩ ፊት ገጽ ታወጣለች።
"ካረጁ አይበጁ" መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅስ ባታገኙለትም ግን ሃሳቡ ጤናማ ነው። እርጅና የፍሬያማነት ዘመን ሳይሆን የእረፍትና አዳዲሶችን የማብቂያ ብሎም የጥሞና ዘመን ነው። ስለ ቀደሙት ሰዎች አሠራርና legacy ለማስቀጠል ሲል አዲሱን ትውልድ ለሚሰዋ ማኅበር ሁሉ አድርሱልኝ። አዲስ ነገር የሚጨንቃቸውና የጥንቱ አሠራር ታማኝ እስረኞች የሆኑት የአመራር መዋቅሮች ከዓለም እንዲማሩ ይህችን ነገር ስደዱልኝ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
አሁን በጨለማው ክምር ላይ ትንሽዬ የብርሃን ተስፋ እያቆጠቆጠች ነው። ቀጥሎ ያለውን ዐረፍተ ነገር ስጽፍ ደግሞ ጨለማው አድራሻውን ሊለቅ ነው። ይኸው ብርሃን! ይኸው ወገግታ። ታዱያ ጎህ ሲቀድ ሊነጋ ሲያቅላላ የብርሃኑ ጮራ ሲፈነጥቅ ጨለማው ደግሞ ሲፈረጥጥ ያዩ ዓይኖቼ የእግዚአብሔርን በጎነት የሚተርክ ዘጋቢ ፊልም እያዩ ይመስል ትዕንግርት ውስጥ ናቸው። እግዚአብሔር ቸሩ!
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
Repost from መጽሐፉ ይናገር | Official
ሰማዩ ዝም ያለ ሲመስለንና ነገረ ዓለሙ ግራ ገብቶን ስንዋትት እግዚአብሔር የነፍሳችን ማረፊያ ነው። እርሱ ልባችንን በሕያውነቱ የሚያሞቅ የደህንነታችን ምንጭ ነው። የሞት ሸለቆ በሚመስል ዝቅታ እያለፍን ያለን ሲመስለን እርሱ የዘላለሙ ከፍታችን ነው። ስለ ነገያችን አስበን እርግጠኝነት ሲጎድለን ዓለማትን በመግቦቱ የያዘው እርሱ መድን ዋስትናችን ነው።
-------
Join Us!
@metsihafuyinager
@metsihafuyinager
-------
በውስጥ፦ @adfontess
1 414
የኢሉሚናቲ መንፈስ!
---🔘-----
ከበርናባስ በቀለ
ከሰሞኑ ሚስቴና ልጄ ለጋራ ተልዕኳችን ኼዴዋልና ሳምንቱን ላጤ ነኝ። ምግብ ሠርቼ መብላት እችላለሁ፣ ኧረ ማብላትም እችላለሁ። ግን እነርሱ ኼደው ብቻዬን ስበላ የከዳኋቸው ይመስለኝና አይዋጥልኝም። ላስበውም አልፈልግም። እናም ሚስቲቱ "ትክክል አይደለህም፣ እንደውም ስመለስ ሽምግልና መቀመጥ አለብን!" ብላኛለች። እሺ፣ እኔ ምን ላድርግ? እርሷ በሌለችበት ቤት ምግብ መብላት በታማኝነት ጉድለት የሚያስከስስ የሚመስለኝን ነገር ምን ላድርግ? ደግሞ እኮ ላለፉት 7 አመታት እንደ ትንሽ ልጅ እንዲሁ ነው ሳስቸግራት የኖርሁት።
ትላንትም ወደ ነበረኝ መርሓ-ግብር ያቀናሁት ምሳዬን ሳልበላ ነበርና ጓደኛዬ ሰሎሞን አዝኖልኝ "መፍትሔ አግኝቼልሃለሁ" አለኝና ቀጥሎ "የኛ ቤቱን የምግብ policy ተከተሉ! እኛ ቤት ሁሉም ሰው በየራሱ ሳህን (Dish) ስለሚበላ በምግብ ጉዳይ ማንም ከማንም ጋር emotionally attached አይደለም! ስለዚህ Betty ስትመለስ ይህን ዘዴ ተከተሉ!" እኔም ከአፉ ቀበል አደረግሁና "ይህ የኢሊሙናቲ መንፈስ ነው!" ሥራህ ይፍረስ! አልኩት። በቃ Ema ስትመጣ በትክክል እበላለሁ። ዛሬም በምሽት ፕሮግራሜ አምሽቼ 4:35 ገብቼ ስለ ውሎዬ ምስጋናዬን ወደ ላይ ካሳረግሁ በኋላ "ስለ ምግብ" የሕሊና ጸሎት በማደርግበት ሰዓት ነው ይህችን የጻፍሁት። ነገ ወጥቼ ፏ ያለ ቁርስ እበላለሁ። እናንተ ምን አለባችሁ፣ ራታችሁን በልታችሁ የሰው ቤት ጉድ አንብቡ! የመጣ ይመጣል እንጂ ግን Solን አልሰማውም።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
ሞትም ሰልጥኗል!
---🔘----
ከበርናባስ በቀለ
የቅርብ ወዳጄ ናት። እጅግ ትጉህና የአቋም ሴት በመሆኗ ዙሪያ ባሉ ዘንድ ተከብራ የምትኖር እንስት እንደሆነች ስነግራችሁ እኔም ከተጽዕኖዋ ያልተረፍሁ መሆኔን ሳልሸሽጋችሁ ነው። ከምትኖርበት ከተማ ወደ ሌላኛው የክፍ'ላገር ከተማ በጉዳይ ተጉዛ ነበር (እርሱንም ከሳምንታት በፊት አሳውቃኛለች)፣ የዚያ ከተማ ተልዕኮዋን ጨርሳ ወደ እናት ከተማዋ ልትመለስ ሁለት ቀን ሲቀራት "ወንድምሽ አርፏልና ቶሎ ድረሺ" የሚል የስልክ ጥሪ ደረሳት። 😥
"ባርኒ ወንድሜን አጣሁት እኮ" ብላ text አደረገችልኝ። መደወል ፈራሁ! ስልኬን አስሬ እያነሳሁ መለስሁ። እንደምንም ግን ደወልኩላት። መቼ? እንዴት ምን ሆኖ? ብቻ ብዙ ጥያቄዎችን አከታትዬ ጠየቅኋት። "ባርኒ እንዴት የሚለውን እኔም አላውቅም" ይኸው ቀብረነው ቁጭ ብለናል። እኔም ማለት? ምንም ሳይታመም? ያለ ምንም አደጋ? ብዬ እንደ ደነገጥሁ ግራ መጋባቴን ነገርኋት።
እሺ፣ ቆይ ምን ይባላል? ስለ ብዙዎች ኃላፊነት በመውሰድ የሚታወቅ ጀግና ወንድም ሲሠራ ውሎ ባለበት ወደቀ ሞተ፣ የሚለውን እንዴት እንመን? ህመም ቀርቷል ማለት ነው? ሞትም ሰልጥኖ በሌላ version እየመጣ መሆኑ ነው? ወይስ እኛ ያልገባን ሌላ ነገር አለ? ወንድማችን ሳይማቅቅ ሳይሰቃይ ወደተሻለችው ከተማ ኼዷል፣ ወዳጄ (ሀረግዬ) ከጥቂት ቀናት በኋላ ደህና ትሆናለች አውቃለሁ፣ እኛም አለንላት። ግን ለምን? እና እንዴት የሚለው ጥያቄ አዕምሮዬን ሰቅዞ ይዞታል።
ቤተሰቦቼ ሞት ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ራሱን አዘምኖ ወደኛ ቀርቧልና አጠገባችሁ ያለውን ሰው ቼክ ማድረጋችሁን አትዘንጉ። በርግጥ ሞትን የምፈራ አይደለሁም፣ እርሱም ይህን ጠንቅቆ ያውቃል። ሞቼ አላየሁትም እንጂ የምወዳቸውን ስቀብራቸው ኖሬአለሁ። ተስፋዬም ከሞት ባሻገር ያለው ሕይወት ስለሆነ ወደዚያ ለመሻገር ከሚናፍቁ መካከል ነኝ። የኼደ አንዴ ኼዷልና እርሱ አይጨነቅም፣ ግን እዚህ ለቀረን ግዙፍና በዓይነቱ ልዩ የሆነ ጥያቄ ትቶልን ይኼዳል።
ስለ ወዳጄ እጸልያለሁ፣ እናንተም በጸሎታችሁ ታግዟታላችሁ። ግን አጠገባችሁ ላለ ሰው መልካምነት ልታሳዩ አስባችሁ እንደሆነ ቀን አትቅጠሩ። አዝናችሁበት እንደሆነ ለነገ አትበሉ። ትወዱትም እንደሆነ ፍቅራችሁን ለመግለጥ ዘይግታችሁ ጠሃይቱ አትግባ። ነገ አታገኙትምና ዛሬ ድረሱለት። ቀጣይ አመት አብሯችሁ ላይሆን ይችላልና ልባችሁ ከብዶበትም ከሆነ ዛሬውኑ ጊዜ ሰጥታችሁ ንገሩት። በንፁህ ፈገግታችሁ ቀን የምትጨምሩላቸው በአጠገባችሁ አይጠፉምና ግራ ቀኛችሁን ቼክ ማድረጋችሁን አትዘንጉ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
"የዓለም ዋንጫ"
----▣------
ከበርናባስ በቀለ
ከሚከተሉት መካከል ስለ ዓለም ዋንጫ ትክክል ያልሆነው የቱ ነው? በፍጥነትና በትክክል የመለሱ የመጀመሪያዎቹ 5 ሰዎች ይሸለሙ ዘንድ ወስነናል።
-----------
ሀ) ዓለም ዋንጫ አላት፣ በብርቱ ለሮጠላት ትሰጠዋለች።
ለ) ዓለም የዋንጫ ጨዋታ አዘጋጅታ ልጆቿን እያጫወተች ነው፤ ልጅ ጨዋታ ይወድ የለ?
ሐ) የእግር ኳስ ስፖርቱ ተወንጫፊ ከዋክብት በዓለሙ ገጽ ፊት የሚያበሩበት የትዕይንት መድረክ።
መ) አንተ ደግሞ፣ እስቲ አታወዛግበን።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
⚠️
------
ከበርናባስ በቀለ
ሩጫ በዝቶብኝ ጉልበቴ ዝሎ እና አዕምሮዬ ረጅም እረፍት የሚያስፈልገው አይነት አኳኻን ውስጥ ስሆን--- ከአካላዊ እረፍቱ በላይ ለምን በዚህ ልክ ተወጣጠርሁ? ጊዜዬን እየበሉት ያሉት ነገሮች ድንበር ዘለል፣ መርኾ ተኮርና እግዚአብሔር ለአጽናፈ ዓለሙ ካለው እቅድ ጋር የሚቆራኙ ናቸው? ለሚል ጥያቄ ትክክለኛ ምላሽ ማግኘቱ የበለጠ ያሳርፈኛል። ከዚያም ወደ physical & mental እረፍቴ አቀናለሁ።
ባለፉት ጊዜያት ብዙውን ጊዜዬን የበላብኝ አፍርሶ መገንባት እንደሆነ ስላስተዋልሁ፤ አሁን አዲስ ግንባታዎችን ሁሉ ማቆም አለብኝ። ባይሆን የተገነቡ ግኑኝነቶችንም ሆነ እንቅስቃሴዎቼን እየመረመርሁ በየቅድሚያቸው ማሰለፍ ይኖርብኛል። ትክክል የሆነ ነገር ሁሉ እውነተኛ ብሎም ዘላለማዊ አይደለምና እድሜዬን በtrial & error ⚠️ እንዳልጨርስ ከወዲሁ በተጠንቀቅ መቆም አለብኝ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
በምድሩ ላይ ርገጥ!
----▣---
ከበርናባስ በቀለ
ለተጨነቀች ነፍስ ማዳንህን ለምትሻ
ለ"አዳኝ ያለህ!" ባይዋ ከክፉው ንክሻ
በሰማያት ያለህ በምድሩ ላይ ርገጥ
ምህረትህን አውርድ ክንድህንም ግለጥ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 414
በቸርነትህ ብቻ የቆሙ ግን ማዳንህን የዘነጉ በየእለት ኑሯቸው ከእጅህ የሚበሉ ግን ስለ ፊትህ ግድ የሌላቸው ሰዎች መካከል ራሴን ሳገኝ አንተ እግዚአብሔር የመልካም ነገር ሁሉ መገኛ ምንጭ እንደሆንህ እመሰክር ዘንድ ክንድህ ይደግፈኝ። አለዚያ እኔም ተደርቤ ለጠላቶችህ ሳማህ ልውል ነውና በፊትህ ብርሃን ጨለማዬን ወግድ በልልኝ። ከበባውንም በትንልኝ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
