cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ትዝብተ-በርናባስ🔎✍️

ምድር እጅግ ሰፊ ናት፤ እኔ ወንድማችሁ በርናባስ ደግሞ ያሉኝ ሁለት ዐይኖች ብቻ! አባካችሁን ኑ...ና አጋጭተን (ዐይኖች አዋጥተን) እንይ!✍️ አሳብ አስተያየት ቢኖራችሁ፦ @barnica የግላችሁ ነው።

Більше
Рекламні дописи
1 505
Підписники
Немає даних24 години
-57 днів
-1530 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

ክርስትና እና የመደመሩ ባለ ራዕይ ብልጽግና! ---●----            ከበርናባስ በቀለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በስጋ ወደ ምድር የመጣው በሮም ዘመነ መንግሥት መኾኑ ይታወቃል። እርሱ የመጣው ታዲያ የእግዚአብሔርን መንግሥት ስርዓት (አስተዳደር) ሊመሠርት እንጂ ለዓለም መንግሥት ጥገናዊ ለውጥ ሊያደርግ አልነበረምና የመንግሥቱን አሠራር መርኾዎች በሮም መንግሥት ለማጋባትና ለማስረጽ ሲጥር አይታይም። እንኳን ከሮም መንግሥት መሲሓዊውን ንጉሥ (the Messianic king) ሲጠብቁ ከኖሩ ከይሁድነት እምነት መሪዎችና ማኅበረሰብ ጋር አብሮ ለመሥራት ሲፈራረም አላነበብንም። የሮም መንግሥት በጊዜው ኃያልና ገናና ከመኾኑ የተነሳ ከርሱ የሚበልጥ አንድ ሉዓላዊ መንግሥት እንዳለ ሲነገረው እንኳን ሊሰማ የመንግሥቱን ዜና አብሳሪዎች ሊያርድ ተያያዘ። የእግዚአብሔር መንግሥት ሕጋዊ ወኪል፣ ሰባኪና ንጉሥ ኾኖ የመጣው ጌታችን ኢየሱስ ለሮም መንግሥት የደህንነት ስጋት (threat) እንጂ ተፎካካሪ ፓርቲም ኾነ የፖለቲካው ሹመኛ ሊኾን አይችልም። መንግሥቱ ከዚህ ዓለም እንዳይደለች ሲሰብክ የመጣው ይህ ንጉሥ የሚያስተዋውቀው አስተዳደር በዓይነቱ ለየት ያለ ከመኾኑም አልፎ የሮምን መንግሥት ፍልስፍና አፈር ከድሜ የሚያበላ ነበር። ስለዚህ ሮም ይህን ሰው ሊሸልመውና የልማት አጋሩ አድርጎ ሊሾመው አይችልም። የወንጌላትን ትረካ በቅጡ ያነበበ ሰው ጌታችን ኢየሱስ እና የሮም መንግሥት ሆድና ጀርባ እንጂ እጅና ጓንት ኾነው ስለመኖራቸው ሊያስብ አይችልም። መዝሙረኛው በቅኔው ዳንኤልም በትንቢቱ የጻፉላት ሁሉን የምትገዛዋ የእግዚአብሔር መንግሥት የሮምንም አስተዳደር በክንዷ ፈጭታ በሁሉ ላይ ኃያል መኾኗ እንዲገለጥ የመጣው ኢየሱስ እንዴት ከሮም ባለ ሥልጣናት ጋር የስምምነት ውል ሊፈራረም ይችላል? አይኾንማ። "የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ" እያለ የመጣው መሲሕ በምን ሂሳብ "የመንግሥትነት ልኩ እኔ ነኝ" ከሚል የሮም መንግሥት ስርዓት ጋር ቡና ሊጠራራ ይችላል? ጽድቅንና ፍርድን የዙፋኑ መሠረት ያደረገው የልዑሉ እግዚአብሔር መልእክተኛ ዙፋኑን በግፍ ካጸናው የሮም መንግሥት ጋር እንዴት አሻሼ ገዳሜ ሊል ይችላል? በፍጹም ሊኾን አይችልም። እንኳን ጌታችን ኢየሱስና ሮም የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ቡድንና ሮም መንገዳቸው ለየቅል ነው። የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ዳዊታዊውን ንጉሥ (Davidic king) የሚጠብቁ የሩቅ አገር ተጓዦች ናቸው። በጊዜው በዙፋኑ ላይ የነበረው ንጉሥ ለእነርሱ የመጨረሻ (ultimate) ንጉሥ እንደኾነ የማያምኑና በሁሉ ላይ ሊያይል የሚመጣውን የአምላካቸውን መንግሥት እየተጠባበቁ በተስፋ የሚያድሩ ናቸውና (ግን ምን ያደርጋል! ከመንግሥቱ ጌታ ጋር ተላልፈዋል)። እንኳን የሮም መንግሥት የይሁድነት እምነት ተከታዮችና ኢየሱስ ተግባብተው አያውቁም። የይሁድነት ሃይማኖት በሮም መንግሥት ሕጋዊ ፈቃድ (ሽፋን) ያለው ተቋም ቢኾንም ግን በምኩራቦቻቸው አምላካቸውን እያመለኩ የሚመጣውን ንጉሥ ይጠባበቁ ነበር። ችግሩ እነርሱ የመሲሑን መንግሥት የሚጠብቁት ካሉበት ፖለቲካዊ ጫና ነጻ እንዲያወጣቸው እንጂ በኃጥአት እስራት ነጻ ስለ መውጣታቸው አይደለም። ክርስቶስ ስለ ሰው ልጆች ኃጥአት በአመጸኞች እጅ ወድቆ የመስቀል ሞት የተፈረደበት በሮም መንግሥትና በእነዚሁ የአይሁድ ሃይማኖት እንቅስቃሴ አራማጆች ጥምረት ነበር። ጌታችን መከራ የተቀበለው በጴንጤናዊው ጲላጦስ ዘመን የመኾኑን መቼስ አታጡትም። ብቻ ምን አለፋችሁ፦ የሮም መንግሥት ኢየሱስን ሲሰቅለው እንጂ ሲሸልመው አልተመለከትንም፤ ሲፈርድበትና ሲያሳድደው እንጂ ወንበሩን ሲለቅለት አላየንም። ከጌታችን ኢየሱስ ሞት በኋላ ይኸው መንግሥት ተከታዮቹን ማሳደዱን ተያያዘ። "የዚያ ሰው መንገድ መጥፋት አለበት" ብሎ ቀንና ለሊት ይሠራ እንደነበር የምናውቀው የሮም መንግሥት ለመሲሑ መንገድ ተከታዮችም የሚበጅ አልኾነም። የመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አማኞች ብዙ እንግልትና መከራ ይደርስባቸው እንደነበር የአዲስ ኪዳን ጽሑፎች በግልጥ ይነግሩናል። ሮምና የመሲሑ መንግሥት ተከታዮች (ደቀ መዛሙርቱ) እጅና ጓንት የኾኑበትን ዘመን አላየንም። እውነተኞቹ የክርስቶስ ተከታዮች እንኳን ከሮምና ከይሁድነት ከእናት ከአባቶቻቸው ተለይተው ለመሲሑ መንገድ ራሳቸውን የሰጡ ናቸውና ከሮም መንግሥት የጋራ የምክክር መድረክ የሚባል ነገር አይታሰብም። ሮም "አገራዊ አንድነት ለሁለንተናዊ ልማት" የሚባል ኮሚሽን አቋቁማለኹ ብሎ ቢያስብ ከደቀ መዛሙርቱ ለካቢኔነት ቢመለመል "የከፍታ ዘመን" ብሎ የሚያስብ አንድም ደቀ መዝሙር የለም። ሲጀመር ሮም ራሱ ሊገድላቸው እንጂ በመንግሥቱ ሊሾማቸው መቼ ይፈልግና! የይሁድነት አቀንቃኞችና የሮም መንግሥት መሲሑን ተባብረው እንደሰቀሉት ሁሉ ክርስቲያኖችንም ተባብረው ያሳድዱ ነበር። እውነተኛ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ለሮምም ለይሁድነትም ግራ ነው። በቃ አይገጥምም። የመሲሑ መንገድ ተከታይ ነውና መከራ፣ ስደትና ሞት የሕይወት ዘዬው ነው። የመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አማኞች ታዲያ መከራው በርትቶባቸው ነበር። መፈናፈን እንዳይችሉ ከወዲህ የሮም መንግሥት ከወዲያ ደግሞ የይሁድነት አቀንቃኞች ናላቸውን ሲያዞሩ እምነታቸው ጫና ውስጥ ሲወድቅ ከመልእክታት አንብበናል። ከአዲስ ኪዳን ጸሐፍት ጳውሎስ፣ ጴጥሮስ፣ ይሁዳ፣ የዕብራውያን መልእክት ጸሐፊና ሌሎችም ጸሐፍት በመከራ ውስጥ የሚያልፉ አማኞች በእምነታቸው እንዲጸኑ የሚመክሯቸው "እግዚአብሔር የሮምን መንግሥት አሳልፎ ይሰጣችኋል! ባለ ሥልጣናት ከእናንተ መካከል ይመለመላሉ" እያሉ አልነበረም። ይልቅ ያነበብነው "የመንገዱ ባሕርይ ነው! የሚሞተው ስጋችሁ በጌታ ቀን ሕይወትን ያገኛልና ሞትን አትፍሩ፤ ዘመኑ በጣም ትንሽ ነውና ጽኑ" ሲሉ ነው። አንዳንድ አማኞች መከራው እጅጉን ስለ ከበዳቸው ወደ ቀድሞ ሃይማኖታቸው (ይሁድነት) ሊመለሱ አስበው ነበር። የዕብራውያን ጸሐፊ "ማፈግፈግ"  (drifting away) ብሎ የሚጠራው ይህንኑን (ዕብ 2:1) ሲኾን ጴጥሮስ ደግሞ "ቢያሰፈልግ አሁን (ለጥቂት ጊዜ) በልዩ ልዩ መከራ አልፋችኋል... ግን በኋላ ክርስቶስ ሲገለጥ እጅግ ደስ ይላችኋል" (1ጴጥ 1:6-7) ይላል። የጌታ ወንድም ያዕቆብ ደግሞ እምነታችሁ ተፈትኖ ጽናትን (Perseverance) ያፈራላችሁና ምሉዓንና ፍጹማት ትኾናላችሁ (መከራው purify ያደርጋችኋል) እያለ የመከራቸውን ዓላማ redifine ያደርጋል (ያዕ 1:4)። ቆይ ግን፦ አማኞቹ ወደ ይሁድነት የሚመለሱት ለምን ይኾን? ይሁድነት በሮም የሚታወቅ (ጫናው ስር ያለ) ሃይማኖት ስለኾነ ነዋ! ሮም ይሁድነትን በጫናው ስር አድርጎ ለመንግሥቱ አሠራር በሚመች በልኩ ይዞታልና ለዙፋኑ ስጋት አይኾንበትም፤ ክርስቶስ ግን አካኼዱ ለያዥ ለገናዥ እንደማይመች ያስተዋለው ሮም ሰቅሎት ተገላግሏል። ይሁድነት ሮም ከሚያወጣው አዋጅ ስር ስለኾነ ስጋቱ አይደለም፤ ስለዚህ ሮም መከራ አያደርስበትም። የመጀመሪያዎቹ አማኞች ከመከራው ለማምለጥ በገዢው መንግሥት በአዋጅ ወደተመዘገበው (officially registered ወደኾነው) የይሁድነት ሃይማኖት መመለስ ነበረባቸው።
Показати все...
የመሲሑ ተከታዮች officially እንደሚሰደዱ እንጂ register እንደሚደረጉ ከመሪያቸው የተሰጣቸው ተስፋ የለምና ያላቸው አማራጭ በመከራው እስከ መጨረሻ መጽናት ነው። ሲያልፍም የተሰጣቸው ትልቅ ተስፋ የአምላካቸው የእግዚአብሔር መንግሥት ንጉሥ ዳግመኛ መመስ ነው። መከራቸው officially የሚያበቃው ያኔ ነውና እስከዚያው officially ይሰደዳሉ፣ ይወገዛሉ፣ ይሞታሉም። የአዲስ ኪዳን ጸሐፍት የሚነግሩን በጊዜው ዙፋን ለተቆናጠጡ ገዢዎች በጌታ (having Christ's mind) እንድንታዘዝ እንጂ ከአሠራሩ ጋር ጋብቻ እንድንፈጽም አይደለም። በእኛ ዘመን ጭራሽ የሮም መንግሥት ተሿሚዎች፣ የፍልስፍናው አሳላጮችና ካቢኔዎቹም እኛው ነን። የሮምን መንግሥትና ክርስቶስን ያፋቀርንና አብሮ ሠራተኞች ያደረግን በዓለም ታሪክ ምርጦቹ የእርቅ ኮሚሽን ጀግኖች እኮ ነን!😎 ስለ ዕውቅና ያለን አመለካከት ደግሞ እንዴት ሸውራራ (ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ) እንደኾነ ሳስብ ሃዘኔ ይበዛል። ክርስትና በመንግሥት ዕውቅና የነበረው ከ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ይልቅ በ1ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው። ከአሁኑ ብልጽግና ይልቅ በጥንቱ ደርግ ዘመን ነው። እንዴት ማለት ጥሩ አይደል? ሕጻኑ ኢየሱስ የተወለደ ጊዜ ሄሮድስ ጨቅላ ሕጻናትን ሁሉ ያስጨፈጨፈው ለምን ነበር? እርሱ የአይሁድ ንጉሥ እንደኾነ አውቆ አይደለምን? የሮም መንግሥት መሲሑን የሰቀለው ለምን ነበር? መንግሥቱና አሠራሩ ከእነርሱ የማይገጥም መኾኑን ስላወቀ አይደለምን? የኮሙኒስት እምነቱ (እግዚአብሔር የለሹ) የደርግ መንግሥት ቤተ ክርስቲያን የሚያሳድደው ለምን ነበር? "እግዚአብሔር አለ" የምትል ወኪል ድምፅ መሆኗን ስላወቀ አይደለምን? የዚህ ዓለም መንግሥት እውነተኛ የመሲሑ መንግሥት ተከታይ መኾንህን ሲረዳ ያሳድድሃል፤ ያኔ አንተ በእነርሱ ዘንድ ታውቀሃል። መታወቅ የሚባል እውነታ የሚረጋገጠው እግዚአብሔር እኛን በሚያውቀን መንገድ ሰዎች ሲያውቁን ነው። ቅዱሱ መጽሐፍ በነገረን ሕይወትና ማንነት ሰዎች እኛን ሲያውቁን ያኔ በርግጥ ታውቀናል፤ ለመታወቅ ብለን የምናደርገው ነገር አይኖርም እኮ፣ ግን የመሲሑ መንገድ ተከታዮች መኾናችን እንዲያው ይታወቃል። እኛ መታወቅን ከአደባባዮች ስብሰት፣ ከቤተ እምነቶች ግንባታ፣ ከመቃብር ስፍራዎች፣ ከሚዲያ ሽፋን፣ ከሥልጣን መደብ እኩልነት እናም በመሰል ርካሽ መወደዶች ተክተናል። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር እኛን በሚያውቀን መንገድ የታወቅን ይመስላችኋል? ከዚያም ተደራጅተን ስደትንና መከራን የሚከላከል ተቋም መሠረትን ክርስቶስን የሰቀለው የዓለም መንግሥት ለክርስቲያኖች ከለላ እንዲያደርግ ተማጽኖ አቀረብን። አቤቱ አምላኬ ሆይ፦ አንተ በምታውቀን በዚያ መንገድ ብቻ እንድንታወቅ የርካሽ ዕውቅና ቅጥሮቻችንን አፍርስልን።
Показати все...
ለምን እንጸናለን!? ----●---- ድነታችን የተመሠረተው በእግዚአብሔር ታማኝነት እንጂ በእኛ መጽናት አይደለም፤ ግን ደግሞ የያዘን እግዚአብሔር ለዘላለሙ ታማኝ ከኾነ እኛም እስከ መጨረሻ እንጸናለን። ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
ባለ ሱቁና ሚስኪኑ በርናባስ! ---●---          ከበርናባስ በቀለ     ሱቅ ቆሜአለሁ! ባለ ሱቁ ነዷል፤ ግሏል። ቆሽጡ አርሯል፤ ውስጥ ካለው ወዳጁ ጋር ያወራል። "በቃ እኔ ተስፋ ቆርጫለሁ! ከእንግዲህ ማንም በዚህ ጉዳይ እንዲያወራኝ አልፈልግም" ይላል። ትዳሩ ሊፈርስ ተቃርቦ መኾን አለበት ብዬ አሰብሁ። ከዚያም ላግዘው ከቻልሁ ብዬ፦ ወዳጄ አይዞኝ! ኧረ ይህን ቀን ታልፈዋለህ! ደግሞ የልብህ ጉዳት መጠን በፊትህ ያስታውቃል። ይህን ያህል ልብህን የጎዳው ግን ምንድነው? አልሁት። ቀበል አደረገና፦ "ይኼ አርሴናል ነዋ በሕይወቴ የሚጫወትብኝ።" እኔ፦ በል አኹን ያዘዝሁትን እቃ መዝንልኝ። ይቀልዳል እንዴ? 😥 "ቤትህ ለልማት ተፈልጓልና ነገ በጠዋት ይፈርሳል" የተባለ እኮ ነው የሚመስለው። ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
የጳውሎስ መልእክት ወደ በርናባስ ሰዎች!?😥 ----●------         ከበርናባስ በቀለ ዳዊት ይባላል፣ አመለ ሸጋ የኾነ ባጃጅ ሾፌር። ትንሽዬ ዕቃ (ለማንበቢያ የሚኾን ወንበር ነው! የበዓል ሸመታ ጋር አገናኙ ደግሞ!😉) ጭኖ ወደ ቤቴ እንዲያደርስልኝ በኮንትራት ውል ተገናኝተን ከCMC አካባቢ ጉዞ ጀምረናል። #እኔ፦ ባጃጅህን ጥሩ ይዘሃታል! እንተዋወቅ? ከደንበኝነት ያለፈ ቤተሰብ ልንኾን እንችል ይኾናል፤ ማን ያውቃል? #ዳዊት፦ "አንተም ተመችተኸኛል! ስምህ ማን ይባላል?" #እኔ፦ ስሜ በርናባስ ነው። #ዳዊት፦ "ይህን ስም መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነው የማውቀው አይደል? Yes! እንደውም አስታወስኩት፣ 'የጳውሎስ መልእክት ወደ በርናባስ ሰዎች' የሚል ሃሳብ በቆሮንቶስ ውስጥ አንብቤአለሁ" #እኔ፦ ወንድሜ! መጽሐፍ ቅዱስ የምታነብ በመኾንህ ደስ ብሎኛል፤ በርናባስ ከተማ አይደለም! ሰው ነው። አዎን በርግጥ ጳውሎስን ያቀና (መጋቢው) የነበረ ሰው ነው። በሐዋሪያትም ዘንድ ተወዳጅ ወንድም ነበር። የቆጵሮስ ሰው ነበርና ስሙ "በርናባስ" የተባለው በሐዋርያት ነው። #ዳዊት፦ "ይገርማል! መጽሐፍ ቅዱስ ካነበብሁ ቆየሁ ማለት ነው አይደል? ተምሬው እኮ ነበር። ተመርቄም ጭምር! እንደውም የድቁ'ና ትምህርት አጠናቅቄ የተመረቅሁበትን ፎቶ ላሳይህ!" (ብሎኝ በአንድ እጁ እየነዳ በሌላኛው እጁ ስልኩን ከኪሱ መዥለጥ አደረገና የምርቃት ምስሉን አሳየኝ!) #እኔ፦ ይገርማል! ታዲያ ለምንድነው በድቁ'ናው ያልገፋህበት? #ዳዊት፦ "ከድቁ'ናው ስንመረቅ በአንድ ደብር ውስጥ ዲያቆን ኾኔ ለመቀጠር 300,000 (ሦስት መቶ ሺህ ብር) መክፈል እንዳለብኝ ነገሩኝ! እኔም ተስፋ ቆረጥኩኝ። ይኸው ለእነርሱ ጉቦ ከምከፍል ብዬ እጄ ላይ በነበረው ገንዘብ ባጃጅ ገዝቼ ወደ ሥራ ገባኹ እልሃለሁ!" #እኔ፦ "አዝናለሁ በጣም!😥 አብረውህ የነበሩ ተማሪዎች እንዴት ኾኑ? አንተ እንዴት ተለየኻቸው?" #ዳዊት፦ "አቅም ያላቸው ከፈሉ፤ እንቢ ያሉ ደግሞ እንደ'ኔው በተለያዩ የጉልበት ሥራዎች ጭምር ተሰማሩ። በውስጡ ይህ አሻጥር ያለ መኾኑን ባውቅ አልማርም ነበር እኮ! እኔ ነፍሴን ወደ መንፈሳዊ ቦታ አስጠጋለሁ ብዬ ነበር የገባኹት ይኸው ወደ ዓለም ወርውረውኝ ያነበብሁት በርናባስ የሚባል መልካም ሰው ከተማ ሆነብኝ። ቢኾንም ግን ከባጃጅ ሥራዬ እዚያ ነበር የሚሻለኝ።" #እኔ፦ አይዞኝ ወንድሜ!😥 አንተ ጀግና ሰው ነህ። እንቢ ማለትህን በጣም አድንቄልሃለኹ። ከአመጻቸው ጋር ባለመተባበርህም ላመሰግንህ እወዳለኹ። ደግሞ ይኸው ባለ ባጃጅ ኾነሃል እኮ። ይህች ትንሽዬ የልፋትህ ጅማሮ ነገ ትልቅ እንደምትኾን አምናለኹ።  #ዳዊት፦ ዓለም ብትቆሽሽ ወደ እግዚአብሔር ቤት ተሸሽቶ ይዳናል፣ የእግዚአብሔር ቤት በዚህ መልኩ ሲጨቀይ የት ተኼዶ እረፍት ይደረጋል? ይኸው ሁሉም አስጠላኝ! #እኔ፦ በዚህ ጊዜ ዓለምንና የዓለማዊነትን ጥግ ለማየት የሚኬድበት ስፍራ ቤተ ክርስቲያን ኾናል፤ ይህን ዐውቃለሁ! ግን አንተና እኔም በግላችን ማድረግ ያለብን ነገር አለና በደንብ እንጨዋወታለን፤ በርታልኝ። ስላወቅሁህ ደስ ብሎኛል፣ እደውልልሃለሁ። ጥሩ ወንድም እኾንሃለሁ! ይኸው ሰፈራችን ደርሰናል፤ እዚህ ጫፍ ያዝልኝ። 😥 ይህን ልጥፍ ሙስና ጠያቂዎቹ ቢያነቡት ደስ ባለኝ፤ ለማንኛውም እናንት በድኾች ላብና ዕንባ የከበራችኹ (በየትኛውም ሃይማኖት ውስጥ ኹኑ) እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ነው!!!!!! 💪 ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
ሞት ምርጡ አገልጋዬ! ----●----       ከበርናባስ በቀለ ስለ ክርስቶስ ሞት ስናወራ ስለ ትንሳኤውም ድል እያወራን መኾኑ ግልጽ ነው፤ ስለ አዳም ኃጥአት የሞተው እርሱ ስለ ሕያውነቱ ደግሞ ከሙታን በኩር ኾኖ ተነስቷልና። በሞቱ ኃጥአትን ገድሎ በትንሣኤው ደግሞ ሕይወትን እውን አድርጓል። በክርስቶስ ኢየሱስ መስቀል ሥራ የሚያምን ኹሉ ሞትንና ኃይሉን አሸንፏል። ከእንዲህ ሞት ለእነርሱ አገልጋይ እንጂ ገዳይ አይደለም፤ እንደውም ዓለም አቋራጭ ትራንስፖርት ነው (ከዚህኛው ወደዚያኛው ዓለም)! ማለቴ፦ አያምጣውና አሁን ካሁበት ወደ ቦሌ ልኽድ ብል ራይድ እይዝ የለ? ልክ እንደዚያው የምድር ቆይታዬን ጨርሼ ወደ ጌታዬ ስኼድ ሞት መጓጓዣዬ ነው። ለምርጦቹ የስጋ ሞት ወደ ሌላኛው የሕይወት ምዕራፍ የሚሸጋገሩበት Exit door እንጂ መጥፊያቸው አይደለም። ሞት ተሸንፏላ! ኃይሉም በትንሳኤው መንፈስ ድል ተነሥቷላ! ከሰሞኑ ትንሳኤውን ስናስብ ታዲያ ሞትን በሞቱ የዘረረልን ጌታ ወደ ራሱ ሊወስደን በቅርቡ እንደሚመለስ እያሰብን ይሁን!! "በሦስተኛው ቀን እነሳለሁ!" እንዳለ የሞትን ኃይል አጥፍቶ የተነሳው ጌታችን "እኔ ባለሁበት እንድትኖሩ መጥቼ እወስዳችኋለሁ" ብሎ አይዋሸንምና!!!! ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
እግዚአብሔርን ትወደዋለህ? ----●------ ከበርናባስ በቀለ እግዚአብሔር ሰውን በጥልቅ ፍቅር መውደዱ በርሱ በተወደዳችኹ በእናንተው የታወቀ ነው፤ ግና ይህ ፍቅሩ የተረጋገጠው ለዓለሙ ባቀረበው ውድ ስጦታ መኾኑ አይዘነጋም። የእግዚአብሔር ፍቅር "Self giving" ነውና ልጁን ስለ'ኛ ኀጥአት ለመስቀል ስቃይ አሳልፎ ሊሰጠው ሁለት ጊዜ አላሰበም። ስለዚህም የእግዚአብሔር ፍቅር በሕያዋን ምድር የፍቅሮች ሁሉ መለኪያ ሊኾን ችሏል። "ከዚህ በላይ ለማንም ፍቅር የለውም" የተባለውን ልብ ይሏል። ሁላችንም ርሱን የምንከተለው ስለዚህ ፍቅሩ መኾኑን አልጠራጠርም። ይህ ፍቅር ታዲያ ምላሽ የሚፈልግ መኾኑም ግልጽ ነው። የፍቅሩ ምላሽ ስለ መስጠት ብዙዎች ብዙ ብለዋል፤ "ምላሽ ከኾነልህ ምስጋናዬን ዝማሬዬን" ብለንም ዘምረናል። ይኸው የወደደን አምላክ እግዚአብሔር ለፍቅሩ ምላሽ መስጠት የምንችልበትን መንገድ በግልጽ ነግሮናል። ምስጋና ጥሩ ነው፤ ግን ምስጋናችን የእግዜሩ ጽሕፈት ቤት ሥራ ማስኼጃ አይደለም። ርሱ ከምስጋናችን በፊት ዙፋኑ ጽኑ መንግሥቱም ከዘላለም ነውና። "እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ ውደድ" ተብለኻል፤ ርሱን መውደድህ የሚረጋገጠው ለባልንጀራህ ባለህ ፍቅር ነው። ይህን ስልህ ታዲያ ፍቅርን የምትጀምረው ከባልንጀራህ ነው እያልሁህ አይደለም፤ እግዚአብሔርን የመውደድህ ዋነኛ ማሳያ ለባልንጀራህ ያለህ ፍቅር መኾኑን ላመለክትህ አስቤ እንጂ። ስሊዚህ "አምላኬ ሆይ ለፍቅርህ ምላሽ አጣኹ! የምሰጥህ የለኝም" ልትል አትችልም። የፍቅሩ ምላሽ መንገድ በመጽሐፉ ቁጭ ብሎልሃልና። ርሱ ራሱን ስላንተ ሰጥቶህ የለ? አንተ ደግሞ ስለ ባልንጀራህ ራስህን ትሰጣለህ። ልጁም እስከ መስቀል ሞት ወዶህ የለ? አንተ ደግሞ ርሱ የሞተላቸውን ትወድ'ለታለህ። ይኸው ነው። ወዳጄ ይህንኑን በሚመለከት የሞተላቸውን ልንወድ'ለት በI Care Ministries የርኅራኄ አገልግሎት ክፍል የፊታችን እሁድ ሰው ከሌላቸው ሰዎች ጋር የትንሣኤውን በዓል መታሰቢያ ለማሳለፍ ታስቧልና አንተም ለፍቅሩ ምላሽህን ልትሰጥ አብረኸን መኾን ትችላለህ። ● ልብሶች ● የበዓል ፍጆቻ እቃዎች ● ገንዘብ ለዝግጅቱ የሚፈለጉ ግብዓቶች ናቸው። CBE: 1000426193737 የውስጥ መስመር፦ @metsafu ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
ማጤን አለብህ! -----●--- ከበርናባስ በቀለ እንዴት እንዳገኘኸው የማታውቀውን ነገር እንዴት አንተ ጋር እንደምታቆየው አታውቅምና "ሳላውቅ እጄ ገባ" እያልህ ስትፈነጥዝ ነገሩ workout ስለሚያደርግበት መንገድ ደግሞ ማጤን አለብህ። ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
ጮማ ጥያቄ! 🥩 ---●--- ከበርናባስ በቀለ #ሮዚ፦ "ባርኒ በነብይ መኖር ታምናለህ?" #እኔ፦ በነብይ ማን መኖር? #ሮዚ፦ "አይይ፤ በዚህ ዘመን ነብይ አለ ብለህ ታምናለህ?" #እኔ፦ እኮ ነብይ ማን? #ሮዚ፦ "እንዴ ባርኒ! ለዘመናችን እግዚአብሔር የቀባው ነብይ!" #እኔ፦ እንዴ... እኔስ ምን አጠፋሁ? እግዚአብሔር ለዘመናችን የቀባው ነብይ ማን? #ሮዚ፦ "እንዴ ባርኒ ነብይነት ማንነት ነው እንዴ?" #እኔ፦ እና ሮዚዬ ምንነት ነው? #ሮዚ፦ "ጥያቄዬን መመለስ አልፈለግህም ማለት ነው አይደል?"😥 #እኔ፦ ይኸው ከንግግሬ አንድ ምላሽ የሚያሻው ሃሳብ አግኝተሽ የለ? ለአሁን "ነብይ አለ የለም" ብዬ ጥቁርና ነጭ ምላሼን አልነገርሁሽም። ግን "ነብይነት ማንነት ነው እንዴ?" ብለሽ ያቀረብሽልኝን ጮማ ጥያቄ ደጋግመሽ አሰላስዪው። ከአሰላስሎትሽ ያገኘሽውን መረዳት በቀጣይ ጊዜ ታጋሪኛለሽ። ይህን ኮስታራ ጥያቄ በስልክ ከምናወራ ፊትለፊት ቢሆን እመርጣለሁ። በዘያ ላይ ከተያየን ቆየን አይደል? እስቲ ቢሮ ብቅ ነዪና እንመካከር! አሁን ስላልመለስሁ አትጨነቂ፤ ይደርሳል! ነብይነት ከገዛ አገሩ የት ይኼድና! ዋናው ነገር ጤና። ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
በስፒከሮቻችን አይደለም! ---●---- ከበርናባስ በቀለ የጥንት አማኞች "ጌታ ነው!" ማለት በማይቻልበት ዘመን የኢሱስን ጌትነት መስክረው (with their confession out of conviction) ነፍሳቸውን ሰጡ፤ የዚህ ዘመን አማኞች ደግሞ ለጌትነቱ በምናሳየው መገዛት (with our submission to his Lordship) ጌታ መሆኑን እንመሰክራለን። በስፒከሮቻችን አይደለም! ለአስተያየትዎ፦ @barnica Join ➘ & Share ➝      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊      ◊   @barnabasism  ◊
Показати все...
Оберіть інший тариф

На вашому тарифі доступна аналітика тільки для 5 каналів. Щоб отримати більше — оберіть інший тариф.