ትዝብተ-በርናባስ🔎✍️
前往频道在 Telegram
ምድር እጅግ ሰፊ ናት፤ እኔ ወንድማችሁ በርናባስ ደግሞ ያሉኝ ሁለት ዐይኖች ብቻ! አባካችሁን ኑ...ና አጋጭተን (ዐይኖች አዋጥተን) እንይ!✍️ አሳብ አስተያየት ቢኖራችሁ፦ @barnica የግላችሁ ነው።
显示更多1 424
订阅者
无数据24 小时
+57 天
-730 天
帖子存档
1 424
በቸርነትህ ብቻ የቆሙ ግን ማዳንህን የዘነጉ በየእለት ኑሯቸው ከእጅህ የሚበሉ ግን ስለ ፊትህ ግድ የሌላቸው ሰዎች መካከል ራሴን ሳገኝ አንተ እግዚአብሔር የመልካም ነገር ሁሉ መገኛ ምንጭ እንደሆንህ እመሰክር ዘንድ ክንድህ ይደግፈኝ። አለዚያ እኔም ተደርቤ ለጠላቶችህ ሳማህ ልውል ነውና በፊትህ ብርሃን ጨለማዬን ወግድ በልልኝ። ከበባውንም በትንልኝ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
የMercy መስመር!
----▣----
ከበርናባስ በቀለ
ጉዳይ ቢጤ ነበረኝና Mercy ጋር በጠዋት ስልክ መታሁ። ያቺ ሴትዮ "የደወሉላቸው ደንበኛ መስመር ስለተያዘ" ስትለኝ ብዙ ነገር አሰብሁ። ደግሞ "የደወሉላቸው ደንበኛ" ትላለች እንዴ? ደበኝነቷ እኮ ለእነርሱ ነው! ለእኔ እኮ ወዳጄ ናት። ለምን "የደወሉላቸው የቅርብ ወዳጅዎ አትለኝም?" ይህች ዓይን አውጣ ሴትዮ! እያልሁ አጉተመትማለሁ።
ብዙ ነገር ማሰቤን ቀጠልሁ። እሺ፣ መስመሯ የተያዘው ለምንድነው? መስመር ያዢዎቹ ጠላፊዎች ቢሆኑስ? የመስመር ላይ ሌቦች ቢሆኑስ? እንዲሁ በቀላሉ መስመርን የመሰለ ነገር ማስያዝ!? ሆሆሆ! እያልሁ መንገዱ ላይ ብቻዬን አወራለሁ። መስመሯ በትክክለኛ ያዥ (በሕጋዊ መስመረኞች) ተይዞ መሆን አለበት። የሆነ ሆኖ ግን ደጋግሜ ስሞክር ስልኳ ተነሳልኝ። እኔም Mercye ደህና ነሽ? ሴትየዋ "መስመርሽ ተይዟል" ስትለኝ እኮ ደንግጫለሁ አልኋት። እርሷ እየሳቀች "ለምን ባርኒ?" አለችኝ። በልቤ ሰው ተጨንቆ እርሷ ትስቃለች እንዴ? እያልሁ መስመርሽ በመያዙ ነዋ! አልኋት።
"ኦኦኦ ባርኒ፤ የስልኬ መስመር እኮ ነው።" አለችኝ። እኔም፦ ኡኡፍ! እንደርሱ በዪኛ ታዲያ አልኋት። እኔ የስልኳ መስመር ብቻ የተያዘ መሆኑን በምን አውቃለሁ። ሴትዮዋ እንደሆነች አታብራራ። "መስመር ስለተያዘ" ብቻ ነው የምትለው። ቀጥዬም ሌሎች መስመሮችሽ ደህና ናቸው? አልኋት። "አዎን! ሁሉም ጥሩ ነው!" አለችኝ። እሰይ! ብዬ ወደ ዋናው ጉዳዬ አመራሁ። እናተስ መስመራችሁ ደህና ነው? በመስመርማ ቀልድ የለም!!!
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ደብረብርሃን አየሯ ብርዳማ ነው። በመግቢያዋ ያለች "ጠባሲ" የተሰኘች ከተማ ስሟን ያገኘችው ብርዷ የሚጠበስ ስለመሆኑ እንደሆነ ነግረውናል። በርግጥ እኛ የመጣነው አየሩ ጥሩ በሆነበት ወቅት ስለመሆኑም አጫውተውናል።
ትራንስፖርት ውስጥ ያገኙን አዳዲስ ከሆናችሁ "አረቄ ግድ ነው!" ይሉናል። "እኛ ቅዝቃዜውን የቻልነው በአረቄው ነው!" እያሉ ምርጥ የደብረብርሃን አረቄ ያለበት ቤት ይጠቁሙናል። እኛ ደግሞ ቡናችንን በሰዓቱ እናግኝ እንጂ አያሳስባችሁ (የኛ ቤት አረቄ ቡና ነው!) እንላቸዋለን።
የሆነ ሆኖ ግን የልበ ቅኖች ከተማ ናት። ለመጣንበትም ተልዕኮ ቀና ምላሿን ሰጥታናለች። ከእንግዲህ ደብረብርሃን በሰሜን ሸዋ አንዷ የተልዕኳችን ማዕከል ሆና ልታገለግለን ቃል ገብታልናለች። አንኮበር፣ ደሴና ኮምቦልቻና መንዝ የቀጣይ ወር መዳረሻዎቻችን ናቸው። በእነዚህ አካባቢ ያላችሁ ወዳጆቼ ከዚህ ጉባዔ ወደ ኋላ ቀርታችሁ እንድታገኙኝ ይሁን!😊
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
እንዳልቀባጥር! 🤲
---▣----
ከበርናባስ በቀለ
ለጣዕመ ቢስ ልሳኔዬ በድንቅ አደራረግህ ለዛ ሰጥተኸው ሌሎችን የሚያንጽ ነገር ማውራት ከቻልሁ ዘንዳ አንደበቴ የምህረትህ ባለ ዕዳ ነውና በጎነትህን ብቻ ያውራ። ክብርህን በሚሻማ መልኩ ለአፍታ እንዳልቀባጥር መንፈስህ ለከናፍርቴ ዘብ ይቁምልኝ።
እንዳስለመድከኝ ሁሉ በዛሬውም ጉዞዬ (ከፊቴ ባለች ከተማ) ነገያቸውን ማየት ላቃታቸው ከነገህ (from your future) እየጨለፍሁ የፍጻሜያቸውን ተስፋ አመለክት ዘንድ ደካማውን ስብዕናዬን እንድትጠቀም ልመናዬን አቀርባለሁ። ምስክርህ ሆኜ በምቆምበት ሁሉ "እኔ አይደለሁም፣ እርሱ ነው!" እያልሁ አድንሆትህን አስተጋባ ዘንድ ቅዱሱ መንፈስህ እኔነቴን በአንተነትህ ይክደንልኝ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ሜሮን፦ "ሰላም! ላለፉት ሁለት ቀናት ለምን አልፖሰትህም? ፖስቶችህን የለመድን ቴሌግራማችንን ቼክ የምናደርግ አለን እኮ።"
እኔ፦ oww! በእውነቱ እንዲህ አስቤ አላውቅም። እኔ እንደው እንደ ጉዞ ማስታወሻዎች ከሆነኝና plus ደግሞ ዙሪያዬ ላሉ የአገልግሎቴ አጋሮች updates ልስጥ በሚል እንጂ በዚህ ልክ የሚጠቅም ነገር እንዳለው አላስብም።
የሆነ ሆኖ ግን ሜሪ (ዛሬ ያወቅሁሽ አንቺ ግን በጽሑፎቼ እንደምታቂኝ የነገርሽኝ) ወዳጄ ስለ አብሮነትሽ አመሰግናለሁ። ትላንት በI Care Family ስለነበረን የጋራ ጊዜ እየተዘገጃጀሁ ስለነበር ለሁለት ቀናት ከዚህ መንደር ጠፍቼ ነበር።
እርሷ፦ "እርሱ family እኛን አያካትምም?"
እኔ፦ በርግጥ! ቃለ እግዚአብሔርን መሠረት ያደረገ አስተምህሮና ተግባራዊ ሕይወት የናፈቃቸው፣ ሲያልፍም እውነተኛ ሰው የራባቸው የሚሰበሰቡበት ወርሃዊ መድረክ ነው።
እርሷ፦ እሺ ባርኒ፣ ለመቀላቀል መስፈርቱ ምንድነው?
እኔ፦ ጤናማውን አስተምህሮ መሠረት ያደረገ ኅብረት የሚናፍቅ ልብ፤ እውነተኛ ወዳጅነት (ቤተሰባዊነት) የሚፈልግ ጠንካራ መንፈስ።
ሜሪ፦ "በል እንግዲህ ለቀጣይ ወር ስብሰባችሁ አንደኛ ላይ ጻፈኝ።"
እኔ፦ ሜሪዬ አመሰግናለሁ። ለአስተባባሪዎቹ የግል መረጃሽን እሰጣቸዋለሁ። ደግሞ ከወዲሁ ቡና የምትጠጪ ስለመሆኑ እርግጠኛ ሁኚ። እኔ ቡና ከማይወድ ሰው ጋር ኅብረት የለኝምና። 😊
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
የ'ኛ ልጅ በርቺ!😊
---▣----
ከበርናባስ በቀለ
በቤተሰቤ (I Care family) ካሉ እንስቶች በትጋትዋ ትታወቃለች። የያዘችውን ነገር አድምታና አድቅቃ ነው የምትሠራው። አዕምሮዋ ብሩህ ነው። መማርና መመራመር ውስጧ ነው። መጠየቅ ስለምትወድ ብዙ ታስወራችኋለች። ላለፉት ጥቂት አመታት ስታጠናው የቆየችውን የምርምር (ወረቀት ሥራዋን) ዛሬ በዘርፉ ጠበብት ፊት አቅርባለች። "Nationwide Phenotypic and Genotypic Assessment of Glucose-6-Phosphate Dehydrogenase Deficiency in Relation to Malaria in Ethiopia" የምርምር ሥራዋ ርዕሰ ጉዳይ ነበር።
ታዲያ ልጅት ምርምሩን አጃዕብ በሚያሰኝ ብቃት ያቀረበች ሲሆን የሙያው ጠበብትም ይህ ሥራ እጅግ የላቀ ውጤት (Excellent) ይገባዋል ብለው ቆመው አጨብጭበዋል። ታዲያ ይህች ልጅ የኛ (የቤታችን) እንደሆነች ማሰቡ ራሱ ደስ አይልም!? ሲያልፍም ልጅት በምርምር ኢንስቲትዩቱ ተመራማሪ ሆና ከተሰየመች ቆይታለች። ከእንግዲህ Malariaን ምን ይውጣት ይሆን!?
ስለርሷ ደስ ብሎኛል፣ ቀጥሎም ደስ ይለኛል። እንደው ከእለቱ ግድንግድ ደስታዎቼ አንዱን ላጋራችሁ ብዬ ነው። ልጅት ማን ናት!? የምትሉና በቅርበት ልታውቋት የምትሹ (አ/አ ያላችሁ ዘመዶቼ) ስለ ስኬቷ አብረናት ቡና ልንጠጣ ማቀድ እንችላለን። ወንድሞች ግን አረጋጉት። የ'ኛ ልጅ በርቺ በርቺ! 😊
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
እኛም...
---▣---
ከበርናባስ በቀለ
አንተ በአምሳልህ ፈጠርኸን፣ ለክብርህም ሠራኸን፤ እኛም ክቡር ፍጥረትህን በአምሳላችን ፈጠርን፣ ለገዛ ክብራችንም ስንዋደቅ አደርን።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
እየተጓዝን ነው፤ "ወሬ አልሰማም አልምኮ ትቼ" የሚለው የዴቭ ዝማሬ በቲክቶኩ ተቀናብሮ እየሰማ ነው። ቀጥሎ Scroll አያደርግም ማለት ነው!? እሰይ! እኛም አረፍን።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ለናታን ቢኾን!
---▣---
ከበርናባስ በቀለ
ዝናቡ ከሰማይ
ቡቃያው ከምድር
ለናታን ቢኾን ለከድር
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ጓደኛችን አፈወርቅ ወዳለንበት ክፍል መጣ። እጅ ነሳ! "ኼይ! እንዴት ናችሁ ጓዶች!?" አፈወርቅ ጭር ሲል አይወድምና በትንሽ በትልቁ ነገር ጨዋታ ይፈበርክና ያስቀናል።
እኔ ከአፈርወርቅ የሰላምታ ኮታዬ ደርሶኛል። ቀጥሎ የጓደኛችን (ተወዳጁ ወንድም Dr. AB) ተራ ነው። ABም ተነሳ ኦውው! "እንዴት ነህ አፌ?" ይለዋል። አፈወርቅ ነገር ይወዳል ብዬአችሁ የለ!? ቀበል አደረገና፦ "ደህና ነኝ! ጻዲቅ ምን ይሆናል!?" ይለዋል።
AB ቀበል አደረገና! "ጻዲቅ ምን ይሆናል አልኸኝ? ሰባት ጊዜ ይወድቃል!"
እነሆ በክፍሉ ታላቅ ጸጥታ ሆነ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
የራስ ሲሆን ደግሞ!
----▣---
ከበርናባስ በቀለ
"ወደው አይስቁ" አሉ አበው! ለአንዳንድ ሁኔታዎች ምላሽ አጥታችሁለት "ሆ!.." ብላችሁ ስቃችሁ አታውቁም? በራሳችሁ ላይ ስቃችሁስ አታውቁም? ምን ኾኜ ነበር!? ብላችሁ በአግራሞት በራሳችሁ ላይ በትዝብት አንገታችሁን የነቀነቃችሁበት ቀን የለም? ለነገሩ ባለ ቅኔውም ብሏል..
"በአግራሞት ካልተነቀነቁ..
ለካስ ወደው አይስቁ፣
ይገርማል ለማለፍ ተገርሞ..
የራስ ሲሆን ደግሞ።"
በራስ ሲሆን ሳቁ ከመገረምም ያልፋል! ለማለት ነው። በራሴ በሳቅሁባቸው ጉዳዮች "ይገርማል" ብዬ ጉዞዬን አልቀጥልም፣ የሕይወቴን ፍልስፍና የሚሞግት ሌላ መነጽር (paradigm) አጥልቄ በራሴ ላይ የአሠራር ለውጥ አውጃለሁ እንጂ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ተግባቦት መላዬ!
---▣----
ከበርናባስ በቀለ
ትክክል መሆኔ ብቻውን በቂ አይደለም፣ ለትክክለኛ ሰው ስለመናገሬ ማረጋገጥ አለብኝ። ትክክለኛውን መልእክት ተቀባይ ማግኘቴ ብቻውን በቂ አይደለም፤ ነገርየውን የምናገርበት ጊዜ ትክክል ስለመሆኑ ማስተዋል አለብኝ። ጊዜውን መረዳቴ ብቻውን በቂ አይደለም፤ የማወራበት ቦታ ደግሞ ወሳኝ ነውና። ቦታውን ብቻ መረዳቴ ደግሞ አያድነኝም፣ መልእክቴን ስለማሳልጥበት መንገድ (platform) መጠንቀቅ አለብኝና፤ እርሱን ብቻ ማወቄ ብቻውን በቂ አይደለም፤ የምናገርበትን ሁኔታ (አኳኋን) መለየት አለብኝና። ይህን ሁሉ ማድረጌ ብቻውን በቂ አይደለም፣ የመልእክቴን ተቀባይ ግብረ-መልስ (reflection/response) ለመስማት በተጠንቀቅ መቆም አለብኝና።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ቴዲዬ ጉድህን ሰምተሃል? ሕዝቡ ዳስ አልጥል ብሎ ስለ አርሴናል ድል ግድንግድ ሰንጋ በሬዎችን እየጣለ ነው። የምር ግን አርሴናል እንደሚያሸንፍ ብታውቅ የAlbum release ጊዜውን adjust ታደርግ ነበር አይደል? እኔ ግን የለሁበትም።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ለካ ሁሉም ሰው ጀርባው ቢፋቅ አርሴናል ነው። በገሐድ በጠራራውም ሆነ በስውር የአርሴ ደጋፊ ጓዶቼ እንኳን ደስ አላችሁ! ደስታችሁን ሳይ ደስ ሊለኝ ነው። ኳስ ብዙ የማይገባኝ ቢሆንም ግን የፈንጠዚያ ስሜታችሁ (ረጅም የጠበቁትን የመታቀፉ ደስታ) ይገባኛል! እናንተ አርሴን ከምድወዱት በላይ እወዳችኋለሁ፣ ልክ እንደዛሬው ደስታቸሁ ስኬታችሁን ሳይ ስለ እናንተ ደስ ብሎኝ እፈነድቃለሁ።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
የሁሉ ልክና ገደብ!
---▣---
ከበርናባስ በቀለ
ፍጻሜ ያልተቀጠረለት ጅማሬ የለም። እግዚአብሔር የማይቀጣው አመጽና የማይከፍለው ብድራት የለም። "...ዝርዝሩን አናውቅም! እግዚአብሔር ግን ትዕቢተኞችን የሚያዋርድበት የራሱ መንገድ አለው!"
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
እየተዋጉልህ አያጸኑህ!
----▣----
ከበርናባስ በቀለ
ስጋ ለባሽ ልኩን አልፎ ትዕግሥትህን ሲፈታተን እያየኸው ዝም ብትል still አንተ በሁሉ ላይ ልዑል ነህ። አብሮ ሠራተኞችህ እንደሆኑ እየደሰኮሩ መጽሐፍህን ለገዛ ፈቃዳቸው ሲጠቀሙ እያየህ እጅ በእጅ ባትከፍል ከሚያደርጉት ነገር የተነሳ የሚበገር መንበር ስለሌለህ ነው። እንኳን ዙፋንህ ላይ የምርጦችህ (አንተ የጋረድኻቸው) ጫፍ ላይ ስልጣን የሌላቸው ድኩማን መሆናቸውን ተረድተው ቢገዙልህ ሕይወት ይሆንላቸው ነበር።
የታገስኻቸው ምህረትህን እንዲረዱ (ማዳንህንም እንዲያዩ) ጊዜ ሰጥተኻቸው እንጂ ስለ አንተነትህ ስለሚያስፈልጉህ አይደለም። እነርሱ ባይኖሩ አንተ አለህ፣ ባለፈውም ሆነ በሚመጣው ዘላለም በምሉዕነትህ ትኖራለህ። ለእግዚአብሔርነትህ አጋዥና ግብረ-አበር አትሻም። ሰዎች ተሰብስበው ወደ ዙፋን አላወጡህምና እየተዋጉልህ የሚያጸኑት መንግሥት የለህም፤ አንተ ከፍጥረት በፊት እግዚአብሔር ነህ!
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ወደ እለቱ ተልዕኮ እየተጓዝን የፍጥነት መንገድ ላይ ነን። ከፍጥነት መንገዱ እንደወጣን ከሦስት ሌሎች ሰዎች ጋር የቆመ ትራፊክ እጅ ይነሳል። ሾፌሩም "ቦታ የለኝም" የሚል ምልክት ሰጥቶት አለፈ። አገር አማን ነው ብለን ጉዟችንን ቀጠልን። ኋላ ግን ትራፊኩ ቀደመንና ጠበቀን! ፊት ለፊታችን ድቅን አለ።
ሾፌሩን "አንተ ቀልቃላ! እጅ እየነሳሁ ለምን አልፈኸኝ ኼድህ? ይህ ከየት ያመጣኸው ስርዓት አልበኝነት ነው?" ልጁም "ሰው ሸኝልኝ ልትለኝ እንደሆነ አስቤ ምልክት ሰጠሁህ! እንደምታየው መኪናው ሙሉ ነው። በሰጠሁህ ምልክት የተረዳኸኝ (የተግባባን) መስሎኝ ነው አልፌ የኼድኩትና ይቅርታ።"
ትራፊኩ "እኮ! ገብቶኛል። ሰው ልሸኝስ ቢሆን እኔ እጄን አንስቼ ሳናግርህ አለመቻልህን (መኪናህ ሙሉ መሆኑን) ቆመህ እንጂ አልፈኸኝ እየኼድህ ነው ልትነግረኝ የሚገባው?" ሾፌሩም፦ በተለዋወጥነው ምልክት ተግባብተን ብናልፍ ችግር አለው? ይህን ለማስረዳት መቆም ነበረብኝ? ትራፊኩ! "ይህችን ይወዳል! በል መንጃ ፈቃድህን አምጣ!"
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ዳኒ፦ "ባርኒ አርሴናል የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን በመሆኑ ምን ተሰማህ?"
እኔ፦ የትኛው አርሴናል?
ዳኒ፦ "ስንት አርሴናል ነው ያለው?"
እኔ፦ ሁሉም ሰው የራሱ አርሴናል አለው።
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ
----▣----
ከበርናባስ በቀለ
ራይድ ውስጥ ነኝ። ከሾፌሩ ጓሮ ሦስት ደስ የምንል ሰዎች አለን። አንዱን ወንድም ተዋወቅሁት፣ በቃ ነገር አያያዙ ተመቸኝ። እናም ወደድሁት። ሥራው ማስተማር እንደሆነ ነገረኝ። ምንድነው የምታስተምረው? ስለው "Theology" አለኝ። ኦውው! ታዲያ የኔ ሰው አይደለህ? አልሁት። ፈገግ አለ!
በመቀጠልም፦ እኔም እዚያው area እንደሆንሁ ሹክ አልሁትና የኃላፊነት ምመራውና የማስተምርበት በጣም ተወዳጅ ትምህርት ቤት እንዳለ ነገርሁት። ከዚያም በደምብ ከተግባባን እኛ ጋርም ታስተምራለሃ! አልሁት። "በደስታ ነዋ" ሲለኝ ግን Specializeሽንህ ምን area ነው? ማለቴ ምን ኮርስ ላይ ብንጠቀምህ በጣም effective ትሆናለህ? አልሁት።
ይኸው ወዳጄ ቀበል አደረገና "እኔ ሁሌም ዝግጁ ነኝ!...ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ" አለኝ። በልቤ ማለት ከዘፍጥረት አስከ ራዕይ ለማንበብ ነው? ቆፍጠን አልሁና (የመጣ ይምጣ ብዬ!) ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ሁሌ ዝግጁ ከሆንህማ መኼድ ነው ያለብህ! "ወዴት?" ሲለኝ.. ወደ አብርሃም እቅፍ አልሁት። አሁን ስልክ ይዟል! ከስልኩ ሲመለስ እኔኑን ወደዚያ ይሸኘኝ ይሆን? ካልተገናኘን መልካም ጊዜ!😥
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
1 424
የትርጉም አልባነት ወረርሽኝ
----▣---
ከበርናባስ በቀለ
"መኖር sense አይሰጥም። ሕይወት ሰልችቶኛል። Routine መደጋገም አንገሽግሾኛል። ከእንግዲህ ምንም የሚለወጥ ያለ አይመስለኝም። ስለዚህ ራሴን ጠልቼዋለሁ! መኖርማ በጣም ሸክኮኛል። ሞት silent በሆነ mood የሚመጣበትን መንገድ ብትጠቁመኝ ደስ ይለኛል። Please ማይንዱን ይቀይራል ብለህ አትምከረኝ! እኔ ጨርሻለሁ ወስኛለሁ!"
ከሰሞኑ "የሕይወት ትርጉም አልባነት" እያስጨነቃቸው እንደሆነ ከነገሩኝ ጥቂት ወጣቶች የሰማሁት አሳዛኝ እውነታ ነው። ወጣቶችን ሳማክር ካሉበት ሁኔታዎች ጫና ተነስተው ለዚህ ድምዳሜ ሲደርሱ መስማቱን ለምጄዋለሁ፤ የዚህ ሳምንቱ ግን በዓይነቱ ይለያል። ሰሞኑን የገጠሙኝ ኬዞች በመሠረታዊ አስፈልጎቶች የሚፈተኑ ወጣቶች ሕይወት አይደለም፣ ሁሉ ተሟልቶ (ካለሙት ብዙውን አሳክተው) ሕይወት ትርጉም አልሰጥ ያላቸውን ወጣቶች እንጂ።
ትንሽ ፍርሃት ቢጤ ከቦኝም ስለነበር አጠገቤ ያሉትን የምወዳቸውን ጥቂት ሰዎች ስለደህንነታቸው ቼክ ለማድረግ ሞክሬአለሁ። ይህ አገልግሎቴ ነውና እኔ ሥራዬን እቀጥላለሁ። ግን ስለነዚህ ወጣቶች ተጠያቂው ማነው? ራሳቸው? ቤተሰቦቻቸው? ቤተ እምነቶቻቸው? መንግሥት? ማኅበረሰቡ? ወይስ ማን? እኮ ማን? ልብ አድርጉ ያጡት የሚያስፈልጋቸውን አቅርቦት አይደለም፤ የመኖር አቅም (courage) እና ነገን አርቆ የማየት ተስፋ እንጂ።
በዚህ ተፈትኖ የሚያውቅ ሰው እዚህ መድረክ አለ ይሆን? በአሁን ወቅት በተመሳሳይ ሁኔታ እያለፈ ያለ ሰውስ አለ? ይህን ያልኳችሁ ነገርየውን አስፍተን ልናይና በመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ እንድንመካከር ነው። በዚህ አቅጣጫ ሰዎችን ማገዙ ላይ የተሰማራችሁስ አላችሁ? በየግላችን ከምንሮጥ እንዴት አብረን መሥራት እንዳለብን ብንመክር አይሻልም? (ይህን እዚህ ለመጻፍ ወጣቶቹን አስፈቅጃለሁ!)
ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
◊ @barnabasism ◊
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
