💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀
Відкрити в Telegram
💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።
Показати більше9 030
Підписники
-424 години
-337 днів
-13630 день
Архів дописів
✅ የሰለፊ ሴት ዋና መገለጫዋ በተውሂዷ ነው።
👌ከአላህ ውጭ ያለን ነገር አጠቃላይ አታመልክም
♦️ከአላህ ውጭ ላለ አካል ስለት አትገባም
♦️ከአላህ ውጭ ባለ ነገር አትምልም
♦️ካአላህ ውጭ ላለ አካል ድረሱልኝ ሀጃየን አውጡልኝ አትልም።
➡️ነብያችን ስለሏሁ አለይሂ ወሰለም ባሳዩት መልኩ ትክክለኛ ሱናዋን፣ አቂዳዋን፣ ተውሂዷን ይዛ እምትጓዝ ናት። ይህ የሰለፊ ሴት ዋና መገለጫዋ ባህሪዋ ነው።
قُل إنَّ صلاتى وَنُسُكى وَمَحياىَ وَمَماتى لِله رَبِّ الْعٰلمين
👌ስግደቴ ፣መገዛቴም ሕይወቴም ፣ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው ።በል።
➡️ይህም ማለት ስራዋን ባጠቃላይ ከሽርክ ትጠብቃለች ። ለአላህ ብላ ብቻ ትሰራለች። የሰዎችን እይታ አትፈልግም በማንኛውም ስራዋ ፣ሰዎች እንዳሞግሷት አትፈልግም።
በስራዋ በአላህ ውደታ የአላህን ፊት
እንድሁም ጀነትን ለማግኘት ከዛ ውጭ የምትፈልገው ምንም ዱኒያዊ ሀጃ የለም። ይህ ነው የሰለፊ ሴት ዋና አቋሟ።
👌ሰለፊ የሆነች ሴት ቢድዓ ከተባለበት ቦታ ትርቃለች ።
🔖ተዉሂድና የተውሂድ ባለቤቶችን የሱና ባለቤቶችን አጥበቃ መያዝ እንዳለባት ሁሉ፣
ሽርክና ከሽርክ ባለቤቶች ፣ የቢድዓ ባለቤትን ባጠቃላይ ትርቃለች። ሱናን አጥብቃ ትይዛለች።
👌ሰለፊ ሆና ሌሎች የሽርክ ባለቤትና የቢድዓ ባለቤቶች የሚፈጽሙትን ቢድዓዎች ሽርካ ሽርኮች አትፈጽምም።
👌ሰለፊ የሆነች ሴት ዐጅኒቢ ባለበት ቦታ ላይ እንደፈለገች አቶንም ።ቁጥብ ፣ ስትር፣ትላለች።
➡️ ምክንያቱም ሰለፊ ብሎ ማለት ትክክለኛ ቁርአንና ሀድስ ይዞ በሱና ላይና በተውሂድ ላይ ቀጥ ማለት ነውና።
➡️አሁን ባለንበት ዘመን ሰለፊነትን ይሞግታሉ። በኢባዳ ላይ ደካማ ሆነው ይታያሉ አላህ የከለከላቸውን ወንጀሎች በችልተኝነት ሲዳፈሩ ይታያሉ።
➡️ሰለፊ ሴት ማለት እኮ በኢባዳ ላይ ጠንካራ ነች ፣ የጧት የማታ ዚክሮችን ሰዓቷን ጠብቃ ትላለች። እህቶቿን በመልካም ስራ ላይ ታነሳሳለች ። ከመጥፎ ነገር እንድርቁ ትገስጻለች። መጥፎ ነገር አይታ ዝም አትልም ታወግዛለች። በማንኛውም ነገሯ ሀያዓና አደብ የተላበሰች ነች ።
👌ሰለፍይ ሴት ማለት እኮ እውነተኛ የሴት አለቃ ማለት እሷ ናት። አላህ ሆይ !እኔንም እህቶቼንም በሱና ላይ ቀጥ አድርገን ።
🔖ከዚህ ቀደም ኢብኑ ተይሚያ ቻናላይ የተሞነ ጨረች !Repost from ስለ ስልካችን
ከመተኛት በፊት የስልክህን ዳታ እንደምታጠፋው ሁሉ
ቀን የሰራሀውንም ወንጀል በኢስቲግፋር ማጥፋትን እንዳትረሳ🙌
©
የልብ ሰላም ርቆሃል?
የኢማን ጣዕም ናፍቆሃል? ✨
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ይላሉ፦ "ልቡ ያልተረጋጋለት፣ የኢማንን ጥፍጥና እና የቀጥተኛውን መንገድ ብርሃን ማግኘት የተሳነው ሰው፤ ተውባንና እስቲግፋርን ያብዛ።" 📿
Repost from DARU-TEWHID [ዳሩ-ተውሒድ]
አላህን በመፍራት ላይ አደራ እላቹሃለሁ !
ትላንት ዙል ቀዕደህ 23/1447 አለም ባንክ ሙስዓብ መስጅድ የቀረበ ምክር።
🎙በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር ሓፊዘሁላህ
~ t.me/Darutewhide
~አንዲት ሴት ልጅ የሸቀጡን
ዋጋ ለማስቀነስ ብላ ሻጩ ጋር
ልትቀላለድ ፣ ወሬ ልታስረዝምና
ልትሳሳቅ አይገባትም።
የሷ ሐያእ ከሸቀጡ ዋጋ ውድ
ነውና።
"جاهد نفسك وتذكّر:
من سبقَ في الدنيا بالخيرات
فهو السابق في الآخرة إلى الجنات!"
ስለ እውቀትና ተግባር፦
➖➖➖➖➖➖...✍️
"እውቀት ማለት መሸምደድ ሳይሆን አላህን መፍራት ነው። አላህን የማይፈራ ሰው የፈለገውን ያህል ቢቀራ 'አሊም' ሊባል አይችልም።"
የሁሉም ጓደኞች የሚያውቁት ግን የማይተገብሩት ሀዲስ!
~ትዋደዱ ዘንድ ስጦታ ተሠጣጡ ረሱል ﷺ
👉 በሉ ፍጠኑ ስጡኝ¡
🔖ኢብኑ ቀይም አላህ ይዘንላችዉና እንዲህ ብለዋል፦
አንድ ባሪያ የቂያማ ቀን እንደ ተራራ የሆኑ መልካም ስራዎችን ይዞ ይመጣል ነገር ግን ምላሱ ሁሉንም እንዳፈረሰበት ያገኛል።
الداء والدواءአምስቱ ደረጃዎች፡-
ኢማም ኢብኑልቀይም እንዲህ ይላሉ፥ “ሰዎች በሶላታቸው መሠረት በአምስት ደረጃ ይከፈላሉ፡-
አንደኛው፡- ራሱን በእጅጉ የበደለና ድንበር ያለፈ ሰው ነው:: የዚህ ዓይነቱ ግለሰብ የሶላቷን ቅድመ ሁኔታ -ዉዱእ ያጓደለ፣ ወቅቶቿን ያልጠበቀና ግዴታዎቿን በትክክል ያላሟላ ሰው ነው::
ሁለተኛው፡- የሶላትን ወቅቶቿን፣ ሕግጋቷንና ግልጽ የሆኑ ማእዘናቶቿን የሚያከብር ሲሆን ነገር ግን ነፍሱ ከሸይጧን የሚደርስባትን ጉትጎታ ከመታገል ይልቅ ከጉትጎታውና ዓለማዊ ሀሳቡ ጋር የሚነጉደው ነው::
ሦስተኛው፡- የሶላትን ህግጋቶች በትክክል የጠበቀ ሲሆን ነፍሱ የሚደርስባትን የሸይጧን ውትወታና ምድራዊ ሃሳብ ለመቋቋም ትግል ላይ ነው:: ይህ ሰው ሶላቱ እንዳይሰረቅበት ለመከላከል ትግል ላይ በመሆን፧ በሶላትና በትግል መካከል ሶላቱን ይፈጽማል።
አራተኛው፡- ሶላት ውስጥ በሚገባበት ጊዜ የሶላቷን ግዴታዎችና ህግጋቶች በትክክል ያሟላል:: ልቡ የሶላቷን ሐቆች ላለማጉደል በከፍተኛ ጥንቃቄ ይጠመዳል:: አንዳች ጉድለት እንዳይኖር የተቻለውን ያደርጋል:: ዋነኛ ሀሳቡ ሶላቱ እጅግ የተሟላችና የተዋበች እንድትሆን ማድረግ ነው:: ልቡ የተጠመደው በሶላቱ ጉዳይና በጌታው አምልኮ ላይ ብቻ ነው፡፡
አምስተኛው- ሶላት ውስጥ ሲገባ በተሟላ ሁኔታ ይሆናል:: ለየት የሚያደርገው ልቡን ሙሉ ለሙሉ ከጌታው ፊት ማስቀመጡ ነው:: በልቡ ወደ እርሱ ይመለከታል:: እንደሚከታተለው ይሰማዋል:: በጌታው ፍቅርና ልዕልና ሙሉ ልቦናው ተሞልቷል:: አላህን (ሱ.ወ.) የሚያየው ያህል ይሰማዋል:: የሸይጧን ውትወታዎችና ውልብታዎች በዚህ ልዩ የአምልኮት ስሜት ውስጥ ይጠፋሉ። በጌታውና በእርሱ መካከል ያለው ግርዶሽ ይነሳል:: የዚህ ዓይነቱ ሰው ሶላትና ፍፁም መዘናጋት ውስጥ ሆኖ የሚሰግድ ሰው ሶላት የሚበላለጡት የሰማይና የምድር ያህል ነው:: ምክንያቱም ይህ ሰው ሙሉ ሀሳቡ ጌታው ዘንድ የሆነና በሶላቱም ዐይኑ ያረፈ ሰው ነውና!
በዚሁ መነሻነት ስለ አምስቱ ሰዎች ሶላት እንዲህ ማለት ይቻላል)-
የመጀመሪያው ዓይነት ሰው ይቀጣል ሁለተኛው ይመረመራል ፤ ሶስተኛው ይቅር ይባላል፤ አራተኛው ይመነዳል፣ አምስተኛው ወደ ጌታው የተቃረበ ይሆናል::''
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
