uk
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Відкрити в Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Канал Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 380 підписників, посідаючи 5 573 місце в категорії Релігія і духовність та 2 194 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 380 підписників.

За останніми даними від 06 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 32, а за останні 24 години на -4, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 22.44%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.50% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 3 449 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 461 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 20.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 07 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.

15 380
Підписники
-424 години
-257 днів
+3230 день
Архів дописів
‹‹#መሐረነ_አብ (#የምሕላ_ጸሎት)፤ #በግእዝና_በአማርኛ፡፡ (በድምፅ ከፈለጋችሁ በቴሌግራም አድራሻችንነ (https://t.me/medihanaelem) በዩቲዩብ ገጻችን (https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w) ያገኛሉ፡፡) ፠ ‹‹ሳታቋርጡ ጸልዩ›› እንዳለ ቅዱ ጳውሎስ በ፩ኛ ተሰ. ፭፥፲፯ ጌታችንም ‹‹ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ›› ማቴ ፳፬፥፬ ብሎ አርአያ ሆኖ እንዳስተማረን፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ከምንገለገልባቸው ጸሎቶች አንዱና ዋነኛው ‹‹መሐረነ አብ›› ጸሎት ነው፡፡ ፠ መሐረነ አብ ጸሎት፡፡ ፠ ስያሜውን ያገኘው ጸሎቱ ሲጀምር ‹‹መሐረነ አብ፥ መሐረነ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ መሐሪ ተዘከረነ በሣህልከ፡፡›› (አብ ሆይ ማረን፥ ወልድ ሆይ ይቅር በለን፥ ይቅር ባይ መንፈስ ቅዱስ ሆይ በይቅርታህ አስበን) ብሎ ስለሚጀምር ነው፡፡ ፠ የመሐረነ አብ ጸሎትን ያዘጋጀው ከ40 መጻሕፍት በላይን የደረሰውና ካልዓይ ቅዱስ ያሬድ ፥ ካልዓይ ቄርሎስ የተባለው ቅዱሱ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ ነው፡፡ ሲያዘጋጀውም ከተለያዩ ቅዱሳት መጻሕፍትና እንደ ቅዱስ ያሬድ ካሉ ሊቃውንት ድርሰቶች ኀይለ ቃላት ያላቸውንና ለጸሎት ተስማሚ የሆኑ ቃላትን እንደ ንብ ቀስሞ ነው ያዘጋጀው፡፡ ፠ ቅዱሱ ያዘጋጀውም በመጽሐፈ ሰዐታት ድርሰቱ ላይ በስተመጨረሻ ከኪዳን በፊት እንዲደረስ አድርጎ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ከዓመት እስከ ዓመት በየዕለቱ ኪዳን በሚደርስባቸው ማንኛውም የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክንና ገዳማት ‹‹የመሐረነ አብ ጸሎት››ም ከኪዳን በፊት ይደርሳል፡፡ ፠ የመሐረነ አብ ጸሎት ከኪዳን በፊት ብቻ ሳይሆን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት በዋይዜማው የሚደርስ፣ ለግል ጸሎት፣ ረሃብ ጦርነት፥ አባር ቸነፈር፥ ተስሕቦና ወረረሽኝ በሽታ በመጣ ወቅት የሚደረስ ሲሆን ከእግዚኦታ ጋር አብሮ ስለሚባልም ‹‹የምሕላ ጸሎት›› በመባልም ይጠራል፡፡ ፠ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ በ14ኛው ክፍለ ዘመን ‹‹መሐረነ አብ››ን ከደረሰው በኋላ የተነሡ ቅዱሳንንና አባ ጊዮርጊስ ያላካተታቸውን በየጊዜው የተነሡ ሊቃውንት አካትተውታል፤ (ነገር ግን ሊቃውንቱ አሻሽለው ያዘጋጁት‹‹የመሐረነ አብ›› ጸሎት የሚደርሰው በታላላቅ ገዳማትና አድባራት ነው፡፡ ፠ የጸሎቱ አደራረስም በመሪና በተመሪ (በቀኝና በግራ) በተራ ስለሆነ በጋራ የሚጸለይና ዜማው የሚመስጥ፤ የቃሉ አሰዳደርም የሚያስደንቅ፤ የያዘው ኀይለ ቃል እንባን የሚያስነባ ነው፡፡ በተለይም በገዳም ያሉ አባቶች በጋራ(በማኅበር)ና በግል ጸሎት ዕለት ዕለት ያደርሱታል፡፡ ፠ በዓለማችን የተከሰተውን የ‹‹ኮሮና ቫይረስ›› የተስሕቦ በሽታ ከሃገራችንና ከዓለማችን እንዲያርቅልን የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ጕባኤ ለሃገራችን ለ1 ወር ያህል (ከመጋቢት 29 - ሚያዝያ 29) ድረስ ጸሎት እንዲደረግ ባስተላለፈው ጥሪ መሠረት፤ ቤተ ክርስቲያናችንም ዘወትር ማታ ከ3-4 ሰዐት የመሐረነ አብ ጸሎት እያደረሰች ትገኛለች፡፡ ፠እኛም በመደበኛ የሚጸለየውን ‹‹የመሐረነ አብ›› ጸሎት በግእዝና በአማርኛ አዘጋጅተንላችኋል፡፡ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

+++ ወሚጥ መዓተከ እምኔነ ሃሌ ሉያ፤ ንዒ ኀቤየ እንቲአየ ሠናይት ርግብየ መዓዛ አፉሃ ከመ ኮል ወኵሉ ነገራ በሰላም፡፡ Maaloo dheekkamsa kee nurraa deebisi haalleluyaa kan bareedde yaa gugee koo akka inkooyi fooliin afaan ishee bareedee dubbiin ishees nagaa kan ta'e gugee tiyya gara koo koottu +++ (አርእየነ እግዚኦ ሣህለከ ሃሌ ሉያ) መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል፣ ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ ዐቢይ Ergamaa nageenya keenya hangafa ergamootaa yaa qulqulluu Mikaa'el waayee keenyaf kadhadhu. Kadhannaa keenyas teessoo mootii guddichaa duratti ol nuuf baasi +++ ገብርኤል አብሠራ ለማርያም ወይቤላ ትወልዲ ወልደ ወይነግሥ ለቤተ ያዕቆብ ለዓለም ወአልቦ ማኅለቅት ለሰላሙ Qulqulluu Gabriel durboo Maariyaamiiti misraachoo himee , akkana jedheni ilma ni deessa bara baraaf gosa Yaa'iqoob irratti ni moo'a mootummaan isaas dhuma hin qabu. +++ ሰዓል ለነ ጊዮርጊስ ኀበ እግዚአብሔር ወጸሊ በእንቲአነ ሀረድዎ ወገመድዎ ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ሐመድ ወወሰድዎ ኀበ ሰብዓ ነገሥት ረገጸ ምድረ አንስአ ሙታነ አባ ጊዮርጊስ በሰላም አደወ መንግሥተ ክብር ወረሰ Yaa qulqulluu Giyoorgis gara Waaqayyootti nuuf kadhadhu waayee keenyaf kadhu.ni qalani ni murani foon isaa daakanii akka biyyootti bittinsani. Gara mootota torbaatamaatti isa fudhatani lafarra dhaabbate du'aas kaase. abbaan keenya Giyoorgis nagaadhan du'arraa gara jireenyatti ce'e. Dhaala mootummaa samiis dhaale. +++ ባርከኒ አባ እንሣእ በረከተከ በእንተ ሰላማ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሳሙኤል አባ ባርከኒ እንሣእ በረከተከ Yaa abbaa Saamu'eel eebba kee akkan fudhadhu na eebbisi, nageenya mana kiristaanaf jedhii na eebbisi eebba kee nan fudhadha +++ ብፁዕ አባ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘኤለ ገዳማተ በኀበ እግዚኡ ይንሳእ እሴተ ቦአ ገዳመ ደብረ ሊባኖስ በፍስሐ ወበሰላም Eebbifamoo abbaan keenya Taklahayimanot Gooftaa isaarraa gatii argachuuf gara gadaamii kan qajeele. Gara kawaala dabra libaanos seene. Gammachuu guddaa fi nagaadhan seene. +++ ማኅደረ ሰላምነ ቅድስት ደብተራ እሞሙ ለሰማዕት ወእኅቶሙ ለመላእክት ንዑ ንስግድ ኩልነ ኀበ ማርያም እምነ Maaloo dhiifama kee nutti agarsiisi haalleeluyaa Dunkaana oorit bultoo nageenya keenyaa haadha wareegamtootaa obboleettii ergamootaa koottaa nuti hunduu gara Durboo Maa diyamitti haa sagadnu +++ መስቀል ብርሃን ለኵሉ ዓለም፤ መሠረተ ቤተ ክርስቲያን፤ ወሀቤ ሰላም መድኀኔ ዓለም ለእለ ነአምን መድኅን፡፡ +++ (ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ) ሰላመ አብ ወሰላመ ወልድ ወሰላመ መንፈስ ቅዱስ የሃሉ ማዕከሌክሙ አኀው Addunyaa fi bara baraaf haalleeluyaa Nagaan abbaa nagaan ilmaan nagaan hafuura qulqulluu isin obboloota keenya fi obboleettiwwan keenya gidduu haa jiraatu. (3) +++ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ /፫ ጊዜ በንዑስ፥ ፫ ጊዜ በዐቢይ ዜማ በል/ Yaa Kiristoos nutti araarami +++ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ /፫ ጊዜ በዐቢይ ዜማ በል/ +++ ሰአሊ ለነ ማርያም ምሕረተ ወልድኪ የሐውጸነ ማርያም፤ ሰአሊ ለነ ማርያም ለለሰዓቱ ተግባረ እደዊሁ ለወልድኪ ኢንጥፋእ በከንቱ፤ ኵሎ መዓልተ ወኵሎ ሌሊተ፥ ብዙኃ ኀጢአተ ዘገበርነ በእንተ ማርያም እምከ ተማኅፀነ (መሐሪ ሥረይ ለነ አበሳነ)፡፡ +++ እግዚኦ ዕቀባ ለሃገሪትነ ኢትዮጵያ፡፡ +++እግዚኦ አዕርፍ ነፍሳተ አግብርቲከ ወአዕማቲከ ኵሎሙ ክርስቶሳውያን፡፡ +++ጸሎተ ሃይማኖት ወአቡነ ዘበሰማያት በል፨ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

#መሐረነ_አብ (#የምሕላ_ጸሎት)፤ #በግእዝና_በኦሮሚፋ Mahaaranna Aabi (Mihillaa) (Afaan Oromo)፡፡ (በድምፅ ከፈለጋችሁ በቴሌግራም አድራሻችንነ (https://t.me/medihanaelem) በዩቲዩብ ገጻችን (https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w) ያገኛሉ፡፡) +++ መሪና ተመሪ በቅብብልና በኅብረት፤ ሃሌ ሉያ ዘበእንቲአሃ ለቤተ ክርስቲያን፤ ተጸፋእከ በውስተ ዐውድ፤ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር፡፡ ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ፤ ወተዐገሠ ምራቀ ርኵሰ፥ እንዘ ዘልቦ ዘአበሰ፤ አምላክ ዲበ ዕፀ መስቀል ተሰቅለ፡፡ /ቅዱስ ያሬድ፥ ድጓ/ +++ መሪና ተመሪ በኅብረት፤ ሃሌ ሃሌ ሉያ አርእየነ እግዚኦ ሣህለከ፤ ረዳኤ ኩነነ ወኢትግድፈነ፤ መሐረነ፥ መሐከነ እግዚኦ እግዚኦ ተሣሃለነ፡፡ Maaloo dhiifama kee nutti agarsiisi haalle Haalle luyaa Yaa abbaa nutti araarami maaloo dhiifama kee nutti agarsiisi Maaloo qabeenya keef dhiifama godhii +++ መሐረነ አብ ………… ሃሌ ሉያ Yaa abbaa nutti ………… araarami Halleeluyaa +++ ተሣሃለነ ወልድ ሃሌ ሉያ Yaa ilma nutti ………… araarami Halleeluyaa +++ መንፈስ ቅዱስ መሐሪ ተዘከረነ በሣህልከ Yaa abbaa araaraa Aafuura Qulqulluu dhiifamaan nu yaadadhu(al 3) +++ ለከ ንፌኑ ስብሐተ ወለከ ነዓርግ አኰቴተ Galata siif ni ergina, galata siif ol baafna +++ መሐረነ መሐሪ ኀጢአተነ አስተሥሪ Abbaa dhiifamaa dhiifama nuuf godhu. Cubbuu keenyas nuuf haqi +++ ወአድኅነነ Nu fayyisis +++ ወተማኅፀን ነፍሰነ ወሥጋነ Foon keenya fi lubbuu keenya eegi +++ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር Ilma Waaqaa yaa Kiristoos +++ አምላክነ ………… ወመድኃኒነ +++ ኢየሱስ ክርስቶስ ተሣሃለነ Yaa Waaqa keenya Faayyisaa keenya Iyyasuus Kiristoos dhiifama nuuf godhi +++ በብዝኃ ምሕረትከ Baay'ina dhiifama keetin +++ ደምስስ አበሳነ Cubbu keenya nuuf haqi +++ ወፈኑ ሣህለከ ላእሌነ Dhiifama kee gara keenyatti nuuf ergi +++ እስመ እምኀቤከ Si biradhaatii hoo +++ ውእቱ ሣህል Dhiifamni +++ ሃሌ ሉያ መሐረነ አብ መሐሪ Haalleeluyaa yaa abbaa dhiifamaa nutti araarami +++ ወተሣሃለነ Dhiifamas nuuf godhi +++ ሀብ ሣህለከ መሐሪ Yaa abbaa dhiifamaa dhiifama kee ergi +++ ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት Yakka keenya darbe yaadattee nuu hin balleessin +++ በምሕረትከ Dhiifama keetin +++ እስመ መሐሪ አንተ Ati abbaa dhiifamaatitii +++ ወብዙኅ ሣህልከ ለኵሎሙ እለ ይጼውዑከ Kan si waamaniif dhiifamni kee baay'edha +++ ይጼውዑከ በጽድቅ Dhugaadhan kan si waamani +++ ሰማዒ ወትረ Yeroo hunda nii dhageessa +++ ከሃሊ ዘውስተ አድኅኖ Yeroo fayyisuu kee atti danda'aadha +++ ከሃሊ Danda'aa +++ ዘውስተ አድኅኖ +++ yeroo fayyisuu kee +++ ለአምላክነ እስመ ጽድቅ ቃሉ Waaqa keenyaf jechisaa dhugaadha +++ ንስአሎ ለአብ ………… ይፈኑ ለነ ሣህሎ Abbaa haa kadhannu araara nuuf haa ergu +++ እስመ አብ የአክል ለዘሰአሎ Abbaa kan kadhateef hunduu ni gahaatii +++ ሃሌ ሉያ Halleeluyaa +++ ስብሐት ሎቱ ይደሉ Isaaf galanni ni ta'aaf +++ ሃሌ ሉያ አኰቴት ሎቱ ይደሉ Halleeluyaa isaaf galanni ni ta'a +++ ሃሌ ሉያ Halleeluyaa +++ ለክርስቶስ ለእግዚአ ኩሉ Gooftaa hundaa Kiristoosiif +++ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ Haalleluyaa haalle haalleluya +++ ወይእዜኒ Ammaho +++ መኑ ተስፋየ Abdiin koo eenyu +++ አኮኑ ………… እግዚአብሔር Waaqa mitii +++ ውስተ እዴከ እግዚኦ አመኀፅን ነፍስየ Kinoo lubbuu koo harka keetti adaraa nan kenna +++ ኀበ አምላከ ምሕረት Gara Waaqa araaratti +++ አመኀፅን ነፍስየ Lubbuu koo adaraa nan kenna +++ ኀበ ንጉሠ ስብሐት Gara mootii galataatti +++ አመኀፅን ነፍስየ Lubbuu koo adaraa nan kenna +++ በእግዚእየ ወአምላኪየ Gooftaa kootin Waaqa kootin +++ አመኀፅን ነፍስየ Lubbuu koo nan eegsisa +++ እምኵሉ ምግባረ እኩይ አድኅና ለኀፍስየ Lubbuu koo hojii hammeenyaa hundarraa fayyisi (3) +++ ሀቡ Kennaa +++ ንስአሎ Haa kadhannu +++ ንስአሎ Haa kadhannu +++ ናስተምህሮ Garaa nuuf laafi haa jennuun +++ ለአምላክነ ጻድቅ እስመ ጽድቅ ቃሉ Abbaa dhugaa kan ta'e waaqni keenya jechisaa dhugaadhatii +++ ዘይክል ኵሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ Hundaa kan danda'u wanti inni dadhabu kan hin jirre +++ አምላከ ነዳያን ረዳኤ ምንዱባን Waaqa hiyyeessotaa kan rakkatan kan gargaartu +++ ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ Nuti siin kadhanneerra +++ ዘይክል ኩሎ ወአልቦ ዘይሰአኖ Hundaa kan danda'u wanti dadhabu kan hin jirre +++ አምላከ ነዳያን ናዛዜ ኅዙናን Hiyyeessotaa fi warra abdii kutaniif waaqa isaanii +++ ንሕነ ኀቤከ ተማኅፀነ Nuti siin kadhanneerra +++ ወበከመ ዐቀብከነ እምነግህ እስከ ሠርክ ዕቀበነ እግዚኦ እምሠርክ እስከ ነግህ Ganamaa jalqabdee hanga galgalaa akkuma nu eegde galgalaa hanga ganamaa nu eegi (yaroo 3) +++ተሣሃልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሉያ ስማዕ ጸሎተነ ወስዕለተነ ወስረይ ኵሎ ኀጢአተነ ስማዕ ጸሎተነ ወስዕለተነ ዘሰማዕኮ ጸሎቶ ወስዕለቶ ለዕዝራ ተወከፍ ምሕላነ ሰላመከ ኀበነ ወእማዕከሌነ ኢትርሐቅ፡፡ Maaloo qabeenya keef dhiifama godhi haalleluya, kadhannaa keenyaa fi watwaata keenya dhagahi. Cubbuu keenya hundaa nuuf haqi. Kadhannaa fi iyyata Izraa akkuma dhageesse, mihillaa keenya fudhu nageenya kee nuuf kenni gidduu keenyayis hin fagaatin.

ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር #በየቀኑ_እስከ_በዓለ_ትንሣኤ_የሚቀርብ #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል_፩ ፠ ‹‹እነሆ በትዕግስት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደፈጸመለት አይታችኋል፡፡›› ያዕ. ፭፥፲፩ ሰይጣንን በዘመናቸው ታግሰው ያሸነፉ ሰዎች ልቡናቸው አስተሳሰባቸው አጠቃላይ አኗኗራቸው ንጹሕና ቅዱስ ስለሚሆን ፍጹም ይቅር ባይና ቸሮች ርኅሩኆችና አዛኞች ናቸው፤ ሐዘኔታቸውም ለወዳጆቻቸውም ብቻ ሳይሆን ለጠላቶቻቸው ጭምር ነው (ቅዱስ ዳዊት /፩ኛ ሳሙ. ፳፬፥፲፰/ ና ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን /ሐዋ. ፯፥፰/ ልብ ይሏል) ቅዱሳን ከሰው ልጆች አልፈው ለአራዊት፣ ለአዕዋፍና ለእንስሳ እንዲሁም ለታላቁ ጠላት ለሰይጣን ሳይቀር የሚያዝኑ ናቸው፡፡ (ነቢዩ ሳሙኤል /፩ኛ ሳሙ. ፲፮፥፩/፣ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን /ገድለ ክርስቶስ ሰምራ/ ልብ ይሏል::) ፠ ቅዱሳን ሰዎች እንዲህ ዓይነቱን ጸጋ ሊያገኙ የሚችሉት የሰይጣንን ክፋት ለይተው ተረድተው ሰይጣንን በፍጹም ትዕግስትና ትሕትና ማሸነፍ በመቻላቸውና ከሰይጣን ባርነት ነጻ ወጥተው የእግዚአብሔርን መንፈስ ገንዘብ በማድረጋቸው ነው፡፡ ፠፠ በተቃራኒ ደግሞ በዓለም ላይ ለተፈጠሩትና እየተፈጠሩም ላሉት ችግሮች መንስኤያቸውና ምንጫቸው የሰይጣን ሰለባና ማደሪያ በሆኑ ሰዎች አማካይነት የሚከሠት ነው፡፡ (ቃዔልን /ዘፍ.፬፥፰፣ ሄሮድስን /ማቴ. ፪፥፲፮/፣ አምኖንን /፪ኛ ሳሙ. ፲፫፥፩/፣ ሰዶማውያንን /ዘፍ. ፲፱፥፩፣ ሮሜ. ፳፮፥፳፱፣ ፪ጴጥ. ፪፥፮/ …. ሌሎችንም …. ልብ ይሏል፡፡ ምክንያቱም፤ *ሰይጣን ተዘክሮተ እግዚአብሔርንና መንፈሳዊ ተግባራትን ካስተወ በኋላ በኃጢአት ላይ ኃጢአት እንዲጨምሩ እንጂ *ሰይጣን ኃጢአትን በቃኝ እንዳይሉ ስለሚያደርጋቸው ነው /ዘዳ. ፮፥፲፫/፡፡ *ሰይጣን ኃጢአትንም ተዉ ብሎ በሚመክራቸው ሰው ላይ በጠላትነት እንዲነሳሡ ያደርጋቸዋል፡፡ *ሰይጣን ቀና የሆኑ ነገሮችን ሁሉ ክፉ አስመስሎ ስለሚያሳያቸው ቅን አሳቢዎችንና ለመልካም ሥራ የተሰለፉትን እንዲጠሉ ያደርጋቸዋል፡፡ *ሰይጣን ቅን አስተሳሰብን መንፈሳዊ ሥራን ሰላምን ፍቅርን ርኅራኄን ከውስጣቸው አሟጦ አውጥቶ የራሱን መንፈስ ስለሚሞላባቸው ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢሠሩ ወንጀል የሠሩና ጥፋት ያጠፉ አይመስላቸውም፡፡ እውነተኛ ሕይወት እንደሚኖሩ ያስመስላቸዋልም፡፡ *ሰይጣን ዲያብሎስ የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማቸው ስለሚያደርጋቸው ለጥፋታቸው ገደብ የለውም፡፡ ፠ ##መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደው ሰው ሁሉ የሰይጣንን የክፋት ሥራ ተረድቶ ከሰይጣን እንዲሸሽና የእግዚአብሔርን ልጅነት አግኝቶ የዘለዓለም ሕይወት መንግሥተ ሰማያትን እንዲወርስ ለማድረግ ነው፡፡ /‹‹ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፡፡ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና፤ ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ፡፡ ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን አያደርግም ዘሩ በእርሱ ይኖራልና፤ ከእግዚአብሔር ተወልዷልና ኃጢአትን ሊያደርግ አይችልም፡፡ የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው፡፡›› ፩ዮሐ.፫፥፰/ /‹‹ክፉ ፍሬ የሚያፈራ መልካም ዛፍ የለምና እንዲሁም መልካም ፍሬ የሚያፈራ ክፉ ዛፍ የለም፡፡ ዛፍ ሁሉ ከፍሬው ይታወቃልና፤ …. መልካም ሰው ከመልካም ልቡ መልካሙን ያወጣል፡፡›› ሉቃስ ፮፥፵፫/ #ማንኛውም ሰው በሚሠራው ሥራ የማን ወገንና የማን ማደሪያ እንደሆነ ለመረዳትና ራሱንም ለመፈተሸ ይችላል፡፡ ፠ ##ጠላት ዲያብሎስ ንስሐ ገብተን መንግሥተ ሰማይትን እንዳንወርስ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በሥጋዊ ኑሯችንም ቢሆን በተገቢው ሰዐትና ጊዜ ተምረን ተገቢውን እውቀት ይዘን ሥራችንን በተገቢው ሰዐትና ጊዜ እንዳንሠራ በማድረግ፤ ሠርተንም እንዳንጠቀም ዕንቅፋት በመፍጠር (በስንፍናና በውሸት፤ በዝሙትና በስካር፤ በቃሚነትና በአጫሽነት፤ በጨፋሪነትና በዳንሰኛነት፤ በስርቆትና በአጭበርባሪነት፤ …. በተለያዩ የኃጢአት አሸክላዎች ተብትቦ ይይዘናል፤ እንዲህ ካደረገን በኋላም ሰይጣን በሚያመነጭልን አእምሯዊ ስሜትና ጭፍን አስተሳሰብ እየነዳን መልካም ሥራን ለሚሠሩ ለእውነተኛ ሰዎች እንቅፋት እንድንሆን በመሣሪያነት ይጠቀምብናል፡፡ /‹‹ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበር … አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን አዘገየን፡፡›› ፩ተሰ. ፪፥፲፰/ /አንተ (ኤልማስ የተባለ አስማተኛን/ ተንኮልንና ክፋትንም ሁሉ የሞላብህ የዲያብሎስ ልጅ የጽድቅም ሁሉ ጠላት የቀናውን የጌታን መንገድ ከማጣመም አታርፍምን?›› ሐዋ. ፲፫፥፮/ /እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ፡፡ እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለሌለ በእውነት አልቆመም፡፡ ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፡፡ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና፡፡›› ዮሐ. ፰፥፵፬/ #ከላይ ባየነው ዓይነት ሕይወት ሰይጣን በእጁ ያደረጋቸውን ሰዎች፤ **ለሕይወታቸው ጠቃሚ ምክርና ትምህርት በሚሰጣቸው ሰዐት ወዲያው እንዲዘነጉትና እንዳይቀበሉት ያደርጋል፡፡ /‹‹ወዲያው እንደሰሙ ሰይጣን መጥቶ በልባቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል፡፡›› ማር. ፬፥፲፭/ **ቢመከሩም ምክርን አይሰሙም አይቀበሉምም፤ /ይሁዳ ሕይወት የሚሆን የጌታን ትምህርት አልሰማ ብሎ ነው ጌታን አሳልፎ የሰጠው፡፡ ማቴ. ፳፮፥፵፱/ /አምኖንም የእኅቱን የትዕማርን ምክር አልሰማ ብሎ ነው አስነዋሪ ጥፋት በእኅቱ ላይ የፈጸመው፡፡ ፪ሳሙ. ፲፭፥፲፱/ /እንዲሁም ደግሞ ሳዖልም የነቢዩ ሳሙኤልን ምክር አልሰማ ብሎ ነው ከአማሌቃውያን ለማረከው ምርኮ በመሣሣት ክፉ መንፈስ ሊያድርበትና በጠላት እጅ ሊወድቅ የቻለው፡፡ ፩ሳሙ. ፲፭፥፲፱/ /#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #ክፍል_፪_ #ሰይጣን_ምንጊዜም_ቢሆን_እንደየሰው_ምኞትና_ፍላጎት፥ #እንደ_ጊዜውና_እንደ_ሰዐቱ፥ #እንደ_ዘመኑና_እንደ_ወቅቱ_ተጨባጭ_ሁኔታ_የማሳት_ጥበቡን_እየለዋወጠ_ይጠቀማል፡፡ .… ይቀጥላል ከነገ ወዲያ ይጠብቁን/ #በፌስቡክ_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ_፤ https://t.me/medihanaelem

መጋቢት 29፤ አምላክ ሰው የሆነባት ቀን፡፡ #እግዚአብሔር_ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበቡ_ይልቅ_ከድንግል_ማርያም_ሰው_ሆኖ_ዓለምን_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም፤ ፠ እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረበ
+2
መጋቢት 29፤ አምላክ ሰው የሆነባት ቀን፡፡ #እግዚአብሔር_ዓለምን_ከፈጠረበት_ጥበቡ_ይልቅ_ከድንግል_ማርያም_ሰው_ሆኖ_ዓለምን_ያዳነበት_ጥበቡ_ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም፤ ፠ እግዚአብሔር ዓለምን የፈጠረበት ጥበቡ፤ 7ቱ ዕለታትን፣ 20ው ዓለማትን፣ 22ት ሥነ ፍጥረታትን ካለመኖር ወደ መኖር፤ ከፈጠራቸውም ላይ አሻሽሎ አስገኘ ፠ ዓለምን ያዳነበት ጥበብ፤ ሰማይና ምድር የማይወስኑት፤ ከጽርሐ አርያም በላይ ጠፈሩ፥ ከበርባሮስ በታች መሠረቱ፥ ለአድማስና ለናጌብ ዳርቻቸው የኾነ አምላክ በእመቤታችን ማኅፀን ተወሰነ፡፡ ሁሉንም ማድረግ ሲችል በትህትና፣ በፍቅር ዝቅ ብሎ ዓለምን አዳነ፡፡ #አዳም_ሲፈጠር_ከተሰጠው_ክብር_ይልቅ_ሲድን_የተሰጠው_ክብር_ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም፤ ፠ሲፈጥረው የሚያስፈልገውን በ5 ዕለታት አዘጋጅቶ ነው፤ /መጽ. ማር ይስሐቅ/ ሲያድነው ግን የሚሆነውን በ5,500 ዘመን አዘጋጅቶ ነው፡፡ ፠ ሲፈጥረው በገነት እንዲኖር ነው፤ ሲያድነው ግን በመንግሥተ ሰማያት እንዲኖር ነው ፠ ሲፈጥረው ቅጠልና ፍራፍሬ እንዲበላ (ኋላ የአዳም ዘር በቃኤል ወገን ምክንያት ሥጋ የሚበላ ቢኾንም) ነው፤ ሲያድነው ግን ሥጋና ደሙን እንዲበላ ነው፡፡ ዘዚአኪ ልበ እንተ ተመሰለት ርግበ፤ ለተወክፎ ብሥራት ገብርኤል በከመ ነበበ፤ በኃሤት ዘአስተርከበ፤ በሰጊድ ሰላም፡፡ /ሰዐታት፥ ለኖኅ ሐመሩ/ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem ፠ በዩቲዩብ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ Https://m.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w

ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #መቅድም ለፌስቡክና ቴለግራም አባላቶቻችን በሙሉ፤ ከዚህ በፊት በተከታታይ ክ
ሰይጣን በአባ ጳውሊ ተገዝቶ ሳለ ያወጣው ምሥጢር #ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ (ተዋስኦተ ጳውሊ ምስለ ሰይጣን)፤ #መቅድም ለፌስቡክና ቴለግራም አባላቶቻችን በሙሉ፤ ከዚህ በፊት በተከታታይ ክፍል ‹‹#ተዋስኦተ_ጳውሊ_ምስለ_ሰይጣን_ /#ከሰይጣን_ጋር_የተደረገ_ቃለ_ምልልስ_››/) በሚል ርዕስ ያቀረብንላችሁን ትምህርት፤ ደግመን እንድናቀርብላችሁ ከፌስቡክና ቴሌግራም አባላቶቻችን በተደጋጋሚ ስለተጠየቅን ከዛሬ ጀምሮ #በየቀኑ_እስከ_በዓለ_ትንሣኤ_ድረስ የምናቀርብ መሆኑን እናበስራለን፡፡ ሰላም ለአባ ጳውሊ፤ ዘንጉሥ ወዓሊ፤ ገዳማዊ ዘበአማን ኅሩይ፤ ርዕሶሙ ለፈላስያን እለ በገዳም፡፡ ትርጉም፤ በበረሃ ላሉ ባሕታውያን(መናንያን) አለቃቸው፤ በእውነት የተመረጠ ገዳማዊ፤ የንጉሥ ሎሌ ለኾነ ለአባ ጳውሊ ሰላምታ ይገባል፡፡ ምንጫችን፤ * ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከግእዝ ወደ አማርኛ ያሳተመው መጽሐፍ፣ * ዜና አበው ግእዝ በግእዝ መጽሐፍ * ፍኖተ ቅዱሳን /FINOTE KIDUSANZETWAHIDO እና ዋልድባ ዋሊ የቴሌግራም ገጽ፡፡ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ የቀጨኔ ደ/ሰላም መድኀኔዓለምና ደ/ትጉሃን ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ/ት/ቤት ሰሌዳ መጽሔት፡፡ #_በቴሌግራም_ሊያገኙን_ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem #በክፍል_፩#የምናያቸው_፤ ፠ በትዕግስት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ሐዘኔታቸውም ለወዳጆቻቸውም ብቻ ሳይሆን ለጠላቶቻቸው ጭምር እንሆነ፤ ለታላቁ ጠላት ለሰይጣን ሳይቀር የሚያዝኑ መሆናቸውን:: ፠ በዓለም ላይ ለተፈጠሩትና እየተፈጠሩም ላሉት ችግሮች መንስኤያቸውና ምንጫቸው ምንድን ነው? ፠ መድኀኔ ዓለም ከሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም የተወለደው ሰውን ሁሉ ምን ለማድረግ ነው? ፠ ጠላት ዲያብሎስ በነፍስና በሥጋዊ ኑሯችን ምን ሊያደርገን ይፈልጋል? /ይቀጥላል ነገ ይጠብቁን/

እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ፤ ያድኅነነ እመዓቱ ይሠውረነ፤ በምሕረቱ በእንተ ማርያም ወላዲቱ፨ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ መላእክት መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ ነቢያት መሐረነ ክርስቶስ፤ በ
+1
እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ፤ ያድኅነነ እመዓቱ ይሠውረነ፤ በምሕረቱ በእንተ ማርያም ወላዲቱ፨ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ መላእክት መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ ነቢያት መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ ሐዋርያት መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ ጻድቃን መሐረነ ክርስቶስ፤ በእንተ ሰማዕታት መሐረነ ክርስቶስ፨ ፎቶው፤ በደብራችን አጥቢያ ከሚገኙ ሰፈሮች መካከል አንዱና ዋና በሆነው በቀጨኔ በየመንደሩ የእግዚኦታ ምሕላ ጸሎትና ትምህርት ከተጀምረ እነሆ ፯ት ቀን ሞላው፨ ፎቶው ላይ የምታዩት ቀጨኔ ፬ት መንታ ላይ እሑድ በ፳፯ የተካሄደ መርሐ ግብር ነው።

እንኳን ለአምላካችንና ለመድኀኒታችን፤ ለፈጣሪያችንና ለአዳኛችን መድኀኔ ዓለም ጥንተ ስቅለት #መጋቢት_፳፯ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ *ከዋይዜማ እስከ ማኅሌት፤ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት
+6
እንኳን ለአምላካችንና ለመድኀኒታችን፤ ለፈጣሪያችንና ለአዳኛችን መድኀኔ ዓለም ጥንተ ስቅለት #መጋቢት_፳፯ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፥ አደረሰን፡፡ *ከዋይዜማ እስከ ማኅሌት፤ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የሚቆመውን ሥርዐተ ማኅሌት በግእዝና በአማርኛ ትርጕሙን ጭምር አቅርበንላችኋል፡፡ (በታላቁ ደብር በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ብቻ የሚቆሙትንም ቀለማት ዘቀጨኔ ደብረ ሰላም ብለን አካተን አስቀምጠናቸዋል፡፡ #ስለ እናትህ ስለ ድንግል ማርያም ብለህ ምሬሃለሁ ይቅር ብዬሃለሁ በለኝ፤ ከአንተ በቀር ቸር ይቅር ባይ የለምና፡፡ በለኒ መሐርኩከ በእንተ ማርያም፤ እስመ አልቦ ዘእንበሌከ ዘይሜሕር ቃል መድኀኔዓለም፡፡ #በእንተ ማርያም ወላዲትከ፤ ወበእንተ ዮሐንስ መጥምቅከ፤ እግዚኦ ኢታስተሃፍረነ በቅድሜከ መድኔዓለም፡፡ (ስለ ወለደችህ እናትህ ማርያም፤ ስለ አጠመቅህ ዮሐንስ ብለህ አቤቱ አምላካችን ሆይ፤ በፊትህ በቆምን ጊዜ እንዳታሳፍረን፡፡ #ወጸሐፈ ጲላጦስ መጽሐፈ፤ ወይብል መጽሐፉ ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ፡፡ (መስፍኑ ጲላጦስ በመጽሐፉ ‹‹ኢ.ና.ን.አ›› (ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሠ አይሁድ ብሎ) ጻፈ፡፡ /ዛሬም በአንገታችን መስቀል ላይ መቀረጽ ያለበት ‹‹ኢ.ና.ን.አ.›› የሚል እንጂ የራሳችንና የሌሎች ስም መሆን የለበትም!!! #አውረድዎ እምዕፅ፤ ወአምጽኡ አፈዋተ ከርቤ ሕውሰ፡፡ ዝናብን የምትሰጥ መድኀኔ ዓለም ሆይ ተጠማሁ ባልክ ጊዜ፤ ከርቤና ሐሞት የተቀላቀለበትን አጠጡህ!! ከእንጨት መስቀል ላይም አወረዱህ። ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ኒቆዲሞስ፤ #ሰባተኛው_ሳምንትና #የዕለቱ_ምንባባትና_መዝሙራት፤ ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል፤ በዚህ ሳምንትም ይህ ይታሰብበታል፡፡ ‹‹ኒቆዲሞስ››፤ * አይሁዳዊ ሲሆን ከፈሪሳውያን ወገን የነበረ ነው * በኢየሩሳሌም በሀብት ቢሉ በዕውቀት እንዲሁም በሥልጣን የአይሁድ አለቃ ነበር፡፡ * ማታ ማታ ጌታችን ዘንድ እየተገኘ ይማር ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እንዲህ አስቀምጦልናል፦ ፨ ‹‹ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ ‹‹መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከእሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህ ተዓምራቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን›› አለው፡፡ ⊚ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ፨ ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው። ⊚ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። #ከሥጋ_የተወለደ_ሥጋ_ነው፥ #ከመንፈስም_የተወለደ_መንፈስ_ነው።›› /ዮሐ. ፫፥ ዘ፩-፲፭/ ፨ለምን በሌሊት ይመጣ ነበር? ⊚ አይሁድ ‹‹ማንም ከእኛ ወገን የሆነ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ከሆነ ሀብት ንብረቱ ይወሰድ፣ በቤተመቅደስ አይግባ፣ መሥዋዕት አይሠዋ›› ብለው ነበርና አይሁድን ፈርቶ፥ ሀብት ንብረቱን ወዶ፥ እንዳይታወቅበት በሌሊት ይመጣ ነበር፡፡ ⊚ በሌላ በኩል ደግሞ የቀን ልብ ባካና ነው፤ ዓይን ብዙ ያያል፥ ሐሳብ ይበታተናል፡፡ በተሰበሰበ ልብ ለመማር፤ በተጨማሪ ‹‹ሊቅ ነኝ›› እያለ ‹‹እስከ ዛሬ ትምህርት አልጨረሰም›› እንዳይሉት በሌሊት ይመጣ ነበር፤ ይህንንም የቀድሞ ሊቃውንት "ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ፤ አኮኑ አጽባሕት እምነ አጽባሕት የአቢ።" በሚል ጕባኤ ቃና ቅኔ አራቅቀውታል፤ ይህ ቅኔም ለተማሪዎች የቅኔ ሀሁ ነው። ⊚ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳን ለመማር የመጣውን እራሱ እየሄደ ያስተምር ነበርና ኒቆዲሞስ ምንም በሌሊት ቢመጣም ማወቅን ፈልጎ ነውና ስለዳግም መወለድ (ስለጥምቀት) በእግዚአብሔር ልጅ ስለማመንና ስለ ጽድቅ ስራ በዝርዝር አስተምሮታል፡፡ ⊚ ኒቆዲሞስ ከአርማትያው ዮሴፍ ጋር በመጨረሻው ቀን በዕለተ ዐርብ ጌታችንን በስቅለቱ ጊዜ፤ ከመስቀል ላይ ሥጋውን ለማውረድና ገንዞ ለመቅበር ቀድሞ ተገኝቷል፡፡ /ዮሐ. ፲፱፥፴፰/ ከኒቆዲሞስ ሕይወት የምንማረው፡- ፩. #ትሕትና፦ ኒቆዲሞስ በትምህርት፣ በሹመት፣ በባለጸግነት የአይሁድ አለቃ ሲሆን፤ አለቅነቱ ግን ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ እርሱ ተገኝቶ ለመማር አልከለከለውም፡፡ (የቅኔውን ትርጕም ከመምህራን ይጠይቁ) ፪. #አለማመካኘት፦ ከመጀመሪያ ሰዎች ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ ሰዎች በምክንያተኝነት በአመፅ መንገድ ይጓዛሉ፡፡ ኒቆዲሞስም ወደ ጌታ በመቅረቡ የጸሐፍት ፈሪሳውያን አድማና ግርግር ታላቅ እንቅፋትና ምክንያት መሆን እንደሚችል ያውቃል፡፡ ነገር ግን ይህ ምክንያት በእግዚአብሔር ፊት እንደማያዋጣ አውቆ የሚያዋጣውን አደረገ፡፡ ፫. #ጥበብ፦ በክርስትና ጉዞ ውስጥ ጥበብ የመጀመሪያ ቦታ ትይዛለች፡፡ ኒቆዲሞስም ጕዞውን በጥበብ አደረገ፡፡ በሌሊት ያደረገበት ምክንያት፡- ራሱ መምህር ሆኖ ሌላ ትምህርት አስፈለገው ብለው ሌሎች እንዳይሰናከሉበት፣ የመዓልት ልቦና ስለሚሰበሰብ በቂ ዕውቀት ለማግኘት፣ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት በመዓልትም በሌሊትም ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዳለብን ለማጠየቅ፣ ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ያሉ ነፍሳት በሲዖል ይገኛሉ ሲል፣ በመዓልትም በሌሊትም ብትፈልጉ ትገኛለች ሲል ነው፡፡ በእውነት ግሩም ጥበብ! ፬. የተነገረውን አምኖ በመቀበሉ፡- ጸሐፍት ፈሪሳውያን ብዙ ምክንያቶች እየደረደሩ የጌታን አምላክነት አምኖ መቀበል ሲያቅታቸው እርሱ ግን ጌትነቱን ለመቀበል ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ፭. ለእውነት መመስከር፡- እነርሱ ሲክዱ ጌታ ላይም ትርፍ ቃል ሲናገሩ፤ በድፍረት መክሰሳቸውን እየነገራቸው የጌታችን አምላክነቱን በግልጽ ይመሰክር ነበር፡፡ ፮. ጽንዓት፡- ብዙዎች በመከራ ጊዜ ላይለዩት ቃል ቢገቡም መጨረሻ ላይ ያኔ በመከራ ሰዓት ከመስቀሉ ሥር ሊገኙ የቻሉ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ኒቆዲሞስም በዚች ሰዓት ያንን መከራ ታግሶ በጽነዓት ከዮሴፍ ጋር የጌታን ሥጋ ከመስቀል አውርደው በአዲስ መቃብር ቀብረውታል፡፡ ምንጭ፤ የዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜ ፠፨፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠፨፠ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

#ኒቆዲሞስ፤ #ሰባተኛው_ሳምንትና #የዕለቱ_ምንባባትና_መዝሙራት፤ ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል፤ በዚህ ሳምንትም ይህ ይታሰብበታል፡፡ ‹‹ኒቆዲሞስ››፤ * አይሁዳዊ ሲሆን ከፈሪሳውያን ወገን የነበረ ነው * በኢየሩሳሌም በሀብት ቢሉ በዕውቀት እንዲሁም በሥልጣን የአይሁድ አለቃ ነበር፡፡ * ማታ ማታ ጌታችን ዘንድ እየተገኘ ይማር ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ እንዲህ አስቀምጦልናል፦ ፨ ‹‹ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው ነበር፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ፦ ‹‹መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከእሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህ ተዓምራቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን›› አለው፡፡ ⊚ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ፨ ኒቆዲሞስም፦ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል? ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? አለው። ⊚ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። #ከሥጋ_የተወለደ_ሥጋ_ነው፥ #ከመንፈስም_የተወለደ_መንፈስ_ነው።›› /ዮሐ. ፫፥ ዘ፩-፲፭/ ፨ለምን በሌሊት ይመጣ ነበር? ⊚ አይሁድ ‹‹ማንም ከእኛ ወገን የሆነ የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ከሆነ ሀብት ንብረቱ ይወሰድ፣ በቤተመቅደስ አይግባ፣ መሥዋዕት አይሠዋ›› ብለው ነበርና አይሁድን ፈርቶ፥ ሀብት ንብረቱን ወዶ፥ እንዳይታወቅበት በሌሊት ይመጣ ነበር፡፡ ⊚ በሌላ በኩል ደግሞ የቀን ልብ ባካና ነው፤ ዓይን ብዙ ያያል፥ ሐሳብ ይበታተናል፡፡ በተሰበሰበ ልብ ለመማር፤ በተጨማሪ ‹‹ሊቅ ነኝ›› እያለ ‹‹እስከ ዛሬ ትምህርት አልጨረሰም›› እንዳይሉት በሌሊት ይመጣ ነበር፤ ይህንንም የቀድሞ ሊቃውንት "ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ፤ አኮኑ አጽባሕት እምነ አጽባሕት የአቢ።" በሚል ጕባኤ ቃና ቅኔ አራቅቀውታል፤ ይህ ቅኔም ለተማሪዎች የቅኔ ሀሁ ነው። ⊚ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እንኳን ለመማር የመጣውን እራሱ እየሄደ ያስተምር ነበርና ኒቆዲሞስ ምንም በሌሊት ቢመጣም ማወቅን ፈልጎ ነውና ስለዳግም መወለድ (ስለጥምቀት) በእግዚአብሔር ልጅ ስለማመንና ስለ ጽድቅ ስራ በዝርዝር አስተምሮታል፡፡ ⊚ ኒቆዲሞስ ከአርማትያው ዮሴፍ ጋር በመጨረሻው ቀን በዕለተ ዐርብ ጌታችንን በስቅለቱ ጊዜ፤ ከመስቀል ላይ ሥጋውን ለማውረድና ገንዞ ለመቅበር ቀድሞ ተገኝቷል፡፡ /ዮሐ. ፲፱፥፴፰/ ከኒቆዲሞስ ሕይወት የምንማረው፡- ፩. #ትሕትና፦ ኒቆዲሞስ በትምህርት፣ በሹመት፣ በባለጸግነት የአይሁድ አለቃ ሲሆን፤ አለቅነቱ ግን ከጌታ እግር ስር ቁጭ ብሎ እርሱ ተገኝቶ ለመማር አልከለከለውም፡፡ (የቅኔውን ትርጕም ከመምህራን ይጠይቁ) ፪. #አለማመካኘት፦ ከመጀመሪያ ሰዎች ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ ሰዎች በምክንያተኝነት በአመፅ መንገድ ይጓዛሉ፡፡ ኒቆዲሞስም ወደ ጌታ በመቅረቡ የጸሐፍት ፈሪሳውያን አድማና ግርግር ታላቅ እንቅፋትና ምክንያት መሆን እንደሚችል ያውቃል፡፡ ነገር ግን ይህ ምክንያት በእግዚአብሔር ፊት እንደማያዋጣ አውቆ የሚያዋጣውን አደረገ፡፡ ፫. #ጥበብ፦ በክርስትና ጉዞ ውስጥ ጥበብ የመጀመሪያ ቦታ ትይዛለች፡፡ ኒቆዲሞስም ጕዞውን በጥበብ አደረገ፡፡ በሌሊት ያደረገበት ምክንያት፡- ራሱ መምህር ሆኖ ሌላ ትምህርት አስፈለገው ብለው ሌሎች እንዳይሰናከሉበት፣ የመዓልት ልቦና ስለሚሰበሰብ በቂ ዕውቀት ለማግኘት፣ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት በመዓልትም በሌሊትም ወደ እግዚአብሔር መቅረብ እንዳለብን ለማጠየቅ፣ ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ያሉ ነፍሳት በሲዖል ይገኛሉ ሲል፣ በመዓልትም በሌሊትም ብትፈልጉ ትገኛለች ሲል ነው፡፡ በእውነት ግሩም ጥበብ! ፬. የተነገረውን አምኖ በመቀበሉ፡- ጸሐፍት ፈሪሳውያን ብዙ ምክንያቶች እየደረደሩ የጌታን አምላክነት አምኖ መቀበል ሲያቅታቸው እርሱ ግን ጌትነቱን ለመቀበል ጊዜ አልወሰደበትም፡፡ ፭. ለእውነት መመስከር፡- እነርሱ ሲክዱ ጌታ ላይም ትርፍ ቃል ሲናገሩ፤ በድፍረት መክሰሳቸውን እየነገራቸው የጌታችን አምላክነቱን በግልጽ ይመሰክር ነበር፡፡ ፮. ጽንዓት፡- ብዙዎች በመከራ ጊዜ ላይለዩት ቃል ቢገቡም መጨረሻ ላይ ያኔ በመከራ ሰዓት ከመስቀሉ ሥር ሊገኙ የቻሉ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ኒቆዲሞስም በዚች ሰዓት ያንን መከራ ታግሶ በጽነዓት ከዮሴፍ ጋር የጌታን ሥጋ ከመስቀል አውርደው በአዲስ መቃብር ቀብረውታል፡፡ ምንጭ፤ የዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜ ፠፨፠ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፠፨፠ ፠ በፌስቡክ ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://www.facebook.com/የቀጨኔ-ደብረ-ሰላም-መድኀኔዓለምና-ደብረ-ትጉሃን-ቅዱስ-ገብርኤል-ቤተ-ክርስቲያን-ፍኖተ-ሕይወት-ሰንበት-ትምህርት-ቤት-1620932764891482/ ፠ በቴሌግራም ሊያገኙን ከፈለጉ፤ https://t.me/medihanaelem

በዓለም አቀፍ ደረጃ በዋነኛነትና በግንባር ቀደምትነት የስቅለት በዓል የሚከበርባችው ፪ቱ ታላላቅ ገዳማት ፩ኛ. ኢየሩሳሌም ዴር ሡልጣን ፪ኛ. #ዋልድባ (ዋሊ)፡፡ እንኳን ሰዉ ቦታው ጌታችንን የሚያስብ
+2
በዓለም አቀፍ ደረጃ በዋነኛነትና በግንባር ቀደምትነት የስቅለት በዓል የሚከበርባችው ፪ቱ ታላላቅ ገዳማት ፩ኛ. ኢየሩሳሌም ዴር ሡልጣን ፪ኛ. #ዋልድባ (ዋሊ)፡፡ እንኳን ሰዉ ቦታው ጌታችንን የሚያስብ ገዳም፤ በሃገራችን ጌታችን ራሱ የመሠረተው ብቸኛው ገዳም፨ +፨+ የሕማማትህንና የሞትህን ዜና ስለሰማች ዋልድባ ቅድስት ከዓመት እስከ ዓመት ታለቅሳለች፤ +፨+ ፈጣሪዋ አምላኳ ስለሆንክ፥ በስደትህ ጊዜ የባረካትና የመሠረትሃት፥ ኋላም እንደ ተሰቀልክ ሆነህ የተገለጽክባትና የቀደስካት በመሆኗ ዓመት እስከ ዓመት በሱባዔ ታስብሃለች፡፡ ++መጋቢት 27 ግን እንባዋን በቅዳሴ ጭምር የምታብስበት የደስታዋ ቀን ነው፤ +፨+ ሰብዐ ዓለም ወሰብአ ኢትዮጵያ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፤ ከሰሜን እስከ ደቡብ ተሰብስበው በኢትዮጵያ ደረጃ በዋነኛነትና በግንባር ቀደምትነት የስቅለት በዓልህን ያስባሉ፤ ማዕከላዊና ደቡባዊ የኢትዮጵያ ክፍሎች ከዋልድባ ገዳም በመራቃቸው ብዙሃን ሕዝብ ለክብረ በዓሉ ወደ ዋልድባ ባይሄድም፤ በሰሜናዊ ኢትዮጵያ በተለይም ከጎንደርና ከትግራይ የ7 ዓመት ሕፃናት ሳይቀር ያን በረሐ አቋርጠው ወደ ገዳሙ ይተማሉ ፤ መነኰሳቱም እንደ አሸን ለበዓሉ የሚመጣውን ምዕመን በቋርፍና በጭልቃ፣ በሰሊጥና በሻይ ይቀበሉታል፡፡ ቅዳሴው እንዳበቃም ነፋስ እንደበተነው አሸዋ ባንዴ ሕዝቡ ወደ መንደሩ ይተምማል፡፡

ዜና እረፍት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የብሪታኒያ እና የአየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ አረፉ፡፡ ብፁዕነታቸው ቀደም ሲል ጀምሮ በነበረባቸው ሕመም ሳ
+1
ዜና እረፍት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የብሪታኒያ እና የአየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ አረፉ፡፡ ብፁዕነታቸው ቀደም ሲል ጀምሮ በነበረባቸው ሕመም ሳቢያ፣ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ለንደን ከተማ በሚገኘው አንድ ኢትዮጵያዊ ዶክተር በመኖርያ ቤቱ በቅርብ ክትትል፤ እንክብካቤና በሕክምና ሲረዱ እንደቆዩ የተገለጸ ሲኾን፣ ዛሬ ሰኞ፣ መጋቢት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. በሎንዶን ማረፋቸው ታውቋል፡፡ በበፊት ስማቸው፥ መጋቤ ኃይለ ኢየሱስ ከበደ ይባሉ የነበሩት ብፁዕነታቸው፣ በአራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አንብሮተ ዕድ፣ ጥቅምት 18 ቀን 1983 ዓ.ም. ከተሾሙት ስድስት ኤጲስ ቆጶሳት አንዱ ናቸው።

ዜና እረፍት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የብሪታኒያ እና የአየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ አረፉ፡፡ ብፁዕነታቸው ቀደም ሲል ጀምሮ በነበረባቸው ሕመም ሳ
ዜና እረፍት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የብሪታኒያ እና የአየርላንድ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ አረፉ፡፡ ብፁዕነታቸው ቀደም ሲል ጀምሮ በነበረባቸው ሕመም ሳቢያ፣ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ለንደን ከተማ በሚገኘው አንድ ኢትዮጵያዊ ዶክተር በመኖርያ ቤቱ በቅርብ ክትትል፤ እንክብካቤና በሕክምና ሲረዱ እንደቆዩ የተገለጸ ሲኾን፣ ዛሬ ሰኞ፣ መጋቢት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. በሎንዶን ማረፋቸው ታውቋል፡፡ በበፊት ስማቸው፥ መጋቤ ኃይለ ኢየሱስ ከበደ ይባሉ የነበሩት ብፁዕነታቸው፣ በአራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ አንብሮተ ዕድ፣ ጥቅምት 18 ቀን 1983 ዓ.ም. ከተሾሙት ስድስት ኤጲስ ቆጶሳት አንዱ ናቸው።

*+* ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፤ ፊቴንም ቢፈልጉ፤ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፤ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፤ ኀጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፤ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ። ፪ኛ ዜና ፯፥ ፲፫ *+* ንስ
*+* ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፤ ፊቴንም ቢፈልጉ፤ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፤ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፤ ኀጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፤ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ። ፪ኛ ዜና ፯፥ ፲፫ *+* ንስሐ ግቡ ኀጢአትም እንቅፋት እንዳይሆንባችሁ ከኀጢአታችሁ ተመለሱ። ሕዝ. ፲፰፥፴ *+* ሰማይ ስማ፥ ምድርም አድምጪ፤ ..... እሽ ብትሉና ብትሰሙኝ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እንቢ ብትሉና ባትሰሙኝ ግን ሰይፍ ትበላችኋለች፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሯልና። ት.ኢሳ. ፩፥፩